ወግ ብቻ
19.2K subscribers
508 photos
11 videos
20 files
49 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch
@zefenbicha

Creator @leul_mekonnen1
Download Telegram
1892 ላይ ስታንፎርድ ዩንቨርስቲ ይማር የነበረ የ18 አመት ወጣት ለትምህረቱ የሚከፍለው ገንዘብ ይቸገራል። ገንዘብ የሚጠይቀው ሰውም አልነበረውም። በዚህ ሃሳብ እያለ ከጓደኛውጋ ይማከራል ... 'ለምን የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅተን ገንዘብ አንሰበስብም?'

ሁለቱ ወጣቶች ወደ አንድ Ignacy J.Paderewski የሚባል ታዋቂ ፒያኒስትጋ ይሄዱና ማናጀሩን ያገኛሉ። ማናጀሩም $2000 ክፈሉና እንደፈቀዳችሁ አላቸው። ወጣቶቹ ሙዚቃቸውን እያጠኑ እና እየተለማመዱ ለሙዚቃ ፕሮግራማቸው ይዘጋጁ ጀመረ

ያ የተባለው ሙዚቃቸውን የሚያቀርቡበት ቀን ደረሰ። ብዙ ትኬት ስላልተሸጠ ባጠቃላይ ያገኙት ገቢ 1600 ዶላር ብቻ ሆነ። ያቺን ያገኟትን ገንዘብ ይዘው ወደ Paderewski ይሄዱና እንዳሰብነው አልሆነልንም። ስለዚህ የምንመልስልህ ያገኘነውን ሙሉ 1600 እና ወደፊት ልታወጣው የምትችለው የአራትመቶ ዶላር ደረቅ ቼክ ነው ይቅርታ አሉት።

ሰውየው ግን ጭራሽ ተቆጥቶ ቼኩን ቀደደ እና ገንዘቡን አልቀበልም አላቸው። ይህ ገንዘብ ለአንዳንድ ወጪ ያወጣችሁትን ይሸፍንላችኋል። የቀረውን ለራሳችሁ ተጠቀሙት አላቸው።

ወጣቶቹ ተደንቀው አመስግነውት ወጡ። ስለተደረገላቸው መልካምነት እጅግ ተደሰቱ።

የማያውቃቸውን ሰዎች ለምን በዚህ መጠን ሊረዳቸው ፈለገ? ከእነሱ ምንንም ሳይጠብቅ ለምን ይሄንን ቸርነት አደረገላቸው? አንዳንዶቻችን "ይህንን ሰው በዚህ በተቸገረው ነገር ብረዳው ለኔ ምን እጠቀማለሁ?" ብለን እናስባለን። አንዳንድ ብሩህ ልብ ያላቸው ደሞ "ይህንን ሰው በዚህ በተቸገረበት ሰአት የአቅሜን ባልረዳው ምን ይሆናል?" ብለው ስለ እዛ ሰው ያስባሉ

ከጊዜያት በኋላ ይህ ፒያኒስት የ ፖላንድ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነ። የተወደደ ገዢ ሆኖ በሚመራበት ዘመኑ የአለም ጦርነት ተጀመረ እና 1.5 ሚሊየን ፖላንዳውያን ተራቡ። እሱም እርዱኝ ብሎ አለማትን መለመን ጀመረ።

ወደ አሜሪካን መልዕክት ላከ። በሰአቱ የአሜሪካ ፕሬዚደንት የነበሩት Herbert Hoover ወዲያው እርዳታ አደረጉለት። በዚህም የፖላንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ተደስቶ ይህንን ሰው በአካል ያለበት ሄጄ አመሰግነዋለሁ ብሎ አሜሪካ መጥቶ እጅ ነሳ። 'ለህዝቤ እና ለእኔ ላደረግህልን በጎነት አመሰግናለሁ' አለ የፖላንዱ ጠቅላይ ሚንስትር።

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ግን 'ለምን ታመሰግነኛለህ?' አለው

'ከብዙ አመታት በፊት ሁለት ተማሪዎችን ለትምህርት የሚከፍሉት ሲቸገሩ በጎ ፈቃድ ያደረግህላቸው ትዝ አለህ? አንዱ ወጣት እኔ ነበርኩ'

By Mastewal Aseffa

@wegoch
@wegoch
@paappii
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (Leul M.)
Exhibition titled, “መልክ”
By Surafel Alemneh

Artawi Gallery
opened for public.

The galley opened  until 20 July 2024 starting from 2 PM - 6 PM bole, around British international school or 250m in from Yod Abyssinia, Kkare Homes, 2nd Floor


@seiloch
መናፍስት አማረኛ አወራ ?
                          በግዕዝ ሙላት

ሰማዬ ጋር የክዋክብት መብራት የአራስ ህፃን አይን መስለው ቡዝዝ ብለው በየፈርጡ ተኮልኩለዋል ። ጨለማው ከሰማዬ ብርሃን ገዝፎ መጠነኛ ንፋስ የግቢውን ዛፎች ያስደንሳቸዋል !ቅጠሎች ደሞ ሰክረዋል መሰል እዬተንገደገዱ ይወድቃሉ (የንፋሱን ውስኪ ገልብጠው)።

እዬለፈለፍኩ ነው? ግን እያወራሁ አይደለም? የተፈጥሮ የድምፅ ፀጥታ ከራሴ ጋር ሊያመካክረኝ ዝግ ስብሰባ ይዟል። ቆይ... ቆይ... ቆይ...ሲጀምር... ለምንድነው? ከራሴ ጋር ምማከረው?... እንደዛ ሲባልስ... ደባል ስዕብና በውስጤ አለ ወይስ የለም  ? ሲጀምርስ ምክክርን ከዚህ ምን አመጣው ? ብሽቅ!(አለ ያነኛው )

አንዳንዴ በቀን ኑሮ ውስጥ ያሉ ትዕይንቶች ለስዕብናችን የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ(political speech ሆነ መሰል ?😏ለምን የድመቱን ድርሻ አይወስዱም ምን አገባኝ? አይጥ!) (አለ ይሄኛው)

ሲጀምርስ ፖለቲካን እዚህ ምን አመጣው? አያችሁ ይሄ ነው ስዕብና ማለት ዝም ብሎ መዘባረቅ። ስዕብና ፀንቶ የሚኖር ሀውልት አይደለም! በሁኔታው ሁሉ ይቀያየራል። ለዛም ይመስለኛል ህፃን ልጅ ልጅ ሳለ ንፁህ ይሆንና የኋለኛው ማንነቱ በአረመኔነት የሚቀዬረው ።
(በሚያዬው ትዕይንት እና ገቢር መጠን...ስል ገና)
" እና እኛ ምን አገባን?' ቅማላም' ቁጭ በል" አለኝ ያነኛው(የትኛው?)

<እኔ>
ሰአቱ ስንት እንደሆነ አላቅም.. እርግጥ ነው መብራት ስለጠፋ (መጀመሪያውንም ስለሌለ)  ብቻ ስልኬም ባትሪው ዘግቷል ።ይመስለኛል ይሄን የተፈጥሮ ፀጥታ  እንዳዳምጥ ያደረገኝ ሰው የፈጠራቸው ነገሮች በቴክኒካል ችግር መደበቃቸውን ነው(ባትሪ መዝጋቱን ማለቴ ነው)።የሚገርመው ግን ተፈጥሮ የምትባለው ሴት ግን (ሁሉንም ከሴት እናገናኜዋለን!) ቴክኒካል ችግር የለባትም! አሁን አሁን የአዬር ብክለት ሚባለው ነገር ትልልቅ ትሪሊዮነሮችን ባለሀብት በገነቡት እንዱስትሪ በሚለቀቀው ጋዝ ተበከለና መልሰው በበከሉት አዬር ያገኙትን ትርፍ መልሰው የአዬር ብክለትን ለማስተካከል ይደክሙበታል።...ቆሻሻ አለ ጋሽነት። (ጋሽነት የሰፈራችን ሰው ነው ልጁ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ልጁ ጋር ያለውን ፍቅር ለመግለፅ የሚጠቀምባት ቃል ናት!ቆሻሻ አለ ጋሽነት( አለ ተኝቶ የነበረው እኔ?)

<ያነኛው እኔ>
በቃ ሰው እንዲህ ነው ዝም ብሎ መባከን መባከን መባከን(አልጨረሰም ገና) ..."አንተ ልጅ ተመለስ ተው" አለ የሆነ ድምፅ ከጨለማው መሃል' እማዬ ድረሽልኝ' ምንድነው የሰማሁት(በአካል የሚታዬው አፌተናገረ)...መናፍስት ?... አይ አይ መናፍስት አማረኛ አይችሉም! ...እና ማነው ያወራው?...ፀጥ አልኩ ሁሉም ነገር ፀጥ አለ ድጋሚ..."ለምን ዝም አልክ" አለ ያ ድምፅ...'ኧረ ደገመው' አልኩና ጆሮዬን የት ጋር ድምፁ እንደመጣ አጣራው ከውስጥህ ነኝ ያለሁት አለኝ የሆነ ድምፅ!.. ግን የሆድ ድምፅ ይመስላል (እ? እንዴት ራሴው አውርቼ ራሴው ፈራሁ አንዳንዴ ከሰውነታችን የሚወጡ ትርጉም የለሽ ድምፆች የሆነ ቅፅፈት ትርጉም ይኖራቸዋል ልክ እንደዚሁ ) በድጋሚ የሚናገረው ድምፅ ተሰማኝ የራሴው ስዕብና ነው ላምን አልቻልኩም "ኧረ ቤስሚያም"አሉ አባ ጎርብጥ

<ወዲህኛው እኔ>
ነግሬቹሃለሁ ሁላችንም በሁኔታዎች የሚቀያዬር ስዕብና ነው ያለን..."መጣሁልህ አንተ ፈሳም" አለኝ ሌላ ድምፅ ከዛፉ ስር "እማዬ ድረሽ መናፍስት አማረኛ አወራ?"....እዬሮጥኩ ወደ ቤቴ....

@geez_mulat

@wegoch
@wegoch
@wegoch
..."አባዬ" (ልጅ)

..."አቤት" (አባት)

..."በግ አስተኝተን፡ አርደን፡ ደሙን አፍሥሰን፡ በጥብስ እና በቅቅል አርገን ስንበላው ነፍሱን በማጥፋታችን ሀጥያት አይሆንብንም?"(ልጅ)

..."ምን ስትል አሰብከው ልጄ? እረ አይሆንብንም።" (አባት)

..."እንዴ አባዬ እየገደልን አደለ እንዴ፡ እንዴት ሀጥያት አይሆንብንም?" (ልጅ)

..."ምን መሰለህ ልጄ... እንዴት ላስረዳህ?... ሞት እኮ በር እንጂ መጨረሻ አይደለም፡ በጉን ስንበላው በኛ ውስጥ መኖሩ ይቀጥላል እንጂ ጨርሶ አይሞትም" (አባት)

..."እረ እረ አባዬ ደሞ እንደዚ አለ እንዴ?" (ልጅ)

...."አዎ! እውነት ስልህ ፥ ያው የበላነው ተስማምቶን ሀይል እና ጉልበት አግኝተን፡ አካላዊ እድገት እያመጣን አይደል የምንኖረው ፡ ያ ታድያ እኮ በኛ ኖረ ማለት ነው ልጄ" (አባት)

..."እሺ እና ጋሽ ጀንበሬ እንደውም ባለፈው በለሊት ወደስራ ሲሄዱ ጅብ የበላቸው ጅብ ሆነው እየኖሩ ነው ማለት ነው አባዬ?" (ልጅ)

..."ወይ ጉድ ዛሬ እንደው ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት...ማነሽ 'አልማዝ ነይ እስኪ ይሄን ልጅ ወደዛ ወስደሽ ገላግይኝ'...አልሞት አልኩህ?" (አባት)

..."ምን አልክ አባዬ?" (ልጅ)

..."ምንም ወዲህ ነው የእራት ሰዓት ደርሷል እናትህን ወስደሽ አብይው እያልኳት ነው....'አንቺ አልማዝ ነይ እኮ ነው ምልሽ'. ..አትሰማኝም እንዴ?" (አባት)

..."እና ንገረኛ አባቴ ጋሽ ጀንበሬ ጅብ ሆነዋል ማለት ነው? የባቢ አባት ጅብ ናቸው ማለት ነው?" (ልጅ)

..."ሆሆ! ደሞ ነገ ት/ት ቤት ሄደህ 'የባቢ አባት ጅብ ሆኑ እንጂ አልሞቱም ብሏል አባዬ' ልትል ነው ሆሆ! ደሞ ከጎረቤቶቼ አቆራርጠኛ! በል በል የለም ያልኩህን እርሳው በቃ እንደውም ሀጥያት ነው ከንግዲህ በግ የሚባል አናርድም።. ..ግልግል እንደውም ተወዷል...ሆ! በገዛ እጄ...ቆይ እዛ ት/ት ቤት ምን ስትማሩ ነው የምትውሉት?" (አባት)

..." እርሳው? አባዬ ደሞ አንዴ ነግረኸኝ እንዴት ነው ምረሳው?...ደሞ ት/ት ቤት ሳይሆን አንተ እኮ ነህ የነገርከኝ በግን ስንበላው እኛን እንደሚሆን...ት/ት ቤት ምን አጠፉ....ህእ!" (ልጅ)

..."ማ? እኔ አልወጣኝም! አይወጣኝምም!. ..ምን ይላል ይሄ...በል ጥፋ ከዚ. ..ድራሽ አባክ ይጥፋና...አትሄድም!".....

By Mikiyas Beshada Kebede

@wegoch
@wegoch
@paappii
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (Leul M.)
#ወደ_ግጥም__ወደ_ነብይ
ፈግታን ስለቸረን መነሱ ___ ስላስጠለለን ዋርካነቱ
ስለ አፅናኝ ጨዋታዎቹ ___ ሕይወት ስለሚያሞቁ ግጥሞቹ
ቅንነቱን ለማቀንቀን ___ አባትነቱን ለማወደስ
ስለ ግጥም _ _ _ ደግሞም ስለ ነብይ
ቅዳሜ እንሰበሰባለን። ፈንድቃ ቤተ ጥበብ [ ፈንድቃ የጥበባትና ባህል ማዕከል:Fendika Art & Cultural Center ]

• ውብ ግጥሞች ልዩ
• ልዩ የሙዚቃ ጨዋታዎች
• ነገረ ነብይ
• የጥበብ ቅማ ቅመም

የምትወዷቸው የምንወዳቸው ሁሉ አሉ። ስለ ግጥም _ ስለነብይ።

ከ8:00 ቀደም ብላችሁ ኑ።
ቡናውም ጨዋታውም ወዳጅ ትውውቁም እንዳይቀርባችሁ።

ቅዳሜ ሀምሌ 6 2016 ዓ.ም 😍🙏🙏🙏😍

@getem
@getem
Notcoin🪙 በአዲስ አሰራር መቷል! ገብታችሁ ስሩበት


https://t.me/notcoin_bot?start=er_36367900
አባት ልጁን ለማግኘት ወደ ክፍሉ ጎራ ይላል፤ ልጁ ግን የለም። እንደለመደው አምሽቶ ሊመጣ እንደሆነ እያሰበ ክፍሉን ለቆ ሊወጣ ሲል የሆነ ነገር አስተዋለ።

አዎ ክፍሉ እንደወትሮው አልተዝረከረከም፤ በሚገባ ተፀድቶ ተስተካክሏል። አልጋውም በስርዓት ተነጥፏል፤ ወለሉ ሸልፉ ምኑ ሁሉ በወግ በወግ ሆኗል።

ግራ በመጋባት ክፍሉን እየቃኘ በመሃል ማጥኛ ጠረጴዛው ላይ ደብዳቤ ያገኛል፤ ከላይ ለ አባዬ ይላል በትልቁ።
ከፍቶ ማንበብ ጀመረ..

“ አባዬ ከትሬሲ ጋ ተያይዘን ጠፍተናል..አውቃለሁ እድሜዋ ከእኔ በ30 እንደሚበልጥ ፤ ቢሆንም እኔ ግን በጣም እወዳታለሁ። ለመጥፋት የወሰንነው እንዳረገዘችና ልጁ የኔ እንደሆነ ስትነግረኝ ነው።
ምንም ገንዘብ ስላልነበረን ከዋሌትህ ልሰርቅ ተገድጃለሁ።

ጥሩ ገንዘብ መስራት የጀመርን ጊዜ፤ የኤች አይ ቪ በሽታዋን ሆስፒታል እየሄድን ክትትል ማድረግ እንጀምራለን። ደሞ ብዙ ልጆችንም የመውለድ እቅድ አለን ፣ ጊዜው ሲደርስ ተሰብስበን መጥተን የምናይህም ይሆናል።

ቆይ ቆይ አባዬ የውሸቴን ነው ተረጋጋ፤ እዚሁ ሰፈር ነው ያለሁት የትም አሌድኩም። የኔ ፍላጎት ከፈተና ውጤቴ በላይ አስፈሪ ነገሮች እንዳሉ ለማስታወስ ነው ፤ ልታየው ከፈለክ ሌላኛው ጠረጴዛ ላይ አለልህ።
ስትረጋጋ ደውልልኝ ”

@wegoch
@wegoch
@paappii
ፀጉር ቆራጩ ደምበኛውን ያዝናናል ብሎ ያሰባቸውን ነገሮች በማጫወት ላይ ነው።
“ያ ይታይሃል?...አስፖልቱ ዳር የተቀመጠው ልጅ..?”
“አዎ”
“ከምታስበው በላይ ጅል ነው”
“እንዴት? ”
“ቆይ ላሳይህ” አለና ፤ወጣ ብሎ ልጁን ጠርቶ ወደ ውስጥ አስገባው።
“ተመልከት እንግዲህ..”

ከኪሱ አንድ የአምስት ብርና አንድ የአስር ብር ኖት አወጥቶ ሁለቱንም መሬት ላይ ጣላቸው ከዛ ልጁን “ ከሁለቱ ትልቁን ብር አንስተህ ሂድ” አለው። ይሄኔ ያ ልጅ አምስቷን ብር ብድግ አርጎ ወደ መጣበት ይመለሳል።
“አየህ ይሄን ደደብ?...በዚ እድሜው አምስት ብርና አስር ብርን መለዬት አይችልም!!”
“በጣም ሚገርም ነው” አለ ፀጉሩን ሊቆረጥ የመጣው ሰውዬ ባዬው ነገር የእውነትም ተገርሞ።

አስተናግዶት ከጨረሰ በኋላ ተሰነባብተው ተለያዩ። ይሁን እንጂ ያ ሰውዬ ቅድም ባየው ነገር ተገርሞ ብቻ ሊቀር ስላልፈለገ ልጁ ወዳለበት ሄዶ ያሳሰበውን ነገር ጠየቀው
“እውነት አንተ..አስር ብር እና መቶብርን መለየት አትችልም?”
“አዪዪ..” አለ ልጁ
“አዪዪ..10 ብሩን ያነሳሁ ቀንማ ጨዋታው ያበቃል”

by Yosef Gezahegn

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሥዕል ለወዳጅ ዘመዶ ስጦታ ማበርከት የምትፈልጉ በ+251984740577 ይደውሉ።


ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!



@seiloch
@seiloch
ብርቅዬ ጎደኞቻችን

———
አብዛኞቻችን ከህይወት ዘመናችን አካል ከሆኑት ውስጥ የት/ቤት ጎደኞቻችን እና ትዝታችዎቻችን በእጅጉ ከምንናፍቃቸው እንዲሁም ወደኋላ ተመልሰን የመኖር ምርጫ ቢሰጠን በድጋሚ ያን ህይወት ለመኖር የምንመኘው እና የምንጎጎለት አንዳንዴም እንደእኔ ያለ የኋላውን ናፋቂ የሆነ ሰው በፈረንጆቹ ፊልም ውስጥ የሚያየውን በእነሱ አፍ  time travel  ወደኛ ስናመጣው ጊዜን ወደፊት እና ወደኋላ መመለሻ machine ለመስራት መመኘቱ አይቀርም ትግበራ ላይ ባንገባም (እውቀታችን ቢገድበንም) እና ስመለስ ወደእኛ አለም  የት/ት ቤት ህይወታችን ወርቃማው አስደሳቹ የህይወት ዘመናችን አካል ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም።የት/ት ቤት ትዝታዎቻችንን ስናነሳ ደሞ የሀይስኩል ህይወታችንን ሳናነሳ ማለፍ የሚታሰብ አይደለም የአብዛኞቻችን አስደሳች ሮማንቲክ አስቂኝ ህይወት ያሳለፍነው እዛ ውስጥ ነው ። ያ  ጊዜ ለብዝዎቻችን መፈንዳት የጀመርንበት (like volcano )ሴት መጥበስ ,መጀንጀን ትምህርቱን ከነጭራሹ መርሳት  ,ቤተሰብ ትልቅ ሰው መስማት ያቆምንበት እንደልባችን የምንሆንበት ከጎደኞቻችን ጋር ጥዋት ወተን ማታ ለማደር ወደቤት የምንገባበት አፍላ እድሜ። በዛ የጡዘት ጊዜ አይደለም ቁምነገረኛ ልጅ መሆን ቀርቶ ጥሩውን ከመጥፎ በቅጡ መለየት የምንቸገርበት እድሜ ነው ።ታዲያ እንዲህ ስል የሁሉንም የት/ት ቤት ህይወት የሚያጠቃልል አይደለም ሁላችንም አሉን ለየት ያሉ  ከልጅነት የምናቃቸው አንዳንዴም የቅርብ ጎደኞቻችን የሆኑ አሉን።  ከላይ የጠቀስኩትን life የማያቁት ከእድሜያቸው በላይ የበሰሉ አሁን ላይ ሆነው የወደፊታቸውን ዛሬ የሚቀርፁ,ሚያልሙ ትልቅ የማይዳሰስ የማይጨበጥ ለኛ ሲነግሩን እንድናሾፍባቸው የሚያደርጉን  ቁም ነገር የሚያበዙ በአብዛኛው ነገራቸው ለየት ያሉ ከኛ በተቃራኒ የቋሙ ውስጣቸው ሌላ ትልቅ ሰው አለ እስከምንል ንግግራቸው እና ሀሳባቸው የሚያስደንቀን እኛም የእነሱ አለም ገብቶንሞ ሆነ ሳይገባን እንዲሳካላቸው የምንመኝላቸው አሉን ብርቅዬ ጎደኞች ከዘፋኞች መሃል ያሉ ዘማሪዎች ከወረኞች መሃል ያሉ ዝምተኞች ከተደባዳቢዎች መሃል ያሉ አስታራቂዎች አሉን በትምህርት ብቻ ዕውቀታቸው ያለተገደበ ከኛ መሃል ምሁሮች አሉን። ታዲያ ይሄ ሁሉ ነገር እንዳነሳ ያስገደደኝ አንድ ነገር ነበር ተዕለታት በአንዱ ቀን ማታ ላይ ከቤተሰቦቼ ጋር ተሰብስበን  ቁጭ በልንበት ልጄ ለመዝናኛ የሚሆን ነገር ለመክፈት ከቻናል ቻናል ይቀያይራል በድንገት ግን አንድ  ከዚ ቀደም የማውቀውን ሰው በቲቪ መስኮት አየሁት በፍጥነት እንዲመልሰው ወደቻናሉ ልጄን አዘዝኩት ትዕዛዝ ይሁን ቁጣ አላቀውም እሱም ደንግጦል መለሰው እንዳልኩት አየሁት በድጋሚ ልቤ ደነገጠ የማውቀው ስሜት ተሰማኝ ልዩ ታሪክ አለኝ ከሱ ጋር ግን አልመጣል አለኝ ተብሰለሰልኩ አዕምሮዬን አስጨነቁት ጎልማሳውን ሰው ለማስታወስ የአዕምሮዬን የትውስታ ፋይሎች አገላበጥኩ ደከምኩ ከብዙ ድካም በኋላ የሆነ ሰው ያፋልጉኝ ማስታወቂያ ተለጥፏለት ሲገኝ እንዳለው ስሜት ተሰማኝ ተደሰትኩ አመሰገንኩ ወደራሴ ስመለስ  ቆሜ ነበር እና ተረጋግቼ ቁጭ አልኩ ሳቅኩ ከልቤ ተገረምኩ የደስታም እንባ አነባው ይሄ ሁሉ ሲከሰት ለካ እረስቻቸዋለው ቤተሰቦቼን ቁጭ ብለው እንደቲያትር ታዳሚ ይመለከቱኛል ከዛም ትወናው  አለቀ መሰለኝ ሚስቴ ልጆቼን ወደክፍላቸው አስገብታ ልታወራኝ መጣች መቼም ልጆጄ ዛሬ እንቅልፍ የላቸውም ምን እንደተፈጠረ ሲያሰላስሉ ሲጠይቁ እና ሲመልሱ ነው ሚያደሪት ።ወደሷ ስለመስ በአግርሞት እና በነዛ ስስ አይኖቾ በስስት እያየቺኝ ስፖንጅ በሚመስሉ እጆቾ እየዳበሰቺኝ ምን እንደተፈጠረ ጠየቀቺኝ ምኑን ብዬ ምን ልበልሽ ከየትኛው ልጀምርልሽ አልኳት አይን አይኖን እያየዋት እኔም በተራዬ ።ደስ ካለ የሷ ምላሽ ነበር  በሀሳብ ብዙ አመታት ተመልሼ ጀመረኩት ትረካውን አንድም ለሶ አንድሜ ለራሴ ።

ይቀጥላል part 2

@wegoch
@wegoch
@paappii