ቃላዊ
346 subscribers
38 photos
5 videos
1 file
121 links
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።

ግጥም ለመላክ
@Melikitegna_bot
Download Telegram
"ከተለያየን ምን አደርጋለሁ እችለዋለው
አብረን ባለን ጊዜ ብዙ አሳልፈን
አይቆጨኝም እኔ እሱ ይበቃኛል"

"አቅም አለኝ ብሎ የሰው ልጅ ቢሰፍርም
ታሰበ አልታሰበ ከልኩ አያልፍም"

"የካብኩት ተናደ ባለማወቅ ስገነባው ፈርሶ
ባፀዳው ቆሸሸ እንደገና የፀዳው ደፍርሶ"

"በሚያስቀና ፍቅር ብዙ አመት ቆየን
ደግ ቀን አዋዶ ክፋ ቀን ለየን"

"ሰው ወዶ ሰው እንደመለየት ክፋ ነገር የለም
ልሸኝሽ የመጨረሻዬ በይ ይሁን ግድየለም"

"ዳገት ቁልቁለቱን ተመፀንኩት
አድርሰኝ ከልጄ እናት እያልኩት
የልቤም ባይሞላ ባላገኝሽ
እመጣለሁ በሳቤ ላጫውትሽ"

"ፍቅር ቸር ማድረጉ በኛ ታይቶ ታምኖ ተከበረ
ሰውን የሚያሳሳው ከነፍስ ወዲያ ሌላ ምን ነበረ"

-ማዲንጎ አፈወርቅ💛
ነፍስ ይማር...
ከኃይማኖትህ ፍሬ ያፈራህ ከሆንክ ፍሬህ ያስታውቃል። ማለዳ ተነስተህ ስለ እከሌ እንዲህ እላለሁ ብለህ አታቅድም። አንተን ፍጹም አድርገህ አትፈርድም። ጎጥ አትይዝም።

ሙስሊሙ፤
"ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" የሚለውን ክቡር ቃል እንዴት ተረዳኸው? እምነት ውስጥ ሆነህ ይህን ቃል በየቀኑ ስታስታውስ ለምን እንደምትለው ጠይቀህ ታውቃለህ?
ከብዙ ሙስሊም ጎራዎች አንዱ ላይ ሆነህ አትዳኝ። ልክነት ከላይ ነው። ፈቃዱን ላገኙ የእምነት ባለጸጎች የሚሰጥ ሽልማት።

ክርስቲያኑ፤
"እኔን እምትወዱ ከሆነ እኔን ተከተሉ..." የሚለው ቃል ጎሳ አለው እንዴ? "በስምህ አጋንንት አወጣን ስትሉኝ አላውቃችሁም" የሚለው ሀረግ ምን ሊነግርህ እንደሆነ አስበኸዋል?
ከብዙ የክርስትና ጎራዎች አንዱ ላይ ሆነህ አትዳኝ። ልክነት ከላይ ነው። ፈቃዱን ላገኙ የእምነት ባለጸጎች የሚሰጥ ሽልማት።

ኤቲስቱ(አምላክ የለም ባዩ)
ከታላላቅ ነቢያትህ አንዱ ሄዲጋር ነው። ''ኤግዚስታንሺያሊዝም" የተሰኘው ፍልስፍና ከጎመራመት የቀደመው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ቁጥራችሁ ጨምሯል። ቅዱስ ቃልህ ሳይንስ ወይም ዲያሌክቲክስ ነው። ታዲያ ጎጠኝነትን እንዴት አጠናኸው? ከፍልስፍናህ ታረቅ። ያላስተዋልከው እውነት አለ።

ብሔርተኛው፤
ያንተ ልማድ ልዩ ክብርህ እንደሆነው፤ ሌላውም ክብሩ የሆነ ልማድ አለው። እኔ በላጭ ነኝ ለማለት አእምሯዊ የሆነ የልማዱ ሚዛን በዓለም ታሪክ አልታየም። አይታይም።

ከስሜት ፖለቲካ ካልቀዳኸው በቀር ልማዱ ውስጥ ሳይንሳዊነት የለም። እያንዳንዱ የጎሳ ልማድ ግን በራሱ የጎሳ አባላቱን የሚያኖር ምልዓት አለው። ነፃነቱን ማክበርና መቀበል ስትችል አእምሮህ መስራት ጀምሯል ማለት ነው።
ፈላስፋ #መሐመድ_አሊ (ቡርሃን አዲስ)

@write_event
(ማለፌን 'ሚጠብቅ ፥
ትል ይናፍቀኛል
መውደቄ 'ሚያከስመው፥
ጥላ ያሳዝነኛል።)


ከመንደሪን... መንደሪን

@write_event
እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
💚💛
Join us

@write_event
ለሰው ዴንታ አይኑርህ አይባልም፡፡
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ስህተት ነው፡፡ የሰው ዋጋው በሰው ተለክቶ ነው፡፡ ማንም ሰው ለራሱ የመጠነውን ያህል ይኖራል፡፡ የልማድና ወግ መልክም ቀርጾ የሚኖር ስብስብ እንዲሁ ራሱን ያከብርበታል፡፡ ስለዚህ ለማንም ግዴለኝም እስከመሰለኝ በመሰለኝ እዋኛለሁ ብሎ መለቀቅ ከደመነብሰኝነት ማግስት የሚመጣ እክል እንዳይሆን ያስፈራል፡፡ የሰውነት ትርጉም የሚፈነጥቀው ከሰዎች ስብስብ ውስጥ ነው፡፡ ያደገንበት የኖርንበትና የምንኖርበት ከባቢ ሰውነትን የሚለካበትና የሚቀበልበት ዘየ አለው፡፡ የሚኖርበትና እንደማህበረሰብ የሚገለፅበት ብይን ነውና እሱን ካከበረ መጠይቅ መነሳት ለጥበብ መነሻ ነው፡፡

@write_event
"የኔልሰን ማንዴላ ..

☞ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው ። ስሙም ፒተር ይባላል ።

አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት
ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ማንዴላ በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ ። ዘረኛው ፒተርም "አቶ ማንዴላ! አሳማና ወፍ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" አላቸው ፣
ብልሁ ማንዴላም " አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ
እሄዳለሁ" ብሏቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ ። በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል።

አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ ....
►"ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው ቦርሳ ብር በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ ጥበብ ቢኖር በቅድሚያ የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ ማንዴላን ጠየቀው ፣
►ማንዴላም "ገንዘቡን አወስደዋለሁ" ብሎ መለሰለት ።
►ፕሮፌሰሩም በግልምጫ " አንተ ሞኝ ነህ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ አወስድ ነበር" አለው፣
►ማንዴላ ፈገግ እያለ" ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው ።

በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ 'ደደብ' ብሎ ይፅፋል ። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ ደደብ የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ ፣ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ " ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ፃፍልኝ"
"በማንም ላለመበለጥና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ለማትረፍ ማስላት እያደረ ሰብዓዊ ፍቅርን ሊቀንስና ፈፅሞም ሊያጠፋ ይችላል። ይህ ባህር ስር ከሰደደ የስራ ሰዓትና የሰዎችን ሁኔታ ሳይለይ ቀ
በማንኛውም ጊዜ ከውስጥ ብቅ ብሎ ሊያፈጥ ይችላል። አንዳንዴም ይሉኝታና ምክንያታዊነትን ደምስሶ ሰዎችን ለጥቅም ብቻ የቆሙ አራዊት ያደርጋቸዋል። የሰው ፍቅር በፍቅረ ንዋይ ሲተካ ለማንም ለምንም ደንታ ያሳጣል።....


ያሳዝናል! ነጮቹን እንዲህ የሚያንጠባርራቸውና በበላይነት ስሜት የሚያስጋልባቸው የእኛ መጠጊያ ማጣት ነው። ሀገራችን መኩሪያ ና መመኪያ ልትሆነን አልቻለችም። በገዛ ሀገራችን ተዋርደንና ስራ አጥተን ከመኖር በስደት መኖርን መርጠን ነበር። ተሰድደን ስንኖር ደግሞ ፈረንጆቹ ይንቁናል። ...
ስለ እኛ ጥሩ ነገር መስማት አይፈልጉም። ምንጊዜም የሚያመሳስሉን ከችግር ከጦርነትና ከጉስቁልና ጋር ነው። ለዚህ አመለካከታቸው ደሞ እኛ ረድተናቸዋል። እርስ በእርሳችን እየተጣላን ሸሽተን እነርሱ ጉያ ስር እንሸጓጣለን፤ የምንዋጋበትን መሣሪያ እንዲሰጡን እንለምናቸዋለን ፤ ሳናጣ ያጣን ሆነን የልመና እጃችንን እንዘረጋላቸዋለን።

መፅሐፍ - የቅናት ዛር
ደራሲ - ሲሳይ ንጉሡ



join
@write_event
ቃላዊ pinned a photo
ቃላዊ pinned «ሙላ ናስሩዲን አንዲትን ሴት እያማከረ ነው .. " ባለትዳር ነሽ ?" አዎ " " ስንት ልጆች አሉሽ ?" " 12 " አስራ ሁለት ! ምን መሆንሽ ነው ? ይሄን ሁሉ ልጅ መወለድ ምን የሚሉት ጉድ ነው .... ያውም በዚህ ዘመን " " እንዴ ተው እንጂ እንደዚህ አትበል .... ባሌን እኮ በጣም ነው የምወደው .." አለች ሴትየዋ። " አይይ በዛ ... እንዴ እኔም እኮ ሲጋራዬን እወደዋለሁ ... ቢሆንም…»