በመንገዴ
743 subscribers
1.49K photos
228 videos
8 files
137 links
My own brain is to me the most unaccountable of machinery,always buzzing,humming,soaring,roaring,diving and then buried in mud.🥀
For any ideas or a friend
@chesed_29
Download Telegram
Forwarded from Sost Kilo
ች ግ ራ ች ን ፡ ም ን ፡ ነ በ ር ?

[ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ]

ሌላ ያልነገርኩሽ ፥ የልደትሽ ቀን አበባ ገዝቼ ነበር ። አዎ ! እኔ ። የሚገርምሽ ባገሩ እንደጠፋ ሁሉ የትናየት ሄጄ መሰለሽ ? መጨረሻ ላይ ወሰን ምናምን እሚሉት ሰፈር ትንሽዬ ኪዮስክ ውስጥ ትልቅ መቀስ የያዘች ሻጭ አየሁ ፤ ፈንታቸው መርገፍ የሆኑ ቅጠሎችን እየከረከመች።

እንዲሁ ልጅ ሳለሁ ፥ ከትምህርት መልስ ሙሽራ የሚሉትን አበባ ከሰው አፀድ ቀጥፌ ወደቤቴ እሮጥልሻለሁ ። ቤት ልደርስ 'ከባቢ እጄ ከአበባው ተሻሽቶ ኖሮ ፥ ወየበ ። ከቆረጡት ኋላ ቶሎ የሚሞት አይነት ዘር ሆኖም ይሆናል ። ብቻ እጄ ላይ ከስሞ ፥ ነደደኝ ።

የቀጠፍኩት እንዲያ እንዳማረበት ለ'ናቴ ልሰጣት ነበር ። ያም ሆኖ አልተውኩትም ። ከስራ መምጫዋን ጠብቄ (አስራ ሁለት ሰዓት እንደምንም ሞልቶልኝ) ሰጠኋት ። የኔ ንጉሥ ብላ አቀፈቺኝ ፥ ከመቀበል ያለፈ ቁብ ሳትሰጠው ። ጭራሽ ወርውራው መክሰስ መብላቴን እየጠየቀች ወደቤት ይዛኝ ገባች ። እጄን ይዛኝ ስትዘልቅ ፊቴ ወደወደቀው አባባ እንደዞረ ነበር ።

እናልሽ ቤሎንዥ...

ኪዮስኩ ውስጥ ያለችው ልጅ የሚቀባውን ነገር ቀብታ የሆነ የሚነፋ ነገር'ም ነፍታበት አጋጊጣ ምናምን ሰጠችኝ ። እንዴት እንዳማረበት ። ገዝቻት ስወጣ አመስግኜ ፥ መልካም በዓል ! አልኹ ። የምን በዓል ደሞ ? በሚል ግርምታ ታየሁ ፥ ሃሃ።

እዝነ ገመዴን ከጆሮዬ ስላልተነሳ ዘፈን እንደምሰማ ሁሉ ምንም ሳልል እግሬን አዙሬ መንገዴን ጀመርኩ ። ለካ ሌላ ሰው የአንቺን ልደት አይቀድስም ። የለም? ፥ ለካ የነሱ ካለንደር በንግስሽ ቀን አይዘጋም ።

ከናቴ ለጥቆ አበባ ልሰጠው የነበረው ላንቺ ነበር ። የገዛሁት አበባ በትራንስፖርት ግፍፊ እንዳይጎዳ ወክ ማድረግን መረጥኩ ። አበባውን እንደያዝኩ ይዤ በቀትር ስንከላወስ አላፊ መንገደኛ እያየኝ በልቡ የሆነ ነገር ይላል ። መቼም አበሻ "ምኗ እድለኛ ነች ፥ አበባ የሚሰጣት " ማለት አይቀናውም ። ...አ...ዬ ባህላችን.. ገለመሌ ...እያሉ ይሆናል ።

ሰባት ሰዓት ላይ የሜክሲኮው ቶታል (ቦንዡ ካፌ) ደረስኩ ። ተረከዜን ከማቃጠል ውጪ በጉዞው ብዙ አልተሰማኝም ። ትዝ ይልሽ ከሆነ አራቴ ስደውልና በአምስተኛው ጥሪውን ስትጠረቅሚው ፥ እዛ ቁጭ ብዬ ነው ። ከተቀመጥኩ ሰዓት ሊደፍን ምናምን ደቂቃ ሲቀረኝ ያ...!...ሜሴጅ ገባ።

- Sorry, Je ne peux pas venir.

መምጣት አልቻልኩም ። እንደው እንደቀላል ፤ የአንድ ግድንግድ መፅሀፍን ግፍ በአንድ ነጠላ መስመር ። አለ አደል ፥ ሲቻኮሉ ከሰው ተገጫጭተው ይቅርታ እንደመጠየቅ አይነት ያለ ።

እና አበባው ሳይደርስሽ ከእጄ ቀረ ። እናቴም ያኔ አበባውን ስሰጣት እንዴት ሆኜ እንዳመጣሁት አልጠየቀችም ። ማለት ፥ ስላልጠየቀች ለመቅጠፍ የከፈለኩትን መስዋዕትነት አልተረዳችም ። በልጅ ሩሄ አበባ ያህል ነገር ከሰው አጥር ላይ አርጄላት ፥ በቅጡ እንኳ አልባረከችኝም ። ከንቱ ድካም ነበር ። አበርክቶቴ መገፋት የጀመረው ከያኔ አንስቶ ነው ፤ እርኩስ እንደሚሠዋው በግ ፥ እሳት ከራማ ወርዶ እንደማይበላው ...።

የዛን ቀን እራሮቴ ተፈቅፍቆ ከልቤ አልወድቅ አለኝ ። የልደትሽ ቀን ባለፈ በሆነኛው ቀን ስልኬን አውጥቼ መርዕዩ ላይ Qu'est-ce qui ne va pas entre nous , bel ange? ብዬ ፃፍኩ ። ችግራችን ግን ምን ነበር ...?

ችግራችን ፥ የፍዮሪ በእጄ ላይ መሞት ሳይሆን ፥ ተቀባይ ማጣት ነው ። አንዳችኝ ጉም ሰንጠቀን አንዳችንን ከህዋ ስናስስ ሌላችን ጣርማበር ጓሣ ውስጥ ለሽ ብለን ነበር ። በተራሽ ደሞ አንዳችን ባነን ሌላችንን ስናስስ የሂማልያ ክምር ጋርዶን ለአይን እንሰወራለን ።

መልሱን እያወቅሁ ያረቀቅሁትን ጥያቄ ላንቺ መላክ አልፈለኩም ። ከደመና በታች እንደቀረ ፀሎት ፥ ካፍ እንዳልወጣ ቃል ፥ እንዳልተኖረ ምኞት ፥ ሲባኑ እንደረሱት ህልም ፥ ደርሰው እንዳልሰበኩት ወንጌል ...

በድህሪት መደለዣ የፃፍኩትን የቃላት ድርድር አንድ በአንድ ከስልኬ መርዕይ ሰረዝኩ ። ሰሌዳው እስኪራቆት ፤ የመተየቢያዋ ከርሰር ግራዋን ሄዳ ውልብ ውልብ እስክትል። ፥ እ ...ን...ዲ..ሁ •••|

------------------------------------------------------------
ያ ል ተ ላ ኩ ፡ አ ም ስ ት ፡ ቴ ክ ስ ቶ ች [ M e s s a g e -1 ]
1
Forwarded from The Sun & Her Flowers
What is daydreaming?
(Trigger Warning ⚠️- Mention of mental illness and trauma)

-Daydreaming is a psychological phenomena where the mind makes up events or ideas from the past, present, future or complete imagination and pretends like it is experiencing it. Every human being daydreams to some extent. When you imagine yourself doing the tasks on your to-do list, when you wish you did something while replaying it in your head...all these are forms of daydreaming. They're a part of normal thinking. Some might even say they make us creative and help us think outside the box. But how far away from the box do you have to be for it to be an inconvenience, or even worse, an addiction?

-When an individual experiences things like trauma (especially from childhood), mental illness, stress, or something that the brain finds too much to handle, it escapes from reality by creating non-existent scenes that feel good and soothing. This helps the mind feel calmer and happier, but in the mean time the person gets heavily distracted from important or even vital things like school, work, taking care of oneself, etc.

-Boredom can also trigger daydreams. You ever noticed how your brain wanders when you are sitting in class and you feel bored? You'd rather think about what you will do later that afternoon or maybe even involve yourself in a scene that you watched on a movie.

*Summing it up, it's a mental activity that makes you deal with anything but reality. In severe situations, it can consume time, energy and interfere with day to day activities and social life.

@thesunandherflowerss
Forwarded from Scribbles
የረገሙትን ጥጥ፣
እኔው እየፈተልኩ
ቀዳዳ አለበስኩ፣
እኔ እያፈሰስኩ
እኔ ጦም አዳሪ፣
እነሱን አስፈሰኩ
ለኔ ሳልሆን እኔ
አቅሜን ጨረስኩት
እራሴን ናፈቅኩት...
ይነጋልኝ ብየ
እራሴን ለማሞቅ
እራሴን ለማንሳት
በፈጠርኩት እሳት
በቀዱልኝ ነዳጅ
እራሴው ተቃጠልኩ

ig: @dagmawit_aemero

@resonantscribbles
Forwarded from Our Side of the Story (Debbie)
I really don’t find comfort in interacting with humans on a daily basis.

Interaction means communication and communication exposes you to the human mind which is a very scary place.
In rare blessed situations you get the chance of experiencing beautiful minds and actually learn from them but in some?
Holding yourself back from judging how people think becomes an exhausting job.

Half of my days are filled with prayers of asking God how he tolerates people with absurd perceptions or am I just too self righteous?
Where do you go to?
Why do you go?
"Did you know that heart break triggers the same area of the brain as physical pain?"
Forwarded from Sost Kilo
"እና አበባው ሳይደርስሽ ከእጄ ቀረ ። እናቴም ያኔ አበባውን ስሰጣት እንዴት ሆኜ እንዳመጣሁት አልጠየቀችም ። ማለት ፥ ስላልጠየቀች ለመቅጠፍ የከፈለኩትን መስዋዕትነት አልተረዳችም ። በልጅ ሩሄ አበባ ያህል ነገር ከሰው አጥር ላይ አርጄላት ፥ በቅጡ እንኳ አልባረከችኝም ። ከንቱ ድካም ነበር ። አበርክቶቴ መገፋት የጀመረው ከያኔ አንስቶ ነው ፤ እርኩስ እንደሚሠዋው በግ ፥ እሳት ከራማ ወርዶ እንደማይበላው ...።"
Forwarded from Hakim
ሁለት ውብ ታሪኮች ከአማኑኤል ሆስፒታል
==========================
አማኑኤል ሆስፒታል የሰው ድክመት፣ ውድቀት፣ ህመም ብቻ የሚሰማበት የሚመስላቸው ሰዎች አይጠፉም፡፡ ነገር ግን በየቀኑ የመነሳት፣ የጥንካሬ፣የፅናትና የፍቅር ውብ ታሪኮች ይስተናገዳሉ፡፡ ሁለቱ በዚህ ሳምንት ከገጠመኝ እነሆ፦

1) አማኑኤል የሴቶች ዋርድ የሀኪሞች ክፍል ተቀምጬ ካርድ ላይ እየፃፍኩ ነው፡፡ በሩ ገርበብ ብሏል፡፡ አንድ ታካሚ ከአልጋዋ ከነጋ አልተነሳችም፡፡ የደበራት ትመስላለች፡፡ ገርበብ ባለው በር ትታየኛለች፡፡ አንድ ወጣት ሴት ፍራፍሬ በፌስታል ይዛ ልትጠይቃት ትገባለች። አይኗ ብርት ብሎ ከአልጋዋ ወዲያው ተነሳች። ተቃቀፉ፡፡ በቀናት ውስጥ ያላየንባት ደስታ ውስጥ ሆና መጫወት ጀመሩ፡፡ ጠያቂዎን አውቃታለሁ፡፡ ከሳምንት በፊት እዚሁ ሆስፒታል እዚሁ ክፍል ተኝታ ነበር፡፡ ጓደኛዋን ልትጠይቅ መምጣቷ ነው፡፡ ተኝታ የምትታከመው ድንገት አቀረቀረች፡፡ አይኗን ሳታነሳ ጓደኛዋን "ግን የምንድን ይመስልሻል?" ብላ ጠየቀቻት፡፡ ጓደኛዋ እቅፍ አደረገቻት "እሱ የፈጣሪ ስራ ነው፡፡ እኛ ግን መድሀኒታችንን እንወስዳለን አለቻት፡፡"...

አንድ የኩላሊት ጠጠር ቀዶጥገና ሀኪም "ሀኪሙ ጠጠሩን ያወጣል፤ የሚያድነው ግን አምላክ ነው፡፡" ያለው ትውስ አለኝ፡፡

2) ታካሚ ወንድሙን ይዞ ኦፒዲ ይገባል፡፡ መልካቸው በጣም ይለያያል፡፡ "እባካችሁ ተኝቶ ይታከም?" አለን፡፡ "ያልተለመደ ፀባይ ሲታይበት አከራዮቻችን ቤት እንድንለቅ ጠየቁን፡፡ ለትንሽ ጊዜ ቢተኛ?" አለን፡፡ "ቤተሰቦቻችሁ የት ናቸው?" ብዬ ጠየቅኩት፡፡ መልሱ ያልጠበቅኩት ነበር፡፡ "ከተለያየ ቤተሰብ ነው የመጣነው ግን ወንድሜ ነው፡፡ በማደጎ አብረን ነው ያደግነው፡፡ እሱ ጎበዝ ተማሪ ነበር፡፡ እኔ ዱርዬ ነበርኩኝ፡፡ ማደጎውን ጥዬ ወጣሁ፡፡ ከዛ ጥሩ ያልሆነ ህይወት ነው ያሳለፍኩት፡፡ የተለያዩ ቦታዎች ዞሬ ስመለስ እሱ ኮሌጅ ተመርቋል ግን አእምሮውን አሞታል፡፡ ማንም አጠገቡ የለም፡፡ ስንገናኝ እኔ ያለፈው ህይወቴን ትቼ በእምንቴ ጠንክሬ ነበር፡፡ አሳከምኩትና ደህና ሆነ፡፡ አብረን መኖር ጀመርን፡፡ አሁን አመታት ሆኖናል፡፡ አንዳንዴ ያስቸግረኛል፡፡ ነገር ግን እኔ ራሴን ብዙ እንደተደረገለት ሰው ነው የምቆጥረው፡፡ ስለዚህ እሱን ማገዝ መቻሌን እንደ እድል ነው የማየው፡፡"....

በየሚዲያው በሚታየውና በሚሰማው እጅጉን ኮስምኖ የነበረው በሰብአዊነት ላይ የነበረኝ ግምት ሲለመልም ተሰማኝ።

መልካም ጊዜ!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው ፤ የአእምሮ ህክምና ሀኪም

@HakimEthio
Another amharic work🖤
Forwarded from αll օբ մs•••
ህፃንነቴ በናፍቆት እጣን አዕምሮዬን ሲስበው

ያ *ውሻ በልቶኝ በልቶኝ በልቶኝ በልቶኝ...* ብዬ ለእኩያ ወዳጆቼ በኩራት የተረኩላቸው ጀብዱ ትዝ አለኝ...
በምክንያት ነው ትዝ ያለኝ.. የሰው ውሻ ለምጄ

ከህፃንነቴ አልተሻልኩም ... እያለቀስኩ ወደ ቤቴ እሮጣለው
ወዳጄን አገኘዋለው... እኩያዬ ባይሆንም ጓደኛዬ ነው .... ፈጣሪ ነኝ ብሎኛል.... ከዛም እናወራለን ....ይጠይቀኛል ....መልስለታለው

*ምን ሆነክ ነው ምታለቅሰው?*


*ውሻ በልቶኝ በልቶኝ በልቶኝ.....*


.
@snasb_hasab
Because it warmed my heart.🖤
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
This found me and it felt like the universe was really talking to me. I wanted it to find you too. Healing is this. This is true healing. No filters or beautiful words to inorder to beautify it. So if this does find you,just know that it's not just you.🖤
🖤