አስተናጋጁ..!
ባልና ሚስት ወደ አንድ ሬስቶራንት ለመገባበዝ ይሄዳሉ
ብዙ ጊዜ ባልና ሚስት ወደ ሬስቶራንት ሲሄዱ ከምግቡ ይልቅ ጨዋታቸውን ይደምቃል ከጥቂት ቆይታ በኃላ አስተናጋጁን ለመጥራት ያጨበጭባሉ
አስተናጋጁ አልመጣም.....
ድጋሚ አጨበጨቡ አሁንም አልመጣም....
ለሶስተኛ ጊዜ አጨበጨቡ ...ድንገት ከጥግ በኩል አንድ ቀብረር ያለ አስተናጋጅ ወደነሱ መጣ...
አስተናጋጅ፦ "ዝም ብሎ ጭብጨባ ምንድን ነው ? ሰርግ ቤት ነው እንዴ ያላችሁት ?
.....ና... ወንድሜ ታዘዝ ነው የሚባለው "
.
በጣም ይደነግጡና
ሚስት ፦"ሆቴል አስተናግደህ እንደዚህ የሆንክ የኣለም ዋንጫ ብታዘጋጅ ምን ልትሆን ነው "
.
አስተናጋጅ፦ " ዝም ብለሽ አትለፍልፊ የመጣሽበትን ብቻ ተናገሪ "
.
ሚስት ፦ " በቃ ታዘዘን ምን ምን አለ ? "
.
አስተናጋጅ፦ "ቋንጣ ፍርፍር አለ .... እንቁላል ፍርፍር አለ....ጥብስ አለ.. እንደገና ቋንጣ ፍርፍር አለ .... እንደገና ጥብስ አለ እንደገና ....."
.
በጣም ይናደዱና
"በቃ ጥብስ አምጣልን!! "
.
አስተናጋጁ፦ "ይመጣላችኃላ !! ይሄዳል ይደርስና ግን አያዝም ....ድጋሚ ወደ ተስተናጋጆቹ ጋር ይመጣና
" ጥብስ ነው ያላችሁኝ ኣይደል ? "
.
"አዎ ጥብስ ነው "
.
"በዳቦ ነው በእንጀራ ? "
.
በጣም ይናደዱና ..
"በእንጀራ አርግልን "
.
አሁንም አላዘዘም ይሄድና ይመለሳል ...
"የሚጠጣ ነገርስ ምን ላምጣ ? "
.
ስልችት ይለውና ባልየው
"ለሷ ፋንታ ለኔ ኮካ "
.
"ይመጣላችዋላ ታድያ ምንድን ነው ግልምጫው "
አሁንም ይሄዳል ግን ሳያዝ ድጋሚ ተመልሶ ይመጣል...
"ለስላሳው ከውጭ ነው ከውስጥ ? "
.
እጅግ ይናደዱና...
"ተወው በቃ ባለቤቱን ብቻ ጥራልን !"
.
"ይጠራላችዋላ ባለቤት መጥራት ብርቅ ነው እንዴ ! "
አሁንም ይሄዳል ተመልሶ ይመጣል ...
"ባለቤቱ ወንዱን ነው ሴቷን??
@write_event
ባልና ሚስት ወደ አንድ ሬስቶራንት ለመገባበዝ ይሄዳሉ
ብዙ ጊዜ ባልና ሚስት ወደ ሬስቶራንት ሲሄዱ ከምግቡ ይልቅ ጨዋታቸውን ይደምቃል ከጥቂት ቆይታ በኃላ አስተናጋጁን ለመጥራት ያጨበጭባሉ
አስተናጋጁ አልመጣም.....
ድጋሚ አጨበጨቡ አሁንም አልመጣም....
ለሶስተኛ ጊዜ አጨበጨቡ ...ድንገት ከጥግ በኩል አንድ ቀብረር ያለ አስተናጋጅ ወደነሱ መጣ...
አስተናጋጅ፦ "ዝም ብሎ ጭብጨባ ምንድን ነው ? ሰርግ ቤት ነው እንዴ ያላችሁት ?
.....ና... ወንድሜ ታዘዝ ነው የሚባለው "
.
በጣም ይደነግጡና
ሚስት ፦"ሆቴል አስተናግደህ እንደዚህ የሆንክ የኣለም ዋንጫ ብታዘጋጅ ምን ልትሆን ነው "
.
አስተናጋጅ፦ " ዝም ብለሽ አትለፍልፊ የመጣሽበትን ብቻ ተናገሪ "
.
ሚስት ፦ " በቃ ታዘዘን ምን ምን አለ ? "
.
አስተናጋጅ፦ "ቋንጣ ፍርፍር አለ .... እንቁላል ፍርፍር አለ....ጥብስ አለ.. እንደገና ቋንጣ ፍርፍር አለ .... እንደገና ጥብስ አለ እንደገና ....."
.
በጣም ይናደዱና
"በቃ ጥብስ አምጣልን!! "
.
አስተናጋጁ፦ "ይመጣላችኃላ !! ይሄዳል ይደርስና ግን አያዝም ....ድጋሚ ወደ ተስተናጋጆቹ ጋር ይመጣና
" ጥብስ ነው ያላችሁኝ ኣይደል ? "
.
"አዎ ጥብስ ነው "
.
"በዳቦ ነው በእንጀራ ? "
.
በጣም ይናደዱና ..
"በእንጀራ አርግልን "
.
አሁንም አላዘዘም ይሄድና ይመለሳል ...
"የሚጠጣ ነገርስ ምን ላምጣ ? "
.
ስልችት ይለውና ባልየው
"ለሷ ፋንታ ለኔ ኮካ "
.
"ይመጣላችዋላ ታድያ ምንድን ነው ግልምጫው "
አሁንም ይሄዳል ግን ሳያዝ ድጋሚ ተመልሶ ይመጣል...
"ለስላሳው ከውጭ ነው ከውስጥ ? "
.
እጅግ ይናደዱና...
"ተወው በቃ ባለቤቱን ብቻ ጥራልን !"
.
"ይጠራላችዋላ ባለቤት መጥራት ብርቅ ነው እንዴ ! "
አሁንም ይሄዳል ተመልሶ ይመጣል ...
"ባለቤቱ ወንዱን ነው ሴቷን??
@write_event
ስብሐት ጫት ሲቅም የደረሰው አንድ ወጣት ይመክረዋል ፡፡ " ጋሽ ስብሐት አይቃሙ መቃም ሱስ ያሲዛል እኔ አልቅምም" ስብሐት ዝም ይልና ሲጋራ ይለኩሳል ወጣቱ ምክሩን ይቀጥላል:: ጋሽ ስብሐት አያጭሱ ማጨስ ሱስ ያሲዛል እኔ አላጨስም፡፡ስብሐት ዝም ይልና ቡና ያዛል ፡፡ ትጠጣለህ ሲል ወጣቱን ጋበዘው ቡና አልጠጣም ሱስ ያሲዘኛል ወጣቱ መለሰ ስብሐት ዝም ይለዋል፡፡በመጨረሻም ሁሉም አልቆ መጠጣት ሲጀምር መጠጥ ሱስ ያሲዛል አይጠጡ፡፡ እኔ ሱስ እንዳይዘኝ አልጠጣም አለው ፡፡ ስብሐት ገረፍ አርጎ አየውና "ከሱስ አላመለጥክም ሱስ የመፍራት ሱስ አለብህ" አለው ::
አለማየሁ ገላጋይ <<ስበሀት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት>>ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት>>
@write_event
አለማየሁ ገላጋይ <<ስበሀት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት>>ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት>>
@write_event
ለፈገግታ ያህል..!
ሙላ ናስሩዲን ሃጅ ወደሳውዲ ሄዶ ነው። ሰው ከመብዛቱ የተነሣ ናስሩዲን ማደሪያ ማግኘት አልቻለም፡፡ በመጨረሻ አንድ ሆቴል ውስጥ ጥንድ አልጋ ያለው እንድ ክፍል አግኝቶ ገባ። ብዙ ሳይቆይ ሁለተኛው አልጋ ተከራይቶ ሰውዬው መጣ። ናስሩዱን ሰውየውን ሲያየው ልክ እንደሱ ነበር የለበሰው። ቁርጥ እራሱን። መተኛት አልቻለም፡፡ ሰውየው ነቅቶ
“ወንድሜ፣ ለምን አትተኛም?” አለው።
“አንድ ችግር ገጥሞኝ ነው።”
“ምን?”
“እኔና አንተ ተመሳሳይ ነን። ተኝተን ስንነቃ እራሳችንን መለየት ቢያቅተንስ?” አለ ናስሩዲን። ሰውየው ለካ ተንኮልኛ ኖሯል። ዞር ዞር ሲል አንዲት አሻንጉሊት ጥግ ላይ ተቀምጣ ይመለከታል። ያነሳና እግሩ ላይ አስሮ...
“አሁን ተኛ፣ አሻንጉሊት እግሬ ላይ የታሰረው እኔ ነኝ ።” ይለዋል። ናስሩዲን ችግሩ ስለተፈታለት አመስግኖ ይተኛል፡፡ ሰውዬው በጠዋት ሲወጣ አሻንጉሊቱን ከእግሩ ላይ ፈቶ ናስሩዲን ላይ አስሮት ይሄዳል። ናስሩዲን ሲነቃ ደነገጠ። እየሮጠ ወደ አደባባይ በመውጣት እንዲህ አለ “አንድ ሰው ተሳስቶ እኔን ይዞ ሄዷል፡፡ እሱ እኔ ነውና የት ነው የማገኘው?” ...አለ ይባላል።
©አለማየሁ ገላጋይ
Join
@write_event
ሙላ ናስሩዲን ሃጅ ወደሳውዲ ሄዶ ነው። ሰው ከመብዛቱ የተነሣ ናስሩዲን ማደሪያ ማግኘት አልቻለም፡፡ በመጨረሻ አንድ ሆቴል ውስጥ ጥንድ አልጋ ያለው እንድ ክፍል አግኝቶ ገባ። ብዙ ሳይቆይ ሁለተኛው አልጋ ተከራይቶ ሰውዬው መጣ። ናስሩዱን ሰውየውን ሲያየው ልክ እንደሱ ነበር የለበሰው። ቁርጥ እራሱን። መተኛት አልቻለም፡፡ ሰውየው ነቅቶ
“ወንድሜ፣ ለምን አትተኛም?” አለው።
“አንድ ችግር ገጥሞኝ ነው።”
“ምን?”
“እኔና አንተ ተመሳሳይ ነን። ተኝተን ስንነቃ እራሳችንን መለየት ቢያቅተንስ?” አለ ናስሩዲን። ሰውየው ለካ ተንኮልኛ ኖሯል። ዞር ዞር ሲል አንዲት አሻንጉሊት ጥግ ላይ ተቀምጣ ይመለከታል። ያነሳና እግሩ ላይ አስሮ...
“አሁን ተኛ፣ አሻንጉሊት እግሬ ላይ የታሰረው እኔ ነኝ ።” ይለዋል። ናስሩዲን ችግሩ ስለተፈታለት አመስግኖ ይተኛል፡፡ ሰውዬው በጠዋት ሲወጣ አሻንጉሊቱን ከእግሩ ላይ ፈቶ ናስሩዲን ላይ አስሮት ይሄዳል። ናስሩዲን ሲነቃ ደነገጠ። እየሮጠ ወደ አደባባይ በመውጣት እንዲህ አለ “አንድ ሰው ተሳስቶ እኔን ይዞ ሄዷል፡፡ እሱ እኔ ነውና የት ነው የማገኘው?” ...አለ ይባላል።
©አለማየሁ ገላጋይ
Join
@write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
#ፈገግታ
#የለመደች_ጦጣ ...
አንድ ቀን ናስሩዲን አሀያዉን ጨው ጥርቅም አድርጎ ጭኖ ገበያ ወጣ ። በመንገዱ ላይ የነበርዉ ወንዝ ሞላ ብሎ ስላጋጠመው ሰፋ ያለ መልካ ፈልጎ
አሀያዉን እየጐተተ ለመሻገር ወንዝ ውስጥ ገባ ፡ ወንዙ መሐል እንደ ደረሰ ፡ አህያ ሆዬ አገሮቹን ወንዙ ውስጥ ተክሎ አልነቃነቅም አለ ፡ ናስሩዲን በመናደድ በያዘው ሽመል እሀያውን ይነርተዉ
ጀመር ፡ አሀያው ዱላ ሲበዛበት እየወደቀና አየተነግ ወንዙን ተሻገሩ ፡፡ ጨዉ ወንዙ ውስጥ ሟምቶ በመገባደዱ አሀያው ሸክሙ ስለቀለለው መንገዱን
በፍጥነት ማቀላጠፉን ተያያዘው ፡
በሌላ ጊዜ ናስሩዲን ያንኑ አህያ ጭኖ ገበያ ሲወጣ ከወንዙ ደረሰ ፡ ናስሩዲን አሀያዉን አየጐተተ ወንዙ ውስጥ ገባ ፡ መሐል እንደ ደረሱ እሀያው አሁንም ግትር ብሎ በመቆም ጭነቱን ወራጅ ውኃ
ያስመታ ጀመር ፡ በዚህ ጊዜ ናስሩዲን እሀያውን አልመታውም ፡ ለጥቂት ጊዜ አጠገቡ ዝም ብሎ
ከቆመ በኋላ መሳቢያውን ገመድ ጐተት ጐተት አደረገው ፡ አሀያወም እንደ ምንም ብሎ ወንዙን
ተሻገረ ፡ መንገዳቸውን ሊጀምሩ ሲሉ ከጭነቱ ክብደት የተነሣ የአሀያው ወገብ ተለምጦ መሬት ሊነካደረሰ ፡
ናስሩዲንም አሀያውን "የኛ ብልጥ ፡ ወንዝ
አቋርጠሀ ባለፍሀ ቊጥር እንደ ለመድከው የጭነትሀ ክብደት የሚቃለልልሀ መስሎሀ ነበር ፡ ዛሬ ጨው
ሳይሆን ጥጥ ነው የተጫንከው" አለው ፡
... #የለመደች_ጦጣ_ሁል_ጊዜ_ሸምጣጣ
@write_event
#የለመደች_ጦጣ ...
አንድ ቀን ናስሩዲን አሀያዉን ጨው ጥርቅም አድርጎ ጭኖ ገበያ ወጣ ። በመንገዱ ላይ የነበርዉ ወንዝ ሞላ ብሎ ስላጋጠመው ሰፋ ያለ መልካ ፈልጎ
አሀያዉን እየጐተተ ለመሻገር ወንዝ ውስጥ ገባ ፡ ወንዙ መሐል እንደ ደረሰ ፡ አህያ ሆዬ አገሮቹን ወንዙ ውስጥ ተክሎ አልነቃነቅም አለ ፡ ናስሩዲን በመናደድ በያዘው ሽመል እሀያውን ይነርተዉ
ጀመር ፡ አሀያው ዱላ ሲበዛበት እየወደቀና አየተነግ ወንዙን ተሻገሩ ፡፡ ጨዉ ወንዙ ውስጥ ሟምቶ በመገባደዱ አሀያው ሸክሙ ስለቀለለው መንገዱን
በፍጥነት ማቀላጠፉን ተያያዘው ፡
በሌላ ጊዜ ናስሩዲን ያንኑ አህያ ጭኖ ገበያ ሲወጣ ከወንዙ ደረሰ ፡ ናስሩዲን አሀያዉን አየጐተተ ወንዙ ውስጥ ገባ ፡ መሐል እንደ ደረሱ እሀያው አሁንም ግትር ብሎ በመቆም ጭነቱን ወራጅ ውኃ
ያስመታ ጀመር ፡ በዚህ ጊዜ ናስሩዲን እሀያውን አልመታውም ፡ ለጥቂት ጊዜ አጠገቡ ዝም ብሎ
ከቆመ በኋላ መሳቢያውን ገመድ ጐተት ጐተት አደረገው ፡ አሀያወም እንደ ምንም ብሎ ወንዙን
ተሻገረ ፡ መንገዳቸውን ሊጀምሩ ሲሉ ከጭነቱ ክብደት የተነሣ የአሀያው ወገብ ተለምጦ መሬት ሊነካደረሰ ፡
ናስሩዲንም አሀያውን "የኛ ብልጥ ፡ ወንዝ
አቋርጠሀ ባለፍሀ ቊጥር እንደ ለመድከው የጭነትሀ ክብደት የሚቃለልልሀ መስሎሀ ነበር ፡ ዛሬ ጨው
ሳይሆን ጥጥ ነው የተጫንከው" አለው ፡
... #የለመደች_ጦጣ_ሁል_ጊዜ_ሸምጣጣ
@write_event
#ፈገግታ
#ነገር_በነገር_ይጠቀሳል ...
ናስሩዲን የሚኖርበት አገር ንጉሥ ባለሟሎቹን ስብስቦ ፡ ከአገሬው ሕዝብ መካከል በጨዋነቱ የሚታወቀ ሰው ተፈልጎ እንዲቀርብለትና የዳኝነት ሹመት ሊሰጠው እንዳሰበ ያስታውቃቸዋል ። የንጉሡን ትእዛዝ የሚያስፈጽም አንድ የመልእከተኞች ቡድን ይሠየምና በአገሩ ውስጥ እየተዘዋወረ መስፈርቱን የሚያሟላ ተስማሚ ሰው ለማግኘት ሥራወን ይጀራል፡ የንጉሡ ፍላጐት ወሬም ከናስሩዲን ጆሮ ይደርሳል ፡ ናስሩዲን ከሚኖርባት ከተማ ነዋሪዎች መካከል
የንጉሡ መልእክተኞች አንዳያነጋግሯቸው ከተመረጡት ሰዎች መካከል እርሱ አንዱ ይሆናል ፡ ናስሩዲን ፡ በተያዘለት ቀጠሮ፡ ከለበሰው ልብስ ላይ የዓሣ ማጥመጃ መረብ ደርቦ መልእከተኞቹ ፊት ይቀርባል ፡ በናስሩዲን አለባበስ የተገረመው የመልእከተኞች መሪ ፤ "እስከ ዛሬ በያለበት ስንዘዋወር እንዳንተ የለበሰ ሰው ፈጽሞ አላጋጠመንም ፡ በልብስሀ ላይ የዓሣ ማጥመጃ መረብ የደረብክበት ምክንያት ምንድን ነው?" በማለት ይጠይቀዋል ።
"ከሥር ክመሠረቴ ድሃ የድሃ ልጅ በመሆኔ ፤ መተዳደሪያዬም ዓሣ ማጥመድ ነበር ፡ ይሀንን መረብ ዘወትር በልብሴ ላይ የምደርበው ያነን የድሮ ኑሮዬን አንዳልዘነጋ በማለት ነው።" ሲል ናስሩዲን ለቀረበለት ጥያቄ መልስ ይሰጣል ፡ መልአክተኛቹ ተልአኮአቸውን ፈጽመው ለንጉሡ ባቀረቡት ሪፖርት የናስሩዲን ስም ከሁሉ ጐልቶ ይታያል ።
ንጉሡም ስለ ናስሩዲን የቀረበወን ዘገባ በመቀበል የዳኝነቱን ሹመት ይሰጠዋል ፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ ፡ ምርጫውን ካካሄዱት ባለሥልጣኖች አንዱ ፡ ናስሩዲን በታላቅ ችሎት ላይ ተሠይሞ አቤቱታ ሲሰማ ፡ የፍርድ ብያኔ ሲሰጥ ፡ ለተበደለው ሲፈርድና በደለኛወን ሲቀጣ ያገኘዋል ፡ ከችሎት መልስ ፡ ናስሩዲንና ባለሥልጣኑ ጥቂት ሲጨዋወቱ ከቆዩ በኋላ፡
"ያን መረብሀን ምነው ዛሬ አላየሁትም"
በማለት ይጠይቀዋል ።
ናስሩዲንም ፡ "የምን መረብ ነው ደግሞ፡ ዓሣው ከተያዘ በኋላ መረቡ ምን ይፌይዳል" በማለት ይመልሳል ፡
... #ነገር_በነገር_ይጠቀሳል_እሾህ_በእሾ_ይነቀላል
@write_event
#ነገር_በነገር_ይጠቀሳል ...
ናስሩዲን የሚኖርበት አገር ንጉሥ ባለሟሎቹን ስብስቦ ፡ ከአገሬው ሕዝብ መካከል በጨዋነቱ የሚታወቀ ሰው ተፈልጎ እንዲቀርብለትና የዳኝነት ሹመት ሊሰጠው እንዳሰበ ያስታውቃቸዋል ። የንጉሡን ትእዛዝ የሚያስፈጽም አንድ የመልእከተኞች ቡድን ይሠየምና በአገሩ ውስጥ እየተዘዋወረ መስፈርቱን የሚያሟላ ተስማሚ ሰው ለማግኘት ሥራወን ይጀራል፡ የንጉሡ ፍላጐት ወሬም ከናስሩዲን ጆሮ ይደርሳል ፡ ናስሩዲን ከሚኖርባት ከተማ ነዋሪዎች መካከል
የንጉሡ መልእክተኞች አንዳያነጋግሯቸው ከተመረጡት ሰዎች መካከል እርሱ አንዱ ይሆናል ፡ ናስሩዲን ፡ በተያዘለት ቀጠሮ፡ ከለበሰው ልብስ ላይ የዓሣ ማጥመጃ መረብ ደርቦ መልእከተኞቹ ፊት ይቀርባል ፡ በናስሩዲን አለባበስ የተገረመው የመልእከተኞች መሪ ፤ "እስከ ዛሬ በያለበት ስንዘዋወር እንዳንተ የለበሰ ሰው ፈጽሞ አላጋጠመንም ፡ በልብስሀ ላይ የዓሣ ማጥመጃ መረብ የደረብክበት ምክንያት ምንድን ነው?" በማለት ይጠይቀዋል ።
"ከሥር ክመሠረቴ ድሃ የድሃ ልጅ በመሆኔ ፤ መተዳደሪያዬም ዓሣ ማጥመድ ነበር ፡ ይሀንን መረብ ዘወትር በልብሴ ላይ የምደርበው ያነን የድሮ ኑሮዬን አንዳልዘነጋ በማለት ነው።" ሲል ናስሩዲን ለቀረበለት ጥያቄ መልስ ይሰጣል ፡ መልአክተኛቹ ተልአኮአቸውን ፈጽመው ለንጉሡ ባቀረቡት ሪፖርት የናስሩዲን ስም ከሁሉ ጐልቶ ይታያል ።
ንጉሡም ስለ ናስሩዲን የቀረበወን ዘገባ በመቀበል የዳኝነቱን ሹመት ይሰጠዋል ፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ ፡ ምርጫውን ካካሄዱት ባለሥልጣኖች አንዱ ፡ ናስሩዲን በታላቅ ችሎት ላይ ተሠይሞ አቤቱታ ሲሰማ ፡ የፍርድ ብያኔ ሲሰጥ ፡ ለተበደለው ሲፈርድና በደለኛወን ሲቀጣ ያገኘዋል ፡ ከችሎት መልስ ፡ ናስሩዲንና ባለሥልጣኑ ጥቂት ሲጨዋወቱ ከቆዩ በኋላ፡
"ያን መረብሀን ምነው ዛሬ አላየሁትም"
በማለት ይጠይቀዋል ።
ናስሩዲንም ፡ "የምን መረብ ነው ደግሞ፡ ዓሣው ከተያዘ በኋላ መረቡ ምን ይፌይዳል" በማለት ይመልሳል ፡
... #ነገር_በነገር_ይጠቀሳል_እሾህ_በእሾ_ይነቀላል
@write_event
" ... እዚህ አዲሳባ ውስጥ አንዳንድ ቦታ እንጀራ በቢላ ሲቆረስ እናያለን። ይኼ በቢላ እንጀራ የመቁረስ ባህል የጀመረው ማን ነው ? ለምን ጀመሩ ?
እንጀራን በቢላ መቁረስ እንጀራን ወደ ዳቦ ለማውረድ መጣር እንደሆነ አልተረዱትም?
የእኛ ትልቁ ችግራችን እውር ኮፒ አድራጊዎች መሆናችን ነው ። ፈረንጅ ዳቦ ሲቆርስ አይተን ከዛ በጭፍን ያለ ጥየቃ ያለትንታኔ ተበደርን ። የዚህ ችግር መነሻው በራሳችን ማመን አለመቻላችን ነው ። በራሱ የማያምን ሕዝብ ወደ ባርነት የሚጓዝ ነው።
ለመሆኑ እንጀራ ለመቁረስ እጅ አነሳትና ነው ቢላ የመጣባት ? በእንግሊዘኛ ኦቨርኪል (overkill) ይባላል። ዝንብ ለመግደል ታንክ ስታወጣ ማለት ነው ።
እንጀራ ቢደርቅ እንኳን አይፈነክትም :: እንጀራ ጥፊ እንኳን አይሆንም :: ምኑ ሰይፍ ያስመዝዛል?
ግን እንጀራ አገር ያቆማል ...”
#ምንጭ
እቴሜቴ ሎሚሽታ ----አዳም ረታ
Share :-@write_event
እንጀራን በቢላ መቁረስ እንጀራን ወደ ዳቦ ለማውረድ መጣር እንደሆነ አልተረዱትም?
የእኛ ትልቁ ችግራችን እውር ኮፒ አድራጊዎች መሆናችን ነው ። ፈረንጅ ዳቦ ሲቆርስ አይተን ከዛ በጭፍን ያለ ጥየቃ ያለትንታኔ ተበደርን ። የዚህ ችግር መነሻው በራሳችን ማመን አለመቻላችን ነው ። በራሱ የማያምን ሕዝብ ወደ ባርነት የሚጓዝ ነው።
ለመሆኑ እንጀራ ለመቁረስ እጅ አነሳትና ነው ቢላ የመጣባት ? በእንግሊዘኛ ኦቨርኪል (overkill) ይባላል። ዝንብ ለመግደል ታንክ ስታወጣ ማለት ነው ።
እንጀራ ቢደርቅ እንኳን አይፈነክትም :: እንጀራ ጥፊ እንኳን አይሆንም :: ምኑ ሰይፍ ያስመዝዛል?
ግን እንጀራ አገር ያቆማል ...”
#ምንጭ
እቴሜቴ ሎሚሽታ ----አዳም ረታ
Share :-@write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
❤️
"ሁሉን ነገር ካስተዋሉት ይገርማል
የኑሮ ትንሽ የለውም. . .
እዛ የወደቀች ሳር አስገራሚ ናት፤ ወፍ ለቅሞ ጎጆ ይሰራባታል . . . .
ጠዋት እዚህ ፀሀይ ስሞቅ የቆረጥኩት የአውራ ጣቴ ጥፍር ለስንት ጉንዳን እራት ይሆናል? ባላርስም አበላሁ ማለት አይደል? "
/መረቅ - አዳም ረታ/
❀:✧๑♡๑✧❀|
@write_event
@write_event
ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ
"ሁሉን ነገር ካስተዋሉት ይገርማል
የኑሮ ትንሽ የለውም. . .
እዛ የወደቀች ሳር አስገራሚ ናት፤ ወፍ ለቅሞ ጎጆ ይሰራባታል . . . .
ጠዋት እዚህ ፀሀይ ስሞቅ የቆረጥኩት የአውራ ጣቴ ጥፍር ለስንት ጉንዳን እራት ይሆናል? ባላርስም አበላሁ ማለት አይደል? "
/መረቅ - አዳም ረታ/
❀:✧๑♡๑✧❀|
@write_event
@write_event
ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ
. አምራች እና ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡
በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡
በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?› ሲል ጠየቀው፡፡
ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡
@write_event
በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡
በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?› ሲል ጠየቀው፡፡
ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡
@write_event
🍁.... ወጣነት ማለት ፉሽን ተከታይ ዘናጭ ተሽቀርቃሪ ማለት አይደለም ወጣትነት ራስን በሱሶች ማጠር ማለት አንደለም።
"ወጣትነት ውቂያኖስ ነው" ወጣነት ማለት አድማሠ ሀላፊነት
ነው ... ወጣትነት እውቀት ለማስፉት የምንጋደልቀበት ሠአት ነው ወጣትነት
ከፍርሀት፣ አይቻልም እና አይሳካልኝም የሚለውን እስር በጣጥሶ ማለፍ
ነው።ወጣትነትለ አንዳች ስኬት በኩራት እና በሞራል መራመድ ነው።
ከ ኤጭ መፅሀፍ የተቀነጨበ ( አዘርግ)
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
"ወጣትነት ውቂያኖስ ነው" ወጣነት ማለት አድማሠ ሀላፊነት
ነው ... ወጣትነት እውቀት ለማስፉት የምንጋደልቀበት ሠአት ነው ወጣትነት
ከፍርሀት፣ አይቻልም እና አይሳካልኝም የሚለውን እስር በጣጥሶ ማለፍ
ነው።ወጣትነትለ አንዳች ስኬት በኩራት እና በሞራል መራመድ ነው።
ከ ኤጭ መፅሀፍ የተቀነጨበ ( አዘርግ)
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
🍁ሙሉጌታ ተስፉዬ የተባለ ገጣሚ
ምን ይላል መሠላችሁ! አለም ላይ ስትኖር ሁለት እድል አላችሁ ወይ ራሣችሁን ችላችሁ መቆም አለበለዚያ መቃብራችሁን ቆፍራችሁ መግባት። ሌላ አማራጭ የላችሁም ይላል..... የአለም ቁጥር አንድ ጀግና ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ጀግና ማለት ጦር ሜዳ ብዙ ገድሎች የሰራ አይደለም። ሠው መግደል ጀግንነት ሣይሆን ሠይጣናዊት ነው። ጀግና ማለት ብዙ ብሮች ያሉት ሀብታም አይደለም ጀግና ማለት ጫካ ውስጥ የሠራውን ገድል ከተማ ውስጥ መጥቶ እየተኮፈሰ ይህን አደረኩኝ የሚል አይደለም!
ትልቅ እውነተኛ ጀግና አምባገነን መሪ ፊት አንዳችም ሣይፈራ እውነቱን የተናገረ እና ውስጡ ያለውን ስንፍና ያሸነፈ ብቻ ነው።
የቆሸሹ ሳቆች
(አዘርግ)
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
ምን ይላል መሠላችሁ! አለም ላይ ስትኖር ሁለት እድል አላችሁ ወይ ራሣችሁን ችላችሁ መቆም አለበለዚያ መቃብራችሁን ቆፍራችሁ መግባት። ሌላ አማራጭ የላችሁም ይላል..... የአለም ቁጥር አንድ ጀግና ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ጀግና ማለት ጦር ሜዳ ብዙ ገድሎች የሰራ አይደለም። ሠው መግደል ጀግንነት ሣይሆን ሠይጣናዊት ነው። ጀግና ማለት ብዙ ብሮች ያሉት ሀብታም አይደለም ጀግና ማለት ጫካ ውስጥ የሠራውን ገድል ከተማ ውስጥ መጥቶ እየተኮፈሰ ይህን አደረኩኝ የሚል አይደለም!
ትልቅ እውነተኛ ጀግና አምባገነን መሪ ፊት አንዳችም ሣይፈራ እውነቱን የተናገረ እና ውስጡ ያለውን ስንፍና ያሸነፈ ብቻ ነው።
የቆሸሹ ሳቆች
(አዘርግ)
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
እንደ ቶማስ በአይንህ ካላየህ በ እጅህ ካልዳሠሥክ አትረካም።
የትውልድ ሕመም ይህነው አንተንም የዚህ ሕመም ተጠቂ ትውልድ ምሣሌ ነህና ጫፉን ነግረንህ በዕምነት እንድትሆን ችላ ብንልህ ለማወቅ ትዳክራለህ። ያወቅከውን ደግሞ ትዘራዋለህ አንተ የትውልዱ ናሙና ነህ.. አንተ የተገዛከውን ገና ብዙዎች ይገዙታል ያወቅከውንና የደረስክበትንም መፃፍ ስለማይቀር ያንን ተከትለው ብዙዎች ይጓዛሉ። ግን ልብ በል! ብታገኙትም አታምኑም። እርሱ ራሱ ለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አለ? ትላላችሁ አንተ በነገርካቸው መሠረት ሌሎች ካላመኑህ ደግሞ አንተም ዕምነትህ ይከዳሀል።
"ራሣችሁንና የራሣችሁን ዕውነት የምታረጋግጡት በምዕራቡ አለም መለኪያ ብቻ ነውና "
(እመጓ) በአለማየሁ ዋሴ ዶ/ር
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
የትውልድ ሕመም ይህነው አንተንም የዚህ ሕመም ተጠቂ ትውልድ ምሣሌ ነህና ጫፉን ነግረንህ በዕምነት እንድትሆን ችላ ብንልህ ለማወቅ ትዳክራለህ። ያወቅከውን ደግሞ ትዘራዋለህ አንተ የትውልዱ ናሙና ነህ.. አንተ የተገዛከውን ገና ብዙዎች ይገዙታል ያወቅከውንና የደረስክበትንም መፃፍ ስለማይቀር ያንን ተከትለው ብዙዎች ይጓዛሉ። ግን ልብ በል! ብታገኙትም አታምኑም። እርሱ ራሱ ለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አለ? ትላላችሁ አንተ በነገርካቸው መሠረት ሌሎች ካላመኑህ ደግሞ አንተም ዕምነትህ ይከዳሀል።
"ራሣችሁንና የራሣችሁን ዕውነት የምታረጋግጡት በምዕራቡ አለም መለኪያ ብቻ ነውና "
(እመጓ) በአለማየሁ ዋሴ ዶ/ር
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ
ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያን ፍቅርን
ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም
ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን
እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው
በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ። ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው።
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያን ፍቅርን
ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም
ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን
እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው
በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ። ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው።
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
➫
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
🌿ውስጣዊ ስሜቶች አይፃፉም፣ ቢፃፉ እንኳ ፍፃሜ የላቸውም። የአንዳንድ ነገሮች መሰባበር ሲሰማህ ትንሽ ራቅ በል። ንግግር ስሜትህን የመግለፅ አቅም ሲያጥረውም ትንሽ ዝም በል።
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
🌿ውስጣዊ ስሜቶች አይፃፉም፣ ቢፃፉ እንኳ ፍፃሜ የላቸውም። የአንዳንድ ነገሮች መሰባበር ሲሰማህ ትንሽ ራቅ በል። ንግግር ስሜትህን የመግለፅ አቅም ሲያጥረውም ትንሽ ዝም በል።
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
ከጥላቻ መንፈስ ፅዱ ሆነን እና በቅን መንፈስ ላይ ሆነን ስናየው እስልምና በራሱ እጅግ አስገራሚ የሆኑ ሰብአዊነትን የተላበሱ ህጎችን ተላብሶ እናገኘዋለን፡፡
...
በእስልምና ድሆችን ለመርዳት የሚሰጥ ማንኛውም እርዳታ "ምፅዋት" ወይም "ሰደቃ" ተብሎ ይጠራል፡፡ በእስልምና ህግ መሰረት "ደሀ ስለሆንኩ ሰውን መርዳት አልችልም" ብሎ ነገር በአላህ ፊት እንደ ምክንያት ማቅረብ አይቻልም... ምክንያቱም ሰውን ለመርዳት ሀብታም መሆን አይጠበቅብህም...
...
ይልቁንስ ብዙ አይነት ምፅዋቶች እንዳሉ እስልምና ያዛል... ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ፈገግታ ነው፡፡ አየህ መንገድ ላይ ነገ ስለምትበላው ቁራሽ ዳቦ እያሰብክ ስታዘግም "መሽናት ክልክል ነው" የሚል ፅሁፍ ከተፃፈበት ግንብ ስር ከአንተ የባሰ ምስኪን ተኮራምቶ ተኝቶ ታገኘዋለህ...
...
ታዲያ በእስልምና ህግ መሠረት ደሀ ነኝና ወይም ደግሞ በኪሴ ሰባራ ሳንቲም የለም ብለህ ሰውዬውን እያየህ ከንፈርህን እየመጠጥክ አታልፍም፡፡ ይልቁንስ አላህ በተፈጥሮ የሰጠህን ፈገግታ ለሰውዬው ትለግሰዋለህ፡፡
...
በቃ ይሄው ነው!!! ከጥርሶችህ ፍልቃቂ ውስጥ በሚወጣ ፈገግታ ካንተ ለባሰ ምስኪን ሰው የነገ ተስፈውን መፅውተኸው ጉዞህን ትቀጥላለህ... ፈገግታ ውስጥ ተስፋ አለ! ፈገግታ ውስጥ ፍቅር አለ! ፈገግታ ውስጥ ነገ አለ!
ሌላዉ መልካም ንግግር ነው የሞተን ተስፋ እንኳን እንኳን አፈሩን አራግፎ ሕይወት እንዲዘራ የማድረግ አቅም ያለው ነገር ነው!!
እስቲ ገንዘብ የለኝም ብለን ምናልፈቸውን ሰዎች አይዞን እንበላቸው ለኛ የአዕምሮ ዕረፍት ስናገኝ ለነሱ ደግሞ የመንፈስ ደስታ እንቸራቸዋለን!!!
መልካም ንግግር የነፍስ ምግብ ነው የልብ ፈገግታ ደግሞ የመንፈስ ዕረፍት የሌለንን እያሰብን ያለንን እየከለከልን እንደሆነ ልብ እንበል
ሰናይ ምሽት
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
...
በእስልምና ድሆችን ለመርዳት የሚሰጥ ማንኛውም እርዳታ "ምፅዋት" ወይም "ሰደቃ" ተብሎ ይጠራል፡፡ በእስልምና ህግ መሰረት "ደሀ ስለሆንኩ ሰውን መርዳት አልችልም" ብሎ ነገር በአላህ ፊት እንደ ምክንያት ማቅረብ አይቻልም... ምክንያቱም ሰውን ለመርዳት ሀብታም መሆን አይጠበቅብህም...
...
ይልቁንስ ብዙ አይነት ምፅዋቶች እንዳሉ እስልምና ያዛል... ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ፈገግታ ነው፡፡ አየህ መንገድ ላይ ነገ ስለምትበላው ቁራሽ ዳቦ እያሰብክ ስታዘግም "መሽናት ክልክል ነው" የሚል ፅሁፍ ከተፃፈበት ግንብ ስር ከአንተ የባሰ ምስኪን ተኮራምቶ ተኝቶ ታገኘዋለህ...
...
ታዲያ በእስልምና ህግ መሠረት ደሀ ነኝና ወይም ደግሞ በኪሴ ሰባራ ሳንቲም የለም ብለህ ሰውዬውን እያየህ ከንፈርህን እየመጠጥክ አታልፍም፡፡ ይልቁንስ አላህ በተፈጥሮ የሰጠህን ፈገግታ ለሰውዬው ትለግሰዋለህ፡፡
...
በቃ ይሄው ነው!!! ከጥርሶችህ ፍልቃቂ ውስጥ በሚወጣ ፈገግታ ካንተ ለባሰ ምስኪን ሰው የነገ ተስፈውን መፅውተኸው ጉዞህን ትቀጥላለህ... ፈገግታ ውስጥ ተስፋ አለ! ፈገግታ ውስጥ ፍቅር አለ! ፈገግታ ውስጥ ነገ አለ!
ሌላዉ መልካም ንግግር ነው የሞተን ተስፋ እንኳን እንኳን አፈሩን አራግፎ ሕይወት እንዲዘራ የማድረግ አቅም ያለው ነገር ነው!!
እስቲ ገንዘብ የለኝም ብለን ምናልፈቸውን ሰዎች አይዞን እንበላቸው ለኛ የአዕምሮ ዕረፍት ስናገኝ ለነሱ ደግሞ የመንፈስ ደስታ እንቸራቸዋለን!!!
መልካም ንግግር የነፍስ ምግብ ነው የልብ ፈገግታ ደግሞ የመንፈስ ዕረፍት የሌለንን እያሰብን ያለንን እየከለከልን እንደሆነ ልብ እንበል
ሰናይ ምሽት
• ◉ Join us share◉●••
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
➫
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
"...ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው ... ሰው ( ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው።
...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ) ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ... ነው :: - _ በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። _ ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው :: መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ። እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ና የምንኮራበት?...."
አለማየሁ ገላጋይ
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
➫
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
"...ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው ... ሰው ( ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው።
...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ) ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ... ነው :: - _ በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። _ ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው :: መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ። እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ና የምንኮራበት?...."
አለማየሁ ገላጋይ
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
➫
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
(ኤፍሬም ስዩም)
:- እውነት ወደ ኋላ
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም ' ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
#ኤፍሬም ስዩም
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
:- እውነት ወደ ኋላ
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም ' ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
#ኤፍሬም ስዩም
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
"ውበትን የምታገኙት የማይታየውን ስታዩ ነው፤ በግልፅ ያልሆነውን ስትረዱ ነው፤ ድምፅ የሌለውን ንግግር ስትስሙ ነው፡፡ ውበት፣ በውስጣችሁ ተጀምሮ ከሥጋዊ ፍላጐቶቻችሁ ባሻገር የሚያበቃ ድንቅ የሀዘንና ደስታ ውህድ ነው፡፡ ልቦና ውስጥ የሚገኝ ብርሃን ነው።"
ካህሊል ጂብራን
Join:
https://t.me/write_event
ካህሊል ጂብራን
Join:
https://t.me/write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
"ዝግመተ ለውጥ"
" እንጋባ" ብሎ ጠየቃት፥ አሳምነው።
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡ ተስማሙ።
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡ ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡፡ ካላት ታቀርባለች- ይበላሉ፡፡ አውግተው ይለያያሉ፡፡ የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ጸሃይ መጣ፡፡ እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ።
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቆ ሄደ፡፡
አስማሩ እሱንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!"አወለቀው።
አስማሩ አጥባ አኖረችው።ካፖርቱን ጥሎ ሄደ፥ አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ጸሃይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡ አስማሩ " ምነው?" አለችው። " በጠራራ ጸሃይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡ " ምች ይሆናል" አለቺው፡፡
የምች መድሃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም፡፡ ጥሎት ሄደ።
አስማሩ አጥባ አኖረችው።
ትንሽ ቆይቶ፥ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡ "ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው።" አላት። አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ላይ መጣ፡ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሽዋ ላይ ደርባው ደረሰ። ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀሎት ተገኘ።
ጠጋ አለችለት፡፡
(ከዓለማየሁ ገላጋይ ኩርቢት ገጽ 11)
join
https://t.me/write_event
" እንጋባ" ብሎ ጠየቃት፥ አሳምነው።
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡ ተስማሙ።
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡ ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡፡ ካላት ታቀርባለች- ይበላሉ፡፡ አውግተው ይለያያሉ፡፡ የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ጸሃይ መጣ፡፡ እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ።
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቆ ሄደ፡፡
አስማሩ እሱንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!"አወለቀው።
አስማሩ አጥባ አኖረችው።ካፖርቱን ጥሎ ሄደ፥ አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ጸሃይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡ አስማሩ " ምነው?" አለችው። " በጠራራ ጸሃይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡ " ምች ይሆናል" አለቺው፡፡
የምች መድሃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም፡፡ ጥሎት ሄደ።
አስማሩ አጥባ አኖረችው።
ትንሽ ቆይቶ፥ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡ "ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው።" አላት። አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ላይ መጣ፡ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሽዋ ላይ ደርባው ደረሰ። ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀሎት ተገኘ።
ጠጋ አለችለት፡፡
(ከዓለማየሁ ገላጋይ ኩርቢት ገጽ 11)
join
https://t.me/write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
ለክቡር ዘበኛ ገንዘብ ቤት አንደኛ መምሪያ ሬድዮ ጣብያ አገልግሎት
ጉዳዩ:- ስለ ሰራተኛ መቀጠር
አቶ ጥላሁን ገሰሰ የተባሉ ግለሰብ ከ መጋቢት 25 ቀን 1949 ዓ.ም ጀምሮ በወር 40 ብር ደመወዝ ተቀጥረዋልና ከዚህ ቀን አንስቶ ስማቸው ከ አንደኛ መምሪያ ደመወዝ መክፈያ መዝገብ ላይ ተሞልቶ ሰቀርብልዎ በየወሩ ወጪ እየሆነ እንዲከፈላቸው ይሁን ::
ግንቦት 13 ቀን 1949 ዓ.ም
********
ጥሬ ቆሎ
ለክቡር ዘበኛ ገንዘብ ቤት አንደኛ መምሪያ ሬድዮ ጣብያ አገልግሎት
ጉዳዩ:-የደመውዝ ቅጣትን ይመለከታል
አቶ ጥላሁን ገሰሰ የተባለው የክፍሉ ሰራተኛ ጥሬ ቆሎ አምጥቶ የሙዚቃ ስራ በሚሰራበት ቀን እየጎረመደና እያስጎረመደ ለሠራተኞችም እያደለ ሥራ በማስፈታት ከአንድ ወር ደመወዙ ላይ 3 ብር እንዲቆረጥበት ይሁን።
ሐምሌ 9 ቀን 1949 ዓ.ም
* ታሪክን የኃሌት
*
┄┄┉✽» ❀🌼❀ »✽┉┄
💜 ጦብያ መፅሔት 💜
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
┄┄┉✽» ❀🌼❀ »✽┉┄
ጉዳዩ:- ስለ ሰራተኛ መቀጠር
አቶ ጥላሁን ገሰሰ የተባሉ ግለሰብ ከ መጋቢት 25 ቀን 1949 ዓ.ም ጀምሮ በወር 40 ብር ደመወዝ ተቀጥረዋልና ከዚህ ቀን አንስቶ ስማቸው ከ አንደኛ መምሪያ ደመወዝ መክፈያ መዝገብ ላይ ተሞልቶ ሰቀርብልዎ በየወሩ ወጪ እየሆነ እንዲከፈላቸው ይሁን ::
ግንቦት 13 ቀን 1949 ዓ.ም
********
ጥሬ ቆሎ
ለክቡር ዘበኛ ገንዘብ ቤት አንደኛ መምሪያ ሬድዮ ጣብያ አገልግሎት
ጉዳዩ:-የደመውዝ ቅጣትን ይመለከታል
አቶ ጥላሁን ገሰሰ የተባለው የክፍሉ ሰራተኛ ጥሬ ቆሎ አምጥቶ የሙዚቃ ስራ በሚሰራበት ቀን እየጎረመደና እያስጎረመደ ለሠራተኞችም እያደለ ሥራ በማስፈታት ከአንድ ወር ደመወዙ ላይ 3 ብር እንዲቆረጥበት ይሁን።
ሐምሌ 9 ቀን 1949 ዓ.ም
* ታሪክን የኃሌት
*
┄┄┉✽» ❀🌼❀ »✽┉┄
💜 ጦብያ መፅሔት 💜
━━━━━✦🌺✦━━━━━
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
♻〰〰🀄️〰〰♻
🕊 ቸር ያሰማን 🕊
◌◉◎◦◈◦◎◉◌
◈◈Join us n share◈◈
◌◉◎ ⬇⬇ ◎◉◌
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
➠ @Write_Event
┄┄┉✽» ❀🌼❀ »✽┉┄