ወግ ብቻ
19.3K subscribers
506 photos
11 videos
20 files
48 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch
@zefenbicha

Creator @leul_mekonnen1
Download Telegram
Finally 🙏
ፈጣሪ ታላቅ ነው።
አዕጋረ ፀሓይ ዛሬ ሕትመቷን ጨርሳ ለስርጭት ጃዕፋር መፅሀፍት ተልካለች። በቅርቡም በመላው አዲስ አበባ እና ክልል ከተሞች ትዘልቃለች።
በሂደቱ ሁሉ ከጎናችን ለነበራችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው።
መልካም ንባብ

ደራሲ ሚካኤል አስጨናቂ
1892 ላይ ስታንፎርድ ዩንቨርስቲ ይማር የነበረ የ18 አመት ወጣት ለትምህረቱ የሚከፍለው ገንዘብ ይቸገራል። ገንዘብ የሚጠይቀው ሰውም አልነበረውም። በዚህ ሃሳብ እያለ ከጓደኛውጋ ይማከራል ... 'ለምን የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅተን ገንዘብ አንሰበስብም?'

ሁለቱ ወጣቶች ወደ አንድ Ignacy J.Paderewski የሚባል ታዋቂ ፒያኒስትጋ ይሄዱና ማናጀሩን ያገኛሉ። ማናጀሩም $2000 ክፈሉና እንደፈቀዳችሁ አላቸው። ወጣቶቹ ሙዚቃቸውን እያጠኑ እና እየተለማመዱ ለሙዚቃ ፕሮግራማቸው ይዘጋጁ ጀመረ

ያ የተባለው ሙዚቃቸውን የሚያቀርቡበት ቀን ደረሰ። ብዙ ትኬት ስላልተሸጠ ባጠቃላይ ያገኙት ገቢ 1600 ዶላር ብቻ ሆነ። ያቺን ያገኟትን ገንዘብ ይዘው ወደ Paderewski ይሄዱና እንዳሰብነው አልሆነልንም። ስለዚህ የምንመልስልህ ያገኘነውን ሙሉ 1600 እና ወደፊት ልታወጣው የምትችለው የአራትመቶ ዶላር ደረቅ ቼክ ነው ይቅርታ አሉት።

ሰውየው ግን ጭራሽ ተቆጥቶ ቼኩን ቀደደ እና ገንዘቡን አልቀበልም አላቸው። ይህ ገንዘብ ለአንዳንድ ወጪ ያወጣችሁትን ይሸፍንላችኋል። የቀረውን ለራሳችሁ ተጠቀሙት አላቸው።

ወጣቶቹ ተደንቀው አመስግነውት ወጡ። ስለተደረገላቸው መልካምነት እጅግ ተደሰቱ።

የማያውቃቸውን ሰዎች ለምን በዚህ መጠን ሊረዳቸው ፈለገ? ከእነሱ ምንንም ሳይጠብቅ ለምን ይሄንን ቸርነት አደረገላቸው? አንዳንዶቻችን "ይህንን ሰው በዚህ በተቸገረው ነገር ብረዳው ለኔ ምን እጠቀማለሁ?" ብለን እናስባለን። አንዳንድ ብሩህ ልብ ያላቸው ደሞ "ይህንን ሰው በዚህ በተቸገረበት ሰአት የአቅሜን ባልረዳው ምን ይሆናል?" ብለው ስለ እዛ ሰው ያስባሉ

ከጊዜያት በኋላ ይህ ፒያኒስት የ ፖላንድ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነ። የተወደደ ገዢ ሆኖ በሚመራበት ዘመኑ የአለም ጦርነት ተጀመረ እና 1.5 ሚሊየን ፖላንዳውያን ተራቡ። እሱም እርዱኝ ብሎ አለማትን መለመን ጀመረ።

ወደ አሜሪካን መልዕክት ላከ። በሰአቱ የአሜሪካ ፕሬዚደንት የነበሩት Herbert Hoover ወዲያው እርዳታ አደረጉለት። በዚህም የፖላንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ተደስቶ ይህንን ሰው በአካል ያለበት ሄጄ አመሰግነዋለሁ ብሎ አሜሪካ መጥቶ እጅ ነሳ። 'ለህዝቤ እና ለእኔ ላደረግህልን በጎነት አመሰግናለሁ' አለ የፖላንዱ ጠቅላይ ሚንስትር።

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ግን 'ለምን ታመሰግነኛለህ?' አለው

'ከብዙ አመታት በፊት ሁለት ተማሪዎችን ለትምህርት የሚከፍሉት ሲቸገሩ በጎ ፈቃድ ያደረግህላቸው ትዝ አለህ? አንዱ ወጣት እኔ ነበርኩ'

By Mastewal Aseffa

@wegoch
@wegoch
@paappii
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (Leul M.)
Exhibition titled, “መልክ”
By Surafel Alemneh

Artawi Gallery
opened for public.

The galley opened  until 20 July 2024 starting from 2 PM - 6 PM bole, around British international school or 250m in from Yod Abyssinia, Kkare Homes, 2nd Floor


@seiloch
መናፍስት አማረኛ አወራ ?
                          በግዕዝ ሙላት

ሰማዬ ጋር የክዋክብት መብራት የአራስ ህፃን አይን መስለው ቡዝዝ ብለው በየፈርጡ ተኮልኩለዋል ። ጨለማው ከሰማዬ ብርሃን ገዝፎ መጠነኛ ንፋስ የግቢውን ዛፎች ያስደንሳቸዋል !ቅጠሎች ደሞ ሰክረዋል መሰል እዬተንገደገዱ ይወድቃሉ (የንፋሱን ውስኪ ገልብጠው)።

እዬለፈለፍኩ ነው? ግን እያወራሁ አይደለም? የተፈጥሮ የድምፅ ፀጥታ ከራሴ ጋር ሊያመካክረኝ ዝግ ስብሰባ ይዟል። ቆይ... ቆይ... ቆይ...ሲጀምር... ለምንድነው? ከራሴ ጋር ምማከረው?... እንደዛ ሲባልስ... ደባል ስዕብና በውስጤ አለ ወይስ የለም  ? ሲጀምርስ ምክክርን ከዚህ ምን አመጣው ? ብሽቅ!(አለ ያነኛው )

አንዳንዴ በቀን ኑሮ ውስጥ ያሉ ትዕይንቶች ለስዕብናችን የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ(political speech ሆነ መሰል ?😏ለምን የድመቱን ድርሻ አይወስዱም ምን አገባኝ? አይጥ!) (አለ ይሄኛው)

ሲጀምርስ ፖለቲካን እዚህ ምን አመጣው? አያችሁ ይሄ ነው ስዕብና ማለት ዝም ብሎ መዘባረቅ። ስዕብና ፀንቶ የሚኖር ሀውልት አይደለም! በሁኔታው ሁሉ ይቀያየራል። ለዛም ይመስለኛል ህፃን ልጅ ልጅ ሳለ ንፁህ ይሆንና የኋለኛው ማንነቱ በአረመኔነት የሚቀዬረው ።
(በሚያዬው ትዕይንት እና ገቢር መጠን...ስል ገና)
" እና እኛ ምን አገባን?' ቅማላም' ቁጭ በል" አለኝ ያነኛው(የትኛው?)

<እኔ>
ሰአቱ ስንት እንደሆነ አላቅም.. እርግጥ ነው መብራት ስለጠፋ (መጀመሪያውንም ስለሌለ)  ብቻ ስልኬም ባትሪው ዘግቷል ።ይመስለኛል ይሄን የተፈጥሮ ፀጥታ  እንዳዳምጥ ያደረገኝ ሰው የፈጠራቸው ነገሮች በቴክኒካል ችግር መደበቃቸውን ነው(ባትሪ መዝጋቱን ማለቴ ነው)።የሚገርመው ግን ተፈጥሮ የምትባለው ሴት ግን (ሁሉንም ከሴት እናገናኜዋለን!) ቴክኒካል ችግር የለባትም! አሁን አሁን የአዬር ብክለት ሚባለው ነገር ትልልቅ ትሪሊዮነሮችን ባለሀብት በገነቡት እንዱስትሪ በሚለቀቀው ጋዝ ተበከለና መልሰው በበከሉት አዬር ያገኙትን ትርፍ መልሰው የአዬር ብክለትን ለማስተካከል ይደክሙበታል።...ቆሻሻ አለ ጋሽነት። (ጋሽነት የሰፈራችን ሰው ነው ልጁ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ልጁ ጋር ያለውን ፍቅር ለመግለፅ የሚጠቀምባት ቃል ናት!ቆሻሻ አለ ጋሽነት( አለ ተኝቶ የነበረው እኔ?)

<ያነኛው እኔ>
በቃ ሰው እንዲህ ነው ዝም ብሎ መባከን መባከን መባከን(አልጨረሰም ገና) ..."አንተ ልጅ ተመለስ ተው" አለ የሆነ ድምፅ ከጨለማው መሃል' እማዬ ድረሽልኝ' ምንድነው የሰማሁት(በአካል የሚታዬው አፌተናገረ)...መናፍስት ?... አይ አይ መናፍስት አማረኛ አይችሉም! ...እና ማነው ያወራው?...ፀጥ አልኩ ሁሉም ነገር ፀጥ አለ ድጋሚ..."ለምን ዝም አልክ" አለ ያ ድምፅ...'ኧረ ደገመው' አልኩና ጆሮዬን የት ጋር ድምፁ እንደመጣ አጣራው ከውስጥህ ነኝ ያለሁት አለኝ የሆነ ድምፅ!.. ግን የሆድ ድምፅ ይመስላል (እ? እንዴት ራሴው አውርቼ ራሴው ፈራሁ አንዳንዴ ከሰውነታችን የሚወጡ ትርጉም የለሽ ድምፆች የሆነ ቅፅፈት ትርጉም ይኖራቸዋል ልክ እንደዚሁ ) በድጋሚ የሚናገረው ድምፅ ተሰማኝ የራሴው ስዕብና ነው ላምን አልቻልኩም "ኧረ ቤስሚያም"አሉ አባ ጎርብጥ

<ወዲህኛው እኔ>
ነግሬቹሃለሁ ሁላችንም በሁኔታዎች የሚቀያዬር ስዕብና ነው ያለን..."መጣሁልህ አንተ ፈሳም" አለኝ ሌላ ድምፅ ከዛፉ ስር "እማዬ ድረሽ መናፍስት አማረኛ አወራ?"....እዬሮጥኩ ወደ ቤቴ....

@geez_mulat

@wegoch
@wegoch
@wegoch
..."አባዬ" (ልጅ)

..."አቤት" (አባት)

..."በግ አስተኝተን፡ አርደን፡ ደሙን አፍሥሰን፡ በጥብስ እና በቅቅል አርገን ስንበላው ነፍሱን በማጥፋታችን ሀጥያት አይሆንብንም?"(ልጅ)

..."ምን ስትል አሰብከው ልጄ? እረ አይሆንብንም።" (አባት)

..."እንዴ አባዬ እየገደልን አደለ እንዴ፡ እንዴት ሀጥያት አይሆንብንም?" (ልጅ)

..."ምን መሰለህ ልጄ... እንዴት ላስረዳህ?... ሞት እኮ በር እንጂ መጨረሻ አይደለም፡ በጉን ስንበላው በኛ ውስጥ መኖሩ ይቀጥላል እንጂ ጨርሶ አይሞትም" (አባት)

..."እረ እረ አባዬ ደሞ እንደዚ አለ እንዴ?" (ልጅ)

...."አዎ! እውነት ስልህ ፥ ያው የበላነው ተስማምቶን ሀይል እና ጉልበት አግኝተን፡ አካላዊ እድገት እያመጣን አይደል የምንኖረው ፡ ያ ታድያ እኮ በኛ ኖረ ማለት ነው ልጄ" (አባት)

..."እሺ እና ጋሽ ጀንበሬ እንደውም ባለፈው በለሊት ወደስራ ሲሄዱ ጅብ የበላቸው ጅብ ሆነው እየኖሩ ነው ማለት ነው አባዬ?" (ልጅ)

..."ወይ ጉድ ዛሬ እንደው ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት...ማነሽ 'አልማዝ ነይ እስኪ ይሄን ልጅ ወደዛ ወስደሽ ገላግይኝ'...አልሞት አልኩህ?" (አባት)

..."ምን አልክ አባዬ?" (ልጅ)

..."ምንም ወዲህ ነው የእራት ሰዓት ደርሷል እናትህን ወስደሽ አብይው እያልኳት ነው....'አንቺ አልማዝ ነይ እኮ ነው ምልሽ'. ..አትሰማኝም እንዴ?" (አባት)

..."እና ንገረኛ አባቴ ጋሽ ጀንበሬ ጅብ ሆነዋል ማለት ነው? የባቢ አባት ጅብ ናቸው ማለት ነው?" (ልጅ)

..."ሆሆ! ደሞ ነገ ት/ት ቤት ሄደህ 'የባቢ አባት ጅብ ሆኑ እንጂ አልሞቱም ብሏል አባዬ' ልትል ነው ሆሆ! ደሞ ከጎረቤቶቼ አቆራርጠኛ! በል በል የለም ያልኩህን እርሳው በቃ እንደውም ሀጥያት ነው ከንግዲህ በግ የሚባል አናርድም።. ..ግልግል እንደውም ተወዷል...ሆ! በገዛ እጄ...ቆይ እዛ ት/ት ቤት ምን ስትማሩ ነው የምትውሉት?" (አባት)

..." እርሳው? አባዬ ደሞ አንዴ ነግረኸኝ እንዴት ነው ምረሳው?...ደሞ ት/ት ቤት ሳይሆን አንተ እኮ ነህ የነገርከኝ በግን ስንበላው እኛን እንደሚሆን...ት/ት ቤት ምን አጠፉ....ህእ!" (ልጅ)

..."ማ? እኔ አልወጣኝም! አይወጣኝምም!. ..ምን ይላል ይሄ...በል ጥፋ ከዚ. ..ድራሽ አባክ ይጥፋና...አትሄድም!".....

By Mikiyas Beshada Kebede

@wegoch
@wegoch
@paappii
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (Leul M.)
#ወደ_ግጥም__ወደ_ነብይ
ፈግታን ስለቸረን መነሱ ___ ስላስጠለለን ዋርካነቱ
ስለ አፅናኝ ጨዋታዎቹ ___ ሕይወት ስለሚያሞቁ ግጥሞቹ
ቅንነቱን ለማቀንቀን ___ አባትነቱን ለማወደስ
ስለ ግጥም _ _ _ ደግሞም ስለ ነብይ
ቅዳሜ እንሰበሰባለን። ፈንድቃ ቤተ ጥበብ [ ፈንድቃ የጥበባትና ባህል ማዕከል:Fendika Art & Cultural Center ]

• ውብ ግጥሞች ልዩ
• ልዩ የሙዚቃ ጨዋታዎች
• ነገረ ነብይ
• የጥበብ ቅማ ቅመም

የምትወዷቸው የምንወዳቸው ሁሉ አሉ። ስለ ግጥም _ ስለነብይ።

ከ8:00 ቀደም ብላችሁ ኑ።
ቡናውም ጨዋታውም ወዳጅ ትውውቁም እንዳይቀርባችሁ።

ቅዳሜ ሀምሌ 6 2016 ዓ.ም 😍🙏🙏🙏😍

@getem
@getem