ወግ ብቻ
17.1K subscribers
526 photos
11 videos
21 files
52 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch
@zefenbicha

Creator @leul_mekonnen1
Download Telegram
ወግ ብቻ pinned Deleted message
"እማዬኮ ሔዱ"
.
.
ባውሮፕላን ሔዱ። ጎረቤቶቻቸው አዋጥተው በአውሮፕላን አበረሯቸው።
ፎቶ እንኳ እንደሌለን ያወቅኩት ሲሔዱ ነበር። ሙሉ ጊቢውን ጠየቅኩ ማንም የለውም።
"ሳላገኘው ልሔድ ነው?" እያሉ ሳለ ትናንት ከአዲስ አበባ መጣሁ።
"እማዬ ማናቸው?"
የዩቲዩብ ትምህርቶቼን የሚከታተል ድምጻቸውን ሳይሰማ አይቀርም።
..
"ለምን ሔዱ?"
.
ምክንያታቸውን ሲናገሩ...
"ደከመኝ! የሽንት ውሀ ማንጠልጠል እያቃተኝ መጣ"
" ደጁ ላይ አስቀምጡልኝ ብለው አላቀብሎትም ያለ ሰው አለ? መሔድ ደስ ካላሎት ለምን አይቀሩም ?"
🥺 " ላዬ ላይ ሲያመልጠኝስ? ምን ታደርጋላችሁ?"
.
እማዬ ለምን በዚህ መሆን ፈለጉ?
.
1. ሀሜት አለ።
አራት አመት ገደማ ሆኗቸዋል ድሬዳዋ ከገቡ። የወሎ ሰው ናቸው።
ተመልሶ ወደ ልጆቻቸው መሔድ ደስ አላላቸውም። ስጋ እንደ ባዳ እንደማይደላ ደመነፍሳቸው ነግሯቸዋል። ዘመድ ስጋን እንጂ ስነልቦናን አይረዳም።
.
ባዳ መሀል ሀሜት አለ። ሀሜትኮ ንሰሀ ነው አይምሮን ያጸዳል። ቅርጥፍ አድርጎ ማማት ያልቻለ ሰው paranoid የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። በአጭሩ ሀሜት #የአይምሮ_ሰገራ ይመስላል። ቆሻሻ ነው ግን መውጣት አለበት ልክ እንደ አር። አማናዊው ሰገራ በባለቤቱ ግፊት በምጥ ይወጣል! የአይምሮ ሰገራ ለማውጣት ግን #ባዳ ይፈልጋል።
.
#ባል ባዳ ነው። ለዛ ነው ሚስቱን #የሚበዳው። ባዳው ባል ከሚስቴ ጋር ይሕ #ስጋዬ ነው ይህ #ስራዬ ነው #ሳይል በሀሜት ከተንበለበለ አይምሮው ጤነኛ ይሆናል! ረጅም ይኖራል። "ሴትንኳ ስራዋ ነው" 🤭 አላልኩም ስርአት!!! ሚስትም ከጎረቤት ማማት ትታ ከባሏ ጋር በማማት ከተባበረች #እባብ ፈጣሪን የሚያሳማው ባዳ አያገኝም።
..
2. ትዕዛዝ አለ።
.
ዘመድ እንደባዳ እርጅናን አያከብርም። አሮጊቷን አንቺ ሲል ያቀረበ ይመስላል። ፍቅር ክብርን የሚበልጥ የሚመስለው ይኖራል። በፍቅር እንደልብ መታዘዝ የለም በክብር እንጂ። አልገባንም ከምናፈቅረው ለምናከብረው እንታዘዛለን። ከእናት በላይ ለአባት እንደማለት።
.
የምናፈቅረው ላይ የምናከብረው ነገር ከተገኘ አቤት መታደላችን።
.
#እማዬ ይከበራሉ። #ደም ለማየት ወራት የቀሯትን የደረሰች ልጅ ሲልኩ በሞገስ ነበር። ማንም የእርጅና ዘውዳቸውን እያየ ይታዘዝላቸዋል። ምናልባትምኮ ልጅቱን ከ 20 ሜትር የጠሯት አንድ እርምጃ ርቀት ላይ ያለች ከሰል እንድታቀብላቸው ነው። ፊቷን ቅጭም እንዳደረገች አቤት ሳትል ታቀብላቸዋለች። እግረመንገድ ለሚያወሯት ዝብዛብ አትመልስም! አቀብላቸው ስትመለስ እየተጉመጠመጠች ነው።
"አንቺ አስቀያሚ ስለምወድሽ ነውኮ!" ምናምን ይላሉ። "ኧረ ጎረመሰች" ይላሉ።
ሌላ ትእዛዝ እንዳይደግሟት እየጸለየች አጎንብሳ ትፈተለካለች። የልጅ ልጃቸው ብትሆንስ?😁
(አንድ የልጅነት ጓደኛዬ አጨባሽ አያቱ በመላክ አማረውት "ጂፓሱ ሸርተት ብሎ በወደቀባቸው" ይለኝ ነበር)
.
.
3. ሰላምታ ያገኛሉ።

ኦኦ እማዬ ሰላምታ ነፍሳቸው ነው። ማንም ሰላም ሳይል አያመልጣትም! በጊቢው 12 ተከራይ አለ። ከአንዱ ቤት ቢያንስ 2 ሰላምታ አያጡም። ሀያአራት ደና አደርክ እና ደና አመሸህ። አንዳንዴም እድል ከቀናም ስምንት ደናእደሩ ይደርሳቸዋል።
.
በሳቸው እድሜ ይሔ ቀላል ሀብት እንይመስልህ። ደሞ ትንሽ ስኳርና ሌላም በሽታ አላቸው/አለባቸው። ስለዚህ በትንሹ ሁለት ረዘም አድርጎ ጤናቸውን ጠያቂ ይገኛል። እግረመንገድህን ስለጤናህ ተመክረህ ታልፋለህ። ምናልባት ከትናንት ወዲያ አንዷ ጎረቤትህ እናትህ ከሪፍትቫሊ #የገዛችውን(ማነው ያገኘችውን! No ያመጣችውን! ይሔም አይሆንም ብቻ whatever u call it) የዲግሪ ወሬ ሰምተዋል።
"እንኳን ደስ አላት...ምን ተማረች...አንተን የመሰለ አድራሳ ምነው እስካሁን...😁" ብዙ ወሬ! ቲክቶክና ፌስቡክ የማይጠቀሙ ሰዎች መሰንበቻ የሚሆን ወሬና ጨዋታቸውን ከየት ያመጣሉ? እንደዚህ ነዋ የሚሸቃቅሉት። በስጋቸው መሀል ይሔም የለም።
.
.
5. ከሰል ይሸጣሉ።

ይሔ ደሞ እንድሜ ለመብራትሀይል መላ ሰፈሩን ወደሳቸው ይነዳዋል።
በህጻን አዋቂው "እማዬ የሉም" መባል ቀላል አይምሰላችሁ። በቀደም በመልክ የማያውቀኝ አንዱ
"የበሀይሉ መጸሀፍ አለ?" ሲሉት ጃፈር ጎን ቆሜ የተሰማኝን ሙቀት አልረሳም። 😊
ጃፊ በአይኑ አይኔን እያጠቀሰ "አልቃለች..." ሲልማ እዛው ገልቤ ልመታ ምንም አልቀረኝ።😁
እማዬ...
"ዝርዝር ይዛችሗል?
ማነው ስምህ አንተ? አባትህ ይቅማል? በል ቀጣይ ስትመጣ ፌስታል ይዘህ ከመጣህ ለበጎቻችሁ የተረፈ ሰላጣና ድንች አዘጋጅልሀለሁ። ምነው አጠርክብኝ ደሞ"
" ኧረ እናቴ ላጭታኝ ነው"
" በልሺ ሒድ አጭበርባሪ ቁመትህን የማላውቅ መስሎህ ነው አ?" (ይቺ ሁለት መስመር እንኳ ነገር አማረልኝ ብዬ ልቦለድ ሳደርጋት ነው። እማዬ አይሞጣሞጡም። አይናፋር አሮጊት ናቸው)
.
ልጆቻቸው ጋር ሲሔዱ ቅላታቸውን እና ክብራቸውን የሚፈታተን ከሰል መሸጥ አይችሉም። ከሰል መሸጥ እናት ማውረድ መስሏቸው። የዋህነታችን!
.
.
6. ትረባ
ትረባ አስለምጃቸው ነበር። የተለመደ ሰላምታቸው ሲያሰለቸኝ የፈጠርኩት መላ ናት። ለተፈሳው ለተገሳሁ ሁሉ ሊመክሩኝ ሲሞክሩ ቤት ገብቼ መሀል ጣት እስከማውጣት ስፈተን ትረባ አስለመድኳቸው።
.
"ምንስለሆኑ ነው እርሶ ሚካኤልን የማያስገቡት" ሙስሊም ናቸውና ይቀኑ ይሆናል ነጭ የለበሱ ጎረቤቶቻቸው ግቢውን አስታቅፈዋቸው ሲጠፉ። ሳቁ አይገልጸውም ፈነዱ! የወለቀ ሶስት ጥርሳቸው ፊት ሻሻቸውን ሳይጎትቱ። ተመልሰው ለመጡ አንጋሽ ጎረቤቶቻቸው እያወሯት ሰላምታቸውን አረዘሙ።
.
በቀደም ከውጪ ሲገቡ አይቼ..
"ከየት ነው?" ስላቸው ገቡልኝ
" ወክ ወጥቼ። ጠበስኩኮ!" 😂😂
ኦቲስቲኩ በሀይሉ ከውስጤ ምን ይላል...
"እንዴ በስተርጅና" ግም!
አፌ " መቼ ነው የሚያስተዋውቁን?"
አፋቸውን አፍነው 🤭 " በል አልችልህም ውጣልኝ"
.
ከሗላዬ...
"ሰላም ይመልስህ በል! ደና እደር..."
መቼም አመል ቶሎ አይለቅ።
.
እኚ ናቸው የሔዱት።

#በሃይሉ_ሙሉጌታ

@wegoch
👍53👎63🔥1😁1
‹‹አልተበላሸም››


÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷
1989 ዓ.ም.



አስራ ስድስት ዓመቷ ነበር፡፡ የአስረኛ ክፍል ተማሪ ነበረች፡፡ ድርስ ነፍሠ ጡር ነበረች፡፡



የልጇ አባት (የልጅሽ አባት ሲባል ደስ አይላትም፡፡ ያስረገዘኝ  ወንድ በሉ ትላለች) የሰባት ወር ቦይፍሬንዷ ነበር፡፡ ማርገዟን እንደሰማ ብን ብሎ ጠፋ፡፡



ለመጀመሪያ ጊዜ ያፈቀረችው ወንድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሳማት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰውነቷን የሰጠችው፡፡ 



ከብዙ ማባበል በኋላ ስትለምደውና ስትወደው በአንዱ ቀን እንዲህ አላት፤
‹‹አጎቴ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት እዚሁ ቤላ ጋር ነው፡፡ ለስራ ሐረር ሲሄድ ቁልፍ ሰጥቶኛል፡፡ ለምን እዚያ ሄደን በነጻነት ስናወራ አንውልም?››

‹‹አጎቴ ቤት ልወስድሽና ድንግልናሽን ልወሰደው ›› የሚል ወንድ የለ መቼስ፡፡ 



እጁን ይዛ ተከተለችው፡፡  የአጎቱ አንድ ክፍል ቤት በአግባቡ ከተነጠፈ ፍራሽ፣ ከብዙ መፅሐፍትና ከትልቅ ቴፕና አጠገቡ ከተዘረገፉ ካሴቶች በስተቀር ዐይን የሚገባ ነገር አልነበራትም፡፡



ፍራሹ ላይ አደላድሎ እንዳስቀመጣት ሰንደል ለኮሰ፡፡

‹‹ዘና እንድንል ነው፡፡ በዚያ ላይ ቤቱ ተዘግቶ ስለዋለ ይናፈስ ብዬ ነው›› ብሎ፡፡ 

‹‹ሰንደል በየት ሃገር ነው የታፈነ ቤት የሚያናፍሰው..?ይልቅ ለምን መስኮቷን አትከፍታትም?›› አላለችውም፡፡


‹‹አጎቴ ሙዚቃ በሃይል ይወዳል፡፡ የወጣ ካሴት አያመልጠውም፡፡ ቆይ ሰሞኑን የወጣ የፍቅራዲስ ካሴት አለ፡፡ እሱን ልክፈተው ለሙድ›› አላት ቀጥሎ፡፡
ለሙድ፡፡



ምንም አላለችውም፡፡


ከዚያ….



ፍቅርአዲስ ቤቱን በአስረቅራቂ ድምፅዋ ስትሞላው የእሱ ከንፈሮች አንገቷ ላይ ነበሩ፡፡


ሰላማዊት ተነክታ የማታውቀው ቦታ ስትነካ ፍቅርአዲስ አትርሳኝ እያለች በሚያባብል ድምፅዋ ታለቃቅስ ነበር፡፡

ፍቅርአዲስ ፣
‹‹ሄደሃል አሉ ብዙ ርቀህ እንደኔ ሆነህ አንተም ናፍቀህ
ምናለ ሆዴ ብትመጣልኝ ብታስብልኝ››  ብላ ስትለማመጥ
‹‹እንዲመችሽ ጃኬትሽን አውልቂው›› ብሎ እየተለማመጣት ነበር፡፡

በስልምልም ዐይኖቹ ሲለማመናት፣ በምትወደው ድምፁ ሲያባብላት ታዘዘችለት፡፡



በዚያ ላይ ቀኑን ሙሉ እህል አልበላችም ነበር፡፡ ከምሳ በፊት አስፎርፏት ስትወጣ ምሳቃዋን ረስታ፡፡
ሲገቡ ከሱቅ ካስመጣላት ሙቅ ሚሪንዳ በቀር ሆዷ ባዶ ነበር፡፡ 
እንደማቅለሽለሽ እያላት ነበር፡፡

እስከዛሬ ድረስ ሙቅ ለስላሳ አልጠጣም ብላ ስትከላከል ብዙ ሰዎች ‹‹ብርድ አይደል…ምን ማለትሽ ነው?›› ሲሏት አታብራራም፡፡ ግን ካልቀዘቀዘ ለስላሳ፣ በተለይ ሚሪንዳ አትነካም፡፡


እስከዛሬ ድረስ ፍቅርአዲስን ስትሰማ ዐይኖቿ በእምባ ይሞላሉ፡፡  ምን ሆንሽ ብሎ የሚጠይቃት ሲኖር መልሷ አንድ ነው፡፡

‹‹ድምጽዋ ደስ ስለሚለኝ ነው››
ግን ውሸቷን ነው፡፡ ፍቅርአዲስ በአትርሳኝ ሙዚቃ አጃቢነት በአንዲት ቀን አስረግዞ የረሳት የመጀመሪያ ቦይፍሬንዷን ስለምታስታውሳት ነው፡፡ ድምፅዋ ሃዘን የሃዘን በረዶ ያወርድባታል፡፡



ከሶስት ወራት በኋላ የኮከበ ፅባህን ግምብ ተደግፈው እያወሩ ‹‹አርግዣለሁ›› ስትለው አመዱ የጨሰው ሳሙኤል ብን ብሎ ጠፋ፡፡

ምስጢረኛ ጓደኞቿ ‹‹ድሮስ ከቅምቢቢት ዱርዬ ምን ይጠበቃል?›› ብለው አብረዋት አለቀሱ፡፡

አማራጭ ስላልነበራት ቤት ሄዳ የሆነችውን ስትናገር አባቷ ያለችውን የሰሙበትን ጆሯቸውን ማስቆረጥ ቢችሉ ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እናቷም ከአንግዲህ ዐይኔ እንዳያይሽ አለቻት፡፡



ልብሷን ሸክፋ ወደ ብቸኛ መሸሸጊያዋ - ወደምትወዳት አክስቷ- ከመሄዷ በፊት ግን እናቷ ለሚቀጥሉት ሃያ አመታት ላትዘነጋው የወሰነችውን ነገር ተናገረቻት፡፡

‹‹ሕይወትሽን ጨርሰሽ አበላሽተሽዋል፡፡ ከእንግዲህ የትም አትደርሺም›› ብላ፡፡



እርግዝናዋ የኮከበጽባህ ትምህርት ቤት ርእሰ ሃሜት ሆኖ ቢከርምም በአክስቷ ፍቅርና ማበረታቻ ተደግፋ አስረኛ ክፍልን ከገፋ ሆዷ ጋር አገባደደችና ሰኔ 12/1989 ልጇን ወለደች፡፡


ሚካኤሏ አለቻት፡፡ የሰኔ ሚካኤል ልጅ ስለሆነች፡፡

አክስቷ ጥላ፣ አክስቷ ግድግዳና ማገር ሆናላት ሚካኤላን ከልጆቿ ጋር ስታሳድግላት መራር የእናቷን የእርግማን ቃል እንደምታመክን ቃል አስገብታት ነበር፡፡


‹‹ዛሬ ተሳስተሻል ማለት እስከወዲያኛው ሕይወትሽ ተበላሽቷል ማለት አይደለም፡፡ ይሄን እውነት ኖረሽ ካሳየሽኝ ልፋቴን ካስሽው ማለት ነው›› ብላ  የልጅነትእኩያ ልጇን ከጎኗ፣ የሰላማዊትን ጨቅላ በእቅፏ አድርጋ ስትመክራት ጉልበት ሆናት ነበር፡፡






ጥር 2016

የአርባ አራት ዐመቷ ሰላማዊት ከሃያ ስድስት ዐመት እኩያ ልጇ ሚካኤሏ ጋር እስክስታ ትወርዳለች፡፡
የሚካኤሏ ሰርግ ነው፡፡

በቅርበት የማያውቃቸው ሰው ሁሉ ደጋግሞ እንዲህ ይላል፡፡

ቀልዳችሁን ነው…እናቷ ልትሆን አትችልም፡፡ ታናሽ እህቷ ናት!
አይሆንም!
እውይ ደስ ሲሉ!
ታድለው!

ትንሽ ቆይቶ፣
ጭፈራው አድክሟት በሚዜና አጃቢዎቿ ታጅባ ከአዲሱ ባሏ ጋር የምትጨፍረውን ሙሽራ ልጇን እያየች ቁጭ ያለችው የሙሽሪት እናት ሙቅ ሚሪንዳዋን እየጠጣች ለራሷ-
‹‹ምንም የተበላሸ ነገር የለም፡፡ ሁሉም ነገር ግሩም ነው›› አለችና፤

ወዲያው በሰዎች ምርጫ ሙዚቃ ወደሚያጫውተው ዲጄ ለመሄድ ወሰነች፡፡


‹‹የፍቅርአዲስ ዘፈን ይኖረው ይሆን?›› ብላ እያሰበች፡፡

By Hiwot Emishaw

@wegoch
@wegoch
@paappii
93👍42😢8🔥6👏2
ብ-ት-ን-ት-ን
-----------------------



ወላጆቼና አያቴ የጎረቤቶቻቸው ቤት ዘወትር በቦምብ እየተደበደበ፣ ጥይት እንደ ወፍ በጣራቸው ላይ እየበረረ ከዚህ ቦታ ሽሹ ብላቸውም አንገታችን ይታረዳል አሉ፡፡



ይሄ የወንድማማቾች ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ ነጋ ጠባ ቀብር ላይ ናቸው፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት ማህበርተኞቻቸውን፣ አብሮ አደጎቻቸውን፣ ጎረቤቶቻቸውን፣ ዘመድ ወዳጆቻቸውን በየተራ፣ በሰልፍ ቀብረዋል፡፡ 



ትላንት ማታ ራሱ ወይዘሮ ታየች- የእማዬ የሴት ማህበር አጣጭ፣ የስንት ዘመን ባልንጀራና የታናሽ እህቴ የክርስትና እናት በሯ ላይ ተገድላ ተገኘች፡፡  ተባራሪ ጥይት ነው አሉ፡፡



‹‹በፈጠራችሁ ተለመኑኝ! አሁንም ከዚህ ሳይብስ ከዚህ እንሂድ›› ብዬ ተለማመጥኳቸው፡፡ ዛሬ ልመናዬ ውሃ ቢያነሳ ብዬ የደብራችንን ቄስ ለምኜ ይዤ መጥቻለሁ፡፡ አጠገቤ ቆመዋል፡፡



ካልሄድን ብዬ ልማለድ ስመጣ ይሄ አራተኛዬ ጊዜዬ ነው፡፡ ብዙ ሳትርቅ የምትገኘው ከተማ ውስጥ አነስተኛ አንድ ክፍል ቤት ተከራይቼ እኖራለሁ፡፡ ደልቃቃ ቤት አይደለችም ግን ቢያንስ ከጦር ሜዳው ሩቅ ናት፡፡



‹‹ልጄ! ቤታችን እዚህ ነው፡፡ ቀያችን ይሄ ነው፡፡ የት ነው ጥለነው የምንሄደው…?ለማን ጥለነው ነው የምንሄደው…? ጎጇችን ምን ይሆናል…እንስሶቻችንስ ማን ይይዝልናል?››  ብለው እንደ ሁልጊዜው አፍ አፌን አሉኝ፡፡




ቄሱ እምብዛም አላገዙኝም፡፡ ‘አረ እባክዎ እርዱኝ ! ›› ብዬ ብጠይቃቸው ይባስ ብለው፤
‹‹ተያቸው በቃ!  እንደ ፈቀዳቸው ይሁኑ፡፡ እዚሁ ይቆዩ›› አሉ፡፡
‹‹አባ! እዚህ ቆይተው ይሙቱ ነው የሚሉት?›› ብዬ እንደ መጮህ አደረገኝ፡፡ እማዬ አፍታም ሳትቆይ ቄሱን ልቆጣ በመድፈሬ ክፉኛ ተቆጣችኝ፡፡



ወዲያው ደግሞ ሁሉ ነገር ሰላም ይመስል ራት ሰርታ አብልታን ‹‹በይ አንቺ ነገ በጠዋት ወደ ሃገርሽ…ነገር ሳይጋጋል›› አለችኝ፡፡


እኔ እንድሄድ ይፈልጋሉ፡፡ እኔ እንዳልጎዳ ይፈልጋሉ፡፡


የአብዛኞቹ ከመንደሩ ወጥተው ከተማ የሚገኙ እኩዮቼ እጣ ፈንታ እንደሚደርሰኝ አውቀው ነበር፡፡ አንዱን ቀን ተደውሎ ቤታችሁ ጋዬ፣ እናት አባትሽ፣ አያትሽ ተገደሉ እንደምባል አውቀው ነበር፡፡


የእኔም ቤተሰቦች ተራ አሃዝ እንደሚሆኑ ልቦናዬ ያውቀው ነበር፡፡



ለመጨረሻ ልመናዬ ከመጣሁ ሳምንት እንኳን ሳይሞላኝ እንደማይቀርልኝ ያወቅሁትን መርዶ ተረዳሁ፡፡  ቤታችሁ በመትረየስ ተመቷል አሉኝ፡፡ እናትሽም.፣ አባትሽም፣ አያትሽም ሞተዋል አሉኝ፡፡



ከቀናት  ለቅሶ በኋላ ነገር ተረጋግቷል ሲባል እኔና ታላቅ ወንድሜ አውቶቢስ ይዘን ወደ ድሮ ቤታችን ተጓዝን፡፡


አይ ቤታችን እቴ! ቤታችን ወደነበረበት ባዶ ሜዳ ብል ይቀላል፡፡

ማልቀሱንስ ሳለቅስ ነው የከረምኩት፡፡



ነገር ግን እማዬ አባዬ እንደነገሩ አጣጥሮላት እንደ ጭስ ቤት የምትጠቀምበት ቦታ ላይ ያ የምወደውን ምስር ወጥ የምትሰራበት ሸክላ ድስት ብትንትን ብሎ ሳየው ግን ለአባባይ እስካስቸግር ማንባት ጀመርኩ፡፡



እኔ ልበታተንልሽ አባዬ፡፡  እኔ ብትንትን ልበል የኔ ዓለም፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Hiwot emishaw
😢73👍203
"ትንሽ ቦታ"

ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦

"ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል

አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ።

ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል...

ቺርስ ለአዲስ ዘመን
ቺርስ ለተስፋችን
ቺርስ🙏.


By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
79👍26🔥3👏2
ሌሶቶ

በዝግታ የሚራመዱ ሰዎች ሃገር (Kingdom of the mountains ይላሉ ራሳቸውን ሲያቆላምጡ)
ከፍ ካለ ተራራማ ሃገር ስለመጣሁ "Kingdom of the slow walkers" እላቸዋለሁ እኔ ደግሞ።

ማሴሩ ተራሮች መሃል የከተመች ከተማ ።
ፀጥ ያለች
የተረጋጋች
ወከባ የማይታይባት።

እግረኞቿና አሽከርካሪዎቿ ብንሮጥም የትም አንደርስም የሚሉ ይመስላሉ።

በጠራራ ፀሃይ ብርድልብስ እና ቦት ያደረገ በግ ነጂ ከጂፕ ነጂ ጋር የሚተላለፍባት፣

ደረቅ፣ ነፋሻማና ቀዝቃዛ
(መዘዞ፣ መሃል ሜዳ ወዘተን የምታስታውስ)፣

ሁሉንም ሱቆቿን 12 ሰአት ላይ ዘግታ ወደ ቤቷ የምትከተት፣

በአንዱ የተራራ ጫፍ ትልቅ ነጭ መስቀል የሰቀለች፣ በዚህም አዲግራትን የምታስታውስ።

ባገሬ መስከረም መጋቢትን የመሰለ ደረቅ ወቅት ላይ ተገኘሁ።
እዚህ የክፍል ማሞቂያ 25 ላይ ይደረጋል ከቅዝቃዜ ለመሸሽ (እንደ ኳታር ባለ ሃገር ደግሞ ማቀዝቀዣ 25 ላይ የሚደረገው ከውጪው ሙቀት ለመሸሽ ነው።)

2800 ሜትር አናት ላይ አድጌ 1600 ሜትራቸውን ማድነቅ አልቻልኩም። በመጓዝ ብዛት የገባኝ ተራራ ለብዙ የአፍሪካ ሃገራት ብርቅ መሆኑ ነው /ደብረሲናን፣ ደሴን፣ አሰላን፣ አርሲ ቀርሳን፣ አዲስአበባን ላየ ሰው ማሴሩ የጉብታ ከተማ ነው/።

የዚህ ሃገር ሰዎች ንጉሳቸውን ይወድዳሉ።
ወይም የሚወዱ ይመስላሉ።

ከባድ ባለስልጣን የተባለው ብርድልብስ ለብሶ ስብሰባ ሊመጣ ይችላል።

ሁሉም በሚባል ሁኔታ ክብ ባርኔጣ ያደርጋሉ።

ዶላር ወደ ሌሶቶ ሎቲ መቀየር ፈልገን ካረፍንበት ሆቴል ፊትለፊት ወዳለ ካፌ ነገር መሩን። ሃበሾች ተሰብስበው ያወራሉ። የካፌውም ባለቤት፣ ዶላር ቀያሪውም የኛው ሰዎች ናቸው። ባልተለመደ ሁኔታ እዚህ የሚኖረው ሃበሻ አብዛኛው Expat ነው። የ አፍሪካ ህብረት፣ የ UN ሰራተኛ ወይንም በፕሮጀክቶች የተቀጠረ ሃኪምና ኢንጂነር።

" አንድ የሃበሻ ሬስቶራንት አለ ለበአል እዚያ እንወስዳችኋለን" አሉን።

ድሮ ድሮ የበአል መንገድ ያማርረኝ ነበርና
አንድ ቀን እናቴን
"መንገድ አማረረኝ የበአል ሰሞን ልቅርና በአዘቦት ቀን እየመጣሁ ልጠይቅሽ?" አልኳት።
መለሰች
" ስንት በአል የምናከብር ይመስልሃል ከዚህ በኋላ? ስሞት ትቀራለህ አትቸኩል።"

ዛሬ የአደይ አበባ፣ የበአል ግርግር፣ የመስከረም ምልክት አንዱም በማይታይበት ከተማ ሆኜ ንግግሯን አስታወስኩ።
እንቁጣጣሽ ሲያመልጠኝ ሁለተኛዬ ነው (የዛሬ አመት በጦርነት ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ፣ ዘንድሮ በስራ)። ስንት እንቁጣጣሽ እንደቀረኝ ባላውቅም፣ ለኔ ለራሴ የበአል ጉጉቱ ባይኖረኝም ከቤተሰቤ ጋር(ከምወዳቸውም ሁሉ ጋር) የሚኖረኝ ጊዜ የተገደበ ነውና አለመገኘቴ አስደበረኝ።

የመንገዱ ሰልፍና ምሬት፣ የበአል ገበያ፣ የበአል ዘፈኖች፣ የእናቴንና እህቴን ቤት ውስጥ ወዲያ ወዲህ ማለት፣ የአባቴን ደጁን ለእርድ ማስተካከል፣ የወንድሜን ለቅዳሴ ለመሄድ መዘጋጀት፣ አልፌ የምሄድባቸውን አረንጓዴና አበባ የለበሱ ሜዳዎችና ተራሮች እናፍቃለሁ።

ከቤተክርስቲያን መልስ ስለምንበላው ጥብስ፣ ከፋዘር ጋር ተጋግዘን ስለምንገፈው በግ፣ በደምብ ስለማላውቃቸው ጎረቤቶች፣ ስለ ብዙ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች፣ ስለ ድፎ ዳቦ፣ ስለ ቡና አስባለሁ።

እዚህ ያለው ቡና በጣም ቢቀጥንብኝ ከኢትዮጲያ መሆኔን አውቃ "ሰላም ነው?" ያለችኝን አስተናጋጅ ፈልጌ ጠራሁ።
"This coffee is too weak I need somthing strong"
"Our coffee is not like yours".

የጀበና እጣቢ የሚመስል ነገር እየጠጣሁ አለሁ። ሆድ ለባሰው ....

ከበአል ድባብ ያላመለጠኝ ብቸኛ ነገር የፌስቡክ ፖስትና የቴሌግራም ስቶሪ ነውና ....

ሁላችሁንም እንኳን አደረሳችሁ።
መልካም አዲስ አመት።

ወንድማችሁ ነኝ ከጉብታዎች አናት ማሴሩ።

By haileleul Aph

@wegoch
@wegoch
@paappii
28👍25😢3🥰2🔥1
«ካባዬ»
(ከለእርቃን ሩብ ጉዳይ መፅሐፍ)

ክፍል አንድ

------------
ይሄንን ኮንዶሚኒየም ቤት ለማግኘት ከሦስት ወር በላይ ተንከራትቻለሁ።

ኪራይ ነው።
ዛሬ ዛሬ አዲስአበባ ላይ ፍላጎትንም፣ አቅምንም አጣጥሞ የሚገኝ የኪራይ ቤት
ማግኘት ሕልም ነው። እኔ ደግሞ የብር ችግር እንደሌለበት ሰው ስመርጥ ዐይን
የለኝም። ሀብታም ስላልሆንኩ ጠባብ ቤት መኖር ይፈረድብኝ፣ ግን ጠባብም
የተግማማም መሆን አለበት?



የለበትም።
ለዚህ ነው ይህንን አራተኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ በጣም ጠባብ ግን ንጹህና ሰላማዊ
ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየምለማግኘት ሦስት ወራት የፈጀብኝ። ከንጽሕናው ፀጥታው፣
አራተኛ ፎቅ ጥግ ላይ ክትት ብሎ መገኘቱ ማረከኝና ተከራየሁት።


ግን ይሄ ታሪክ ስለ ተከራየሁት ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየም አይደለም።
ስለንጽሕናውና ስለፀጥታውም አይደለም። ስለሰፈሩ ከተማ መሀል መገኘትም
አይደለም። ስለ አዲሷ ጎረቤቴ እትዬ እማዋይሽ ነው።


ታኅሳስ ላይ ቤቱን ቀለም አስቀብቼ፣ እቃዎቼን ሸክፌ ገባሁ።


በገባሁ ዕለት ነው እትዬ እማዋይሽን ያገኘኋት እና የተዋወቅኳት።

ቅዳሜ ነበር። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዐት ይሆናል።

እሷ፣ ፎቁን እያረፈች እንደወጣች በሚያስታውቅ ሁኔታ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለና እያለከለከች በሬ አጠገብ የሚገኘው በሯ ጋር የቤቷን ቁልፍ እያንቀጫቀጨች ስትደርስ፣ እኔ ደግሞ ውስጥ ያለውን እስካስተካክል ውጪ የተውኳቸውን ኮተቶቼን ወደ ቤት ለማስገባት ስወጣ ነው፣ ፊት ለፊት የተገጣጠምነው።

እንዳየኋት የተሰማኝ ነገር ያለቦታዋ የምትገኝ ሰው መምሰሏ ነበር።

በዕድሜ ስልሳ ቤት ትሆናለች።

ነገር ግን ሙሉ በሙሉ የሸበተው ጸጉሯ ብዙ ጊዜ ዕድሜያቸው የሄደ ሰዎች ላይ እንደማየው ስስና እንክብካቤ ያጣ አልነበረም። ዘንፋላና በሥነ-ሥርአት የተተኮሰ ነበር። አለባበሷ አሁንም በእሷ ዕድሜ ያሉ ሴቶች እንደሚዘወትሩት ሰፊ ልብስ ላይ ሌላ ሰፊ ልብስ፣ ግራጫ ቀለም ላይ ቡናማ፣ ወፍራም ሹራብ ላይ ወፍራም የአንገት ልብስ ዓይነት አልነበረም።
ደልደል ያለና ውብ ሰውነት አላት።

በልኳ ግን ሳይጠብ የተሰፋ ቆንጆና ደማቅ ቢጫ ቀሚስ፣ አጠር ካለ ሰማያዊ ክፍት ሹራብ ጋር ለብሳለች። ተረከዙ አጭር፣ ፊቱ ሹል ጥቁር ጫማ አድርጋለች። የምታምር ትንሽዬ ቡናማ ቦርሳ አንግታለች።

ደርባባ ነች። ዘንጣለች።

“እንዴት ዋልሽ ልጄ?” ስትለኝ ነው ዕድሜዋን ከዝነጣዋ ያስታረቅኩት።

“ደህና ይመስገን” አልኩኝ ፈጠን ብዬ።

“ጎረቤትሽ ነኝ… እንኳን ደህና መጣሽ… እማዋይሽ እባላለሁ”
“አመሰግናለሁ… ኤደን እባላለሁ” መለስኩላት።
“ሳናግዝሽ ገባሽ… አሁን ምን ልርዳሽ?” አለች ዐይኖቿን ተመሳቅለው
የተኮለኮሉት ውጪ የተዘረገፉ እቃዎች ላይ አሳርፋ።

“ግዴለም ብዙ አይደለም ጨርሻለሁ” አልኩ አሁንም ፈጥን ብዬ።

“በይ ስትረጋጊ ቤቴ ነይና ቡና ጠጪ” አፈር አልኩና፣

“አይ…. እሱ እንኳን ሌላ ቀን” አልኩ። እያግደረደረችኝ ከሆነ መግደርደሬ ነበር።

“ኖንሴንስ… እያግደረደርኩሽ አይደለም… ጎረቤት መተዋወቅ አለበት። ቡና
ማፍላቴ ስለማይቀር እቃሽን ቦታ ቦታ አስይዢና እንጠጣለን”

አሁን ጥያቄ አልነበረም።

ትልቅ ሰውም ስለሆነች፣ ጥያቄም ስላልነበር ምርጫ አጥቼ እሺ አልኳት።
ዐሥራ አንድ ሰዐት ገደማ ላይ የብረት በሬ ተንኳኳች።

እማዋይሽ ነበረች።

“ነያ ቡናው ደርሷል” አለችኝ።

በሬን ቆልፌ ተከትያት ቤቷ ገባሁ።

ቤቷ፣ አዲስ በተቆላ የቡና ጠረንና ለአፍንጫ በሚጥም ዕጣን ጭስ ተጨናንቃ
ተቀበለችኝ።

ረከቦትና ስኒዎቹን በዐይኔ ብፈልግ የሉም። ዕጣን ማጨሻውን ለማግኘት ብሞክር
አልቻልኩም።

ከመቀመጤ፣ “ዛሬ ገብተሽ መቼስ ምግብ አልሠራሽም” ብላ ምን የመሰለ
ፍርፍር አበላችኝ።

ጎንደር ያለችውን ባለሙያ እናቴን አስታወሰኝ።

(ይቀጥላል)

By Hiwot Emishaw


@wegoch
@wegoch
@paappii
👍4725🔥2🥰2
< "እናርግ" አለኝ እኮ፣ ያ ውሻ >

ምናለበት እሺ ብትዪው ? ምትወጂው ከሆነ ስሜቱ ለጋራ ነው ፣ አይደለም እንዴ?

< አንተ ሐይሚን አርገሀታል? ንገረኝ። >

"አድርገሀታል" ማለት? ምን አደረኳት? "

< ሒይ ! እያወክ አትገግም። >

"በድተሀታል ወይ ? ማለት ፈልገሽ ከሆነ ፣ በድቻታለሁ። ብድትድት ነው ያረኳት። ካንቺ ጓደኞች ያልበዳሁት የለም። "

< እህ ? ውሻ! ውሻ ነህ ።>

አዎ ነኝ ! ዉው ዉው ኣዉዉዉዉዉ ። ሀያትንም በድቻታለሁ።

ሀያት ነች ያስተዋወቀችን። ሀያት የጥቁር ቆንጆ ፣ እንደ እሳት ቅልብልብ ፈጣን ውልብልብ እጅግ ብልህና በትምህርትም ጎበዝ ተማሪ የነበረች ናት። ኤለመንተሪ ከሀያት ጋር ስንማር ጥያቄ ና መልስ ውድድር እኔና እሷ ከፍላችንን እየወከልን ዞረናል። ሀይስኩል እንደገባን ሀያት ናት ከዚህችኛዋ አለም ጋር ያስተዋወቀችን። ከአስረኛ ክፍል በሁዋላ ሀያት የት እንደገባች አናውቅም። እኔና አለም ግን አስር አመት ሆነን። በጓደኝነት። ንፁህ የሚባለው አይነት ጓደኝነት።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

አለም

< ወዬ >

" አለም የሚል ስም ይዘሽ እንዴት መንፈሳዊት አማኝ ሆንሽ ? "

< አንተማ ለይቶልሀል። >

ሁሌም ከፍቅረኞቿ ምትለያየው የወሲብ ጥያቄ ሲያቀርቡላት ነው። እሷ "ከጋብቻ በሁዋላ" ትላቸዋለች። እነሱ ጥለዋት ሲሄዱ መጥታ እኔ ላይ ታለቅስብኛለች። ይበዳኛል ብላ ሰግታ አታውቅም።

እኔ ብበዳሽስ ? እላታለሁ።

ሁሌም < ሐይሚን አርገሀታል? እስካሁን ስንት ሴት አወጣህ? > ትለኛለች።

"ስንቷን ሴት ስንት ስንት ጊዜ እንዳወጣሁ ልንገርሽ ? ሐይሚን ...ሐያትን ደሞ እእእ ?"

< ኡህ! አንተስ ባልገሀል >

ትለኛለች።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

በስጋ እናትም አባትም። ቤተሰቦቿ አሳዳጊዎቿ ናቸው። እና እኛ። እኛ ማለት እኔና ሌላ ማላውቃቸው ጓደኞቿ።

< አንተ ቤተሰብ ስላለህ እድለኛ ነህ > ትለኛለች።

" እኔ ቤተሰብ እዳ ነው " እላታለሁ።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

ያኔ ሐያት ከእሷ ጋር ካስተዋወቀችን ማግስት ወደኔ ክላስ እየተጎተተች መጣች። ፀይም ነበረች ግን አመዳም። ፀጉሯ ረጅም ነው፣ ግን ደረቅ ነው። ጥቁር ሻርፕ አንገቷ ላይ ጣል ታደርጋለች ፣ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም። እናም ያግባባን ብቸኛ ነገር እኔ ብልህ እንደሆንኩ ማሠቧ ና እሷ ብርቱ ስለሆነች ከእሷ ጋር እንደምስማማ ስለምታስብ ነው።

እኔስ ? እኔ ትምህርት ላይ እየቀነስኩ አሪፍ መስሎ መታየት ላይ እየበረታሁ ነበረ። ቀንደኛ ቀልደኛ ሚባሉት ተማሪዎችን ጎራ ተቀላቀልኩ። ሁሉም ጓደኞቼ ድንግል ሆነው ሳሉ ቀድሜ ገርልፍሬንድ ያዝኩ፣ ቆንጆ ሴት፣ ከሌላ ክፍል፣ ሐይማኖትን ። በርግጥ ኤለመንተሪ እያለሁ የሔርሜላን አንገት ስሜያለሁ። ከነሱ መፍጠኔ ለእኔ አይገርመኝም።

እና ይህቺ አለም < ትምሕርትህ ይበጅሀል። እሷን ተዋት። ገና ልጅ ነህ። ደግሞም ቆንጆ አይደለችም።> ትለኝ ነበረ።

ግን ሁለታችንም በእድሜ እኩያሞች ነን። እሷን መካሪ እኔን ተመካሪ ያደረገን እሷን ለይቶ የመከራት ኑሮ ነው።

ኑሮ ያስተማራትን ትምህርት በደንብ ይዛዋለች። ፈተናውንም አልፋዋለች። አሁን ዘናጭ ነች። ፀይም መልኳም ፀጉሯም ወዝ ኖሮታል። ለስራ ሌላ ሀገር የሄደች ጊዜ ገንዘብ እኔ አበድራት ነበረ። ሁለት ጊዜ ሌባ ሙልጭ አድርጎ ዘርፏታል። አሁን እኔ ገንዘብ ሲቸግረኝ ከእሷ ነው የምበደረው። የወር ገቢዋ ከእኔ የወር ደመወዝ አስር እጥፍ ነው።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

አስረኛ ክፍል ተዋወቅን ፣ አስር አመት አብረን አሳለፍን ። አሁን ልታገባ ነው። ሰርጓ በቅርብ ነው።

<አንተ መቼ ነው ምታገባው ? >

ብዙ ፍቅረኞች አሉኝ ። የቷን ላግባ?

< ባለጌ

ሐይሚን አሁን ብታገኛትስ ? >

አስር አመት ሙሉ ሐይሚን ያልረሳሻት ለምንድን ነው ?

< ሐይሚን አይደለም ያልረሳሁት። ያንን የግቢውን ቆንጆ፣ ብልህና ትንሽዬ ልጅን ልረሳው ያልቻልኩት። የአስራስድስት አመቱን ያንን ናሁ መሆን እፈልግ ነበር። አሁን ላይ ግን እዚህ ሆነን ደግሜ እሱ ራሱን ሆኖ ማየት እመኛለሁ >

" እመኚኝ። እኔ ምንም ከስሬ አላውቅም። እናም የራሴን መንገድ አገኛለሁ። ሚስትም አገባለሁ።

አንቺ ትንሽ ቀደም ብለሽ ሒጂ። አግቢ። እኔ ባንቺ መንገድ አልሄድምና። መልካም መንገድ። መልካም ጋብቻ።

ለባልሽ የምነግረው ነገር አለኝ ፦ " እሷን እቅፌ ላይ ለብዙ ቀን እንዳሳደርኳትና ከእሷ ገላ ላይ የወሰድኩት ምንም ነገር እንደሌለ ነው።

ስላልፈለኩ። ወይ ፈልጌ ስላልቻልኩ። ወይ ችዬም ታማኝ ሆኜ ይሆናል።

እኔ ባለቤቷ ነኝ። አሁን አንተ ባሏ ልትሆን ነው። ይትባረክ"


By Nahu senay

@wegoch
@wegoch
@paappii
👍44🤔147🥰7👎6😁5🔥3👏2😱2
የሄደበትን የመጨረሻ ቀን አስባለሁ።

ኩራቱን ተገፎ ሀፍረትን ተከናንቦ እርቃኑን እንደቆመ ሠው ዐይኔን ሽሽት አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬት እያየ "እሜትዬ በድዬሻለሁ…" ያለበትን ቃና እሰማለሁ። ምህረት ፍለጋ ለይቅርታ አልመጣም ነበር። አንዳንድ ሀጥያቶች ስርየት የላቸውም፤ ስለአንዳንድ በደሎቻችን ከራሳችንም እርቅ አይኖረንም። ለዋለው ክህደት ይቅርን አልፈለገምና የኔ ይቅር ማለት ትርጉም አልነበረውም። የኔ ምህረት መስጠት ኩራትና ክብሩን ከወደቀበት ሊያነሳለት አቅም አልነበረውም። አንገቱን ደፍቶ በገባበት በር አንገቱን ደፍቶ ሲወጣ ቃል አልወጣኝም። አልተከተልኩትም በዐይኔ አልሸኘሁትም። ልቤ መመለሱን ቢሻ ከበደሉ ሊያልቀው ግን አልተቻለውም። በሰው ለውጦሻል ተይው ይሂድ አለ፡፡ ተውኩት፣ ሄደ…አልተመለሠም ።

ዘመናቶቼ መኸል ግን እጠብቀው ነበር። አንዱን ቀን ይመጣል ብዬ በር በሩን አማትሬያለሁ። ወሬውን ፍለጋ ጆሮዎቼ እልፍ ጊዜ ቆመው የደጁን ድምፅ ሲቃርሙ ኖረዋል። ብዙ ጠብቀዋል፤ ለማንም ሳልነግር በደሉን ውጫለሁ። ባሻዬ ከዳኝ ሳልል ይቅር ብዬ ነበር። ፍለጋ ባልወጣ የት ሄደ ባልል በልቤ በእየዕለቱ 'አንተ ትሻላለህ፤ ተመለስ ግድ የለም' እል ነበር።

እወደው ነበር፤ ኩራት በሸበበው ፈገግታ ቢደበቅም ቅሉ ሳየው ልቤ የፈካ ቀለምን ትፈነጥቅ ነበር። እንደነዛ የመጀመሪያ ቀናት ጠጁን እየተጎነጨ ጓዳውን ሲያማትር በዐይኑ ሲፈልገኝ ትንሿ ልቤ በመጋረጃ ተከልላ እያየች ትደልቅ እንደነበረው፤ እንዲያ…እንዲያ እወደው ነበር። እነዛ ጊዜ ሸምኗቸው ጋቢ ሆነው የለበሳቸው የጥጥ ማጎች ስለሱ እያሠብኩ ሳሾራቸው፤ ተበጥሰው እንደተንከባለሉ ስንት ወድቀው ስንት እንደተነሱ፤ ስንት እንዝርት እንደሰበሩ አያውቅም፤ አልነገርኩትም ለፍቅር ሰነፍ ነበርኩ ።

By Beza Wit

@wegoch
@wegoch
@paappii
13👍8🔥4🥰1😢1
አገባሁ...ወለድኩ...ደገምኩ...ሠለስኩ:: እሱን እያፈቀርኩ ከወንድሙ ሦስት ልጆች ወለድኩ:: እሱን እየተመኘው ወንድሙን አገባሁ:: ካሳለፍናቸው 3 የUniversity ጓደኝነት አመታት በኃላ እንደተመረቅን ነበር ላገኘው እንደምፈልግና ብቻውን እንዲመጣ የነገርኩት ገና ተደላድሎ ከመቀመጡ ነው " አፈቅርሀለው" ያልኩት ::ሳቀ በሀይል ሳቀ
"አንቺ ያምሻል እንዴ ለቁም ነገር ነው ምፈልግህ ስትይኝኮ ምን ሆነች ብዬ ስንት ነገር ነው ጥዬ የመጣሁት ትቀልጃለሻ አንቺ ሆሆ " አየሁት .. እነዛ መጀመሪያ ካየዋቸው ቅፅበት ጀምሮ ራሴን ያሳጡኝን አይኖቹን ትኩር ብዬ አየዋቸው ::ሚያረገው እየጠፋው ሁሌ እንደሚጠራኝ
" ቃሊ የምርሽን ነው እንዴ "
"አዎ አፈቅርሀለው" ፊቱን በአንዴ ወደ ግራ የተገባ ፊት ቀይሮ " ከመቼ ጀምሮ ቃሊ?"
"ከመጀመሪያው የሁለተኛ አመት የትምርት ቀናችን ከማክሰኞ ከመስከረም 22 ጀምሮ" ደነገጠ " ቃሊ please አታሹፊብኝ " ፊቱ ሲቀላ እየታወቀኝ መጣ
"ምንም እንድትለኝ አይደለም ብንጋባ ብታፈቅረኝ ምንምን በደስታ ልሞትብህ ስለምችል አላቅም ግን እህቴ ነሽ ምናምን እንዳትለኝ ደሞ" መንተባተብ ጀመርኩ ::
"ቃሊ"
"ወዬ" ልቤ በፍጥነት ስትመታ ይታወቀኛል
"ኤላኮ ያፈቅርሻል" ፊቱ ማላቀውን እሱን ሆነብኝ..ውስጤ ሲፈረከስ ተሰማኝ ኤላ ማለት? ኤላ የሱ ወንድም? ማለት መንታ ወንድሙ ኤላ ? ኤላ ጓደኛዬ? ኤላ ኤላ ውስጤ ተተራመሰ.....በመልክም በአመልም ምንም አለመመሣሠላቸው ሲገርመኝ ነበር ሶስቱን የጓደኝነት አመታት ያሳለፍነው :: ሁሌም አብረን ነበርን እሱም..ኤላም...እኔም :: በሁለት መንታ ወንድማማቾች መሀል ያለው ብቸኛ ጓደኛቸው በመሆኔ ጊቢ ውስጥ እንደኔ ደስተኛ ሰውም የነበረ መኖሩን እኔንጃ እኔን መሀል አርገው ሲተራረቡ መስማት...ሲበሻሸቁ...አንዳቸው እንዳቸው ላይ ሲቀልዱ ...እጄን የኔው ተፈቃሪ እንደቀልድ በቦክስ ሲመታኝ ኤላ ሲቆጣው...ተሸክመውኝ ሲሯሯጡ ላየን 3 መንታዎች እንጂ ማልዛመዳቸው መሆኔን ማንም አይጠረጥርም አንዳንዶቹ ደሞ የማንኛው ናት እንደሚሉም አቃለው :: የጊቢው ሴቶች ደሞ ኤላን ይወዱት ስለነበር እንዳጣብሳቸው ሚወተውቱት እኔን ነው ኤላ ግን ወይ ፍንክች ስለሚል ማጣበሱ አልተሳካልኝም ነበር :: ሲፈጥረኝ ከሴት አትዋደጂ ያለኝ ይመስል ከልጅነቴ ጀምሮ ሴት ጓደኛ ኖሮኝ አያውቅም ጊቢ ገብቼም የመጀመሪያውን freshman አመት ከማንም ጋር አልግባባም ነበር ከዛ ግን ሁለተኛ አመት ላይ ምንማረውን ትምርት መርጠን ስንመደብ እነሱን አገኘው ለዛም ነበር በጓደኝነታችን ደስተኛ የነበርኩት :: ከ6ኪሎ ጊቢ በታች ያሉ ማሚ ቤቶች ሄደን ምሳ ስንበላ በእጄ ከአንድ ጉርሻ በላይ ስጎርስ አላስታውስም በሁለቱ የፉክክር ጉርሻ ነበር ጠግቤ ምነሣው በዛ ላይ ሳየው ገና ልቤ የደነገጠለት ልጅ ጓደኛ ሆኜ ስስቅ መዋል ..ደስታ ማለት እኔ ነበርኩ:: "ጉድና ጅራት ወደ ኃላ ነው" አሉ....ያን ቀን "ኤላኮ ያፈቅርሻል " ሲለኝ ጉሮሮዬም ልቤም አይምሮዬም ደረቀብኝ ጎኔ ያለውን ግማሽ ኮካ አንስቼ ጨለጥኩት ::
"ኤላ የቱ" አይኖቼ ሲፈጡ ይታወቀኛል
"ቃሊ ኤላ የኛ ነዋ "ፊቱ የማላቀው ቋንቋ ፅሁፍ ሆነብኝ አየዋለው አይገባኝም ::
"ከመቼ ጀምሮ?" እሱ እንዳለኝ እኔም አልኩት ማወቄ ይቀይረው ያለ ነገር ይመስል
"ካየሽ ቀን ጀምሮ ቃሊ ትዝ ይልሻል class እንደጀመርን ካፌ አጊኝተንሽ ብቻሽን ከምትበዪ ከኛ ጋር ምሳ አብረን እንብላ ብዬሽ አብረሽን የዋልሽ ቀን " እንዴት እረሳዋለው ያን ቀን በአይን ካፈቀርኩት ሰውጋር አምላክ አገናኘኝ ብዬ በደስታ ስፈነድቅ ነበር የነጋው :: ፀጥ ብዬ ሳየው ወሬውን ቀጠለ "ያን ቀን ማለት ኤላ ካላስተዋወከኝ ብሎ ሲለምነኝ ነበር ታውቂያለሽ ቃሊ ኤላን ከማህፀን ጀምሮ ሳውቀው ከአፉ ወቶ ሚያውቀው የሴት ስም ያንቺ ብቻ ነበር :: ቃሊ ኤላ አንቺን ስለማግባት ካንቺ ስለመውለድ ብቻ ነውኮ ሚያልመው ደሞ እሱም ከዛሬ ነገ እነግራታለው እያለ ነውኮ የተመረቅነው ቃሊ ኤላን ያዢው ወንድሜ እስከነፍሱ የሚያፈቅራት ሴት ታፈቅረኛለች ብሎ ማሰቡ ለኔም በሽታ ነው ቃሊ ደና ዋይ ኤላን ያዢው" ብሎኝ ነበር በተቀመጥኩበት ጥሎኝ የሄደው "ኤላን ያዢው" ይሄን ነበር ያለኝ :: .....እኔም ኤላን በእጄ በልቤ እሱን ይዤ ይኸው ሶስተኛ ልጃችንን ወለድን:: .....ኤላ ህልሙን ኖረ እሺ እኔስ?? የሱ ህልም ማስፈጸሚያ ልሆን ነበር የተፈጠርኩት? ያፈቀሩትን ስለማግኘት ኤላ ያሟላው እኔ ያጎደልኩት መስፈርትስ ምን ነበር??? ልጆቼስ አጎታቸውን በልቤ አግብቼ እንደምኖር ያወቁ እንደሆነ እንዴት ይዳኙኝ ይሆን ? እንጃ....ሁሉም ያፈቀረውን አያገባም..ልክ እንደኔ::


By ቃል_ኪዳን


@wegoch
@wegoch
@paappii
👍57😢3217👎2🔥2🤔1
God,have mercy! This woman is so obsessed with her life. With her home and her family.

በጠዋት ትነሳለች ቁርስ ትሰራለች ቤተሰቦቿን ታበላለች ታጠጣለች መጥገባቸውን ታረጋግጣለች ከዛም ወደየሚሄዱበት ትሸኛቸዋለች። ቀጥላ ወደቤቷ ጽዳት ፣ ወደእንጀራ ጋገራ ፣ ምሳ ማሰናዳት ወዘተ.... አቤት ያላት ፅናት! ለጉድ ነው! ቤት ጠርጋ ወልውላ አጫጭሳ ልብሶች አጥባ እቃዎቹ ታጥበው ደርቀው በየቦታቸው ተደርድረው።
ወጡ ችክን ብሎ ተሰርቶ፣ ቡናው ትክን ብሎ ፈልቶ እጣኑ እየጤሰ ምሳ 'ሳት ይደርሳል። በር በሩን እያየች የቤተሰቧን መምጣት ትጠብቃለች ሲመጡላት በሚገባ ታስተናግዳቸዋለች።

በፈገግታ እና በምግብ ከፈወሰቻቸው በኋላ መልሰው ወደየሩጫቸው! "አመሠግናለሁ"ን እንኳን ሳትጠብቅ በሳቅ በፈገግታ ሸኝታ ወደቤቷ! የተበላበትን የተጠጣበትን እቃ አጥባ፣ የተዝረከረከውን ቤት አበጃጅታ ስታበቃ ደግሞ ለእራት ዝግጅት ጉድ-ጉድታዋን ትጀምራለች። ጣፋጭ ምግብ አብስላ፣ ሙቅ ሾርባ ሰርታ ቤቷን አሟሙቃ ትጠብቃለች። ወዳሞቀችው ጎጆ ይሰበሰባሉ ከእጇ ፍሬም ይበላሉ።

ይሔ ብቻ አይደለም she is psychiatrist ,she is economist, she is event organizer, she is expert in negotiation and an incredible socialist!

ይህች ሴት እናቴ ናት❤️

ምኞትሽ ምንድነው ብባል " እንደሷ መሆን" እላለው።


By Magi

@wegoch
@wegoch
@paappii
154👍35🥰11🔥3👏1😢1
የምወደው ልጅ ነበር ። እርጋታው ህልሙ መልኩ ሁኔታውን
እወደዋለሁ ስህተቱን ድክመቱን ሳይቀር ነበር የምታገሰው ።

ብጥር ...ብጥር... ከኔ ጋ ማቆየት አልቻልኩም ።

ጊዜ ሄደ ...

እኔም ሄድኩኝ

ሌላ መስመር ሌላ ኑሮ ሌላ ጠዓም አየሁኝ እሱ
ዘግይቶ ወደ ምፈልገው መንገድ መጣ

ዳር ዳር አለ እንዳልገባኝ ሆንኩኝ እብረን እንድንሆን ጠየቀኝ ..ዋጋሽ ገብቶኛል ወድጄሻለሁ አለኝ ።

አልታበይኩም አልጎረርኩም ሰነፍ ነው ቀድሞ ደርሶ ባረፈደ የሚያሾፈው ። ብስለት የሚለካው የሆነልን ሲመስለን በያዝነው አቋም እና ሁኔታ ነው ።

በትህትና አልችልም አልኩት ።

Timing is every thing ፀሎቴ ውስጥ ህልሜ ውስጥ ቅዠቴ ውስጥ ማሳካት የምፈለገው ውስጥ እምይዘው አቋም ውስጥ እሱ ነበር ። ጊዜ ሁኔታ አጋጣሚ ተደራረበ እና አንዱም ውስጥ ጠፋ !!

ምንም ስላላዋጣ ግዜ ልቤ ውስጥ የተወለደውን ፍቅር አደብዝዞት ነበር ። ልቤ ውስጥ የተከማቸውን ፍቅር ስላልወደደው ፍቅሬን ፊት ነስቼው በግዜ ብዛት ተነነ ።

ብቻ መወደድ ከብዶኝ ስለነበር ሳስታውሰው እረፍት አይሰማኝም ነበር ። እረፍት የሌለው ፍቅር ምኑን ፍቅር ነው ??

ናፍቆኝ ጓጉቼ ሳገኘው አይኑ ለኔ ስሜት አልባ እንደሆነ ስለሚነግረኝ ናፍቆቴ ወደ ድብርት ይቀየራል ።

የሚለኝን ያደረገውን የሆነውን ሁኔታውን ትርጉም አየሰጠው ስቀምር የማድር እንደነበርኩ እኔን ካልሆነ አይገባውም !!

ዛሬ ሁኔታሽ አንቺነትሽ ሁሉ ትርጉም ሰጠኝ አብረን እንሁን አለኝ ። ዘግይቶ ነበር Timing is every thing

እንደማይሆን እያወኩ ፍላጎት እንዳለኝ ምልክት ሰጥቼ አልበድለውም !!

" አልችልም" አልኩት

ቁርጣችንን አልነግር እያሉ እንደሚበድሉን መሆን አልፈለኩም ተፈላጊ የመሆኔን እርሃብ ለማስታገስ ወለም ዘለም እያልኩ አልበድለውም

በትህትና " አልችልም ሌላ የህወት መንገድ ላይ ነኝ " አልኩት ። እየመከርኩ አልተመፃደኩም ። መልካሙን ሁሉ እንዲገጥመው ግን በልቤ ተመኝቼለታለሁ ።

ትክክለኛ ነገር ትክክለኛ የሚያደርገው timing ነው !
timing is every thing እንዲሉ አበው!!

By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
👍7527👏6🔥4🥰1
አልዋሸሁም

==============

22 ማዞሪያ፡፡

መንገዱ በሰው ተወሯል፡፡

ለታክሲ በተሰለፉ መአት ሰዎች፣ ከጣሪያ በላይ እየጮሁ ይሄንንም ያንንም በሚሸጡ ነጋዴዎች፣ አጎንብሰው ከነጋዴዎቹ ጋር በሚከራከሩ ገዢዎች፣ በሁሉም አቅጣጫ በቀስታ፣ ቶሎ ቶሎ በሚራመዱ እግረኞች፡፡ ቆመው ስልክ በሚያወሩ ሰዎች፡፡

እኔስ ምን እያደረግሁ ነው?

እየሮጥኩ ነው፡፡ በፍጥነት፡፡ ጠና ካለች ሴትዮ ነጥቄ የያዝሁትን ቅንጡ ቦርሳ በቀኝ እጄ ደረቴ ላይ አጣብቄ ይዤ በግራ እጄ አየሩን እየቀዘፍኩ እሮጣለሁ፡፡

ሁኔታዋ ደህና ብር እንደያዘች ነግሮኛል፡፡

ልክ ኦሎምፒክ ላይ ቀነኒሳ የሐይሌን መቅረት ባለማመን አስሬ ወደ ኋላ እየተገላመጠ እንዳየው አንድ ሁለቴ ዞር ብዬ የተከተለኝ ሰው አለመኖሩን እያየሁ ነው የምሮጠው፡፡

ቦርሳዋን የነጠቅኳት ሴት እንጥሏ እስኪቃጠል እየጮኸች ነበር፡፡

አንድ ወጠምሻ እየተከተለኝ ነበር፡፡ በጎ አድራጎት መሆኑ ነው፡፡ እኔ የምለው…ሰዉ ግን ለምን የራሱን ኑሮ አይኖርም…? ምነው በየጎዳናው የበጎ ሰው ሽልማት ካልሸለማችሁኝ ባዩ በዛ፡፡ ሆ!

ዞር አልኩ፡፡
የለም፡፡
ኡፎይ፡፡

ወያላ ‹‹ፒያሳ በላዳ!›› እያለ ከሚጮህላቸው ተደርድረውና በር ከፍተው ከሚጠብቁ ላዳዎች አንዱ ጋር ስደርስ የሁዋላ ወንበሩ ላይ ገብቼ ዘ---ፍ እንዳልኩኝ እዛው አገኘኋት፡፡

ቦርሳዋን የወሰድኩባት ሴትዮ አይደለችም፡፡ የፊዚክስ ህግ እዚህ ቀድማኝ እንድትገኝ አይፈቅድላትም፡፡

ግን እሷ ብትሆን ይሻለኝ ነበር፡፡

ሳሮን ነበረች፡፡ ሳሮን ገላልቻ፡፡ የሃይስኩል ጓደኛዬ፡፡ የሃይስኩል ፎንቃዬ፡፡ ከአስር ዐመት በላይ ያላየኋት፣ ዛሬም በሚያፈዝ ሁኔታ የምታምረው ሳሮን፡፡

በቁልቢው! ካልጠፋ ቀን፣ ካልጠፋ ሰዐት፣ ካልጠፋ ቦታ ዛሬ፣ እዚህ፣ እንዲህ ላግኛት?

የሰረቅኩትን ቦርሳ ኪሴ ውስጥ አጣጥፌ አስቀምጬው የነበረ ጥቁርና ከውጪ የማያሳይ ፌስታል ውስጥ በፍጥነት ጎሰርኩና ፊት ለፊት ገጠምኳት፡፡

ሳቀች፡፡

‹‹ኤርሚዬ! እውነት አንተ ነህ?›› ብላ አቀፈችኝ፡፡
ስታምር፡፡ መአዛዋ ሲጥም፡፡
አዬ መከራዬ!

ደማቅና ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋውጠንና ላዳው ሞልቶ መንገድ ስንጀምር ዛሬ ስላለንበት ሁኔታ ማውራት ጀመርን፡፡

‹‹እሺ…ሳሮንዬ እንደተመኘሽው አሪፍ ዶክተር ሆንሽ…?›› አልኳት ፌስታሉን ጠበቅ አድርጌ እየያዝኩ፡፡

በጣም እንዳላበኝ ያስተዋለች አትመስልም፡፡ ምናልባት ከረጅም ጊዜ በኋላ በድንገት በመገናኘታችን የደነገጥኩት መስሏት ይሆናል፡፡

‹‹ሃሃ…አዎ…ጎንደር ዩኒቨርስቲ ህክምና ተምሬ ዶክተር ሆኜልሃለሁ›› አለች ያንን የሚያምር ፈገግታዋን ይበልጥ አድምቃ፡፡

ሆኜልሃለሁ፡፡ ግራ እጇን የጋብቻ ወይ የቃልኪዳን ቀለበት ለማግኘት በአይኖቼ ፈተሸኩ፡፡

ባዶ፡፡
ልቤ ቀለጠ፡፡ የባሰ አላበኝ፡፡

ሹፌሩ ጋቢና የተቀመጠውን ተሳፋሪ ሂሳብ ሰብሳቢ አድርጎ እንደሾመ ቶሎ ብዬ ብር አወጣሁና የእሷንም ከፈልኩ፡፡ ሳትግደረደር ፈገግታዋን ለገሰችኝ፡፡

መልስ ተቀብዬ አየት አደረግኋትና ልክ እንደእሷ ፈገግ ለማለት እየጣርኩ፣

‹‹ጠብቄ ነበር፡፡ ትዝ ይለኛል ባይሎጂ ላብ ስንገባ እነዚያን ምስኪን እንቁራሪቶች እየሳቅሽ ስትሰነጣጥቂያቸው፡፡ ሌሎቻችን ላለማስመለስ ስንታገል አንቺ ግን ደስ ይልሽ ነበር …›› አልኩ፡፡

በጣም ሳቀችና ‹‹አንተስ ኤርሚዬ? ሁሌ እንደምልህ ህግ አጠናህ አይደል?›› አለችኝ፡፡

ጥያቄዋ የጥፊ ያህል አመመኝ፡፡

እዚህ ላዳ ውስጥ ዘልዬ ከመግባቴ በፊት፣ እሷን ከማግኘቴ በፊት የተፈጠረው ነገር ሁሉ ልክ እኔ ሳልሆን ሌላ ሰው ሲያደርገው ቆሜ የታዘብኩ ይመስል ትእይንቱ በዐይኔ ላይ ዞረ፡፡

ይህቺ የልጅነት ህልምና ተስፋዬን የምታውቅ፣ ግን ደግሞ ያለፉት አስር አመታት እንዴት አድርገው ተስፋዬንም ህልሜን እንደቀሙት የማታውቅ ከድሮ ሕይወቴ በድንገት ተወንጭፋ የመጣች ልጅ ጥያቄዋ አሳመመኝ፡፡

ስሰርቅ ዛሬ የመጀመሪያዬ ሆኖ አይደለም፡፡

ስርቆትን መቁጠር እስካቆም፣ የጥፋተኝነት ስሜት ሽው እንኳን እስካይለኝ ለአመታት ሰልጥኜበታለሁ፡፡

አሁን ግን፣ ያኔ ማንም ሳያየኝ በፊት አይታኝ፣ ‹‹ኤርሚዬ አንተ ንግግርና ክርክር ላይ…ቋንቋ ላይ ጎበዝ ስለሆንክ አሪፍ ጠበቃ ወይ ዳኛ ይወጣሃል፡፡ ህግ ነው ማጥናት ያለብህ›› ካለችኝ ልጅ ጋር ተቀምጨ የሆንኩትን ነገር ሳስበው ሃፍረት ወረረኝ፡፡

ቢሆንም ፈገግ አልኩና ‹‹ አዎ…ህግ አካባቢ ነኝ›› አልኳት፡፡

መልሴን አጢኖ ለመረመረው አልዋሸኋትም፡፡

By Hiwot Emishaw

@wegoch
@wegoch
@paappii
😁72👍5614👏9🥰3😢3🤬1
የእኛ ሰፈር ስለት ርዕሱ ነው:-

አንዴ እንደማመጥ እንደማመጥ አሉ የሰፈሩ አድባር ሽማግሌ።ሁሉም የሰፈር ሰው ፀጥ አለ።
እህህ እህህ ያው በየ አመቱ እንደምናደርገው መጠጡ ተአቅማችን በላይ ሆኖ ታለ አቅማችን ከርሞ ማቅረብ የማንችለውን ስለት እንዳንሳል ይሄኔ ወደ ሞቅታ እየገባን እያለ በየተራ እየተነሳን ስለታችን እንሳል ወንዶች በጭብጨባ ሴቶች በእልልታ ቸር እንመኛለን።

እሺ ቀጥይ እሟሃይ አስረበብ:-

#እማሆይ:-የዛሬ አመት ሁላችንም ከቁጥር ሳንጎድል እንዲሁ እንዳለን በሰላም ከደረስነ አስር እንጀራ

እልልል ጨብጨብጨብ

አጉረምራሚው ጀማ:-አይ እሟሃይ አልሳልም አይሉም እንዴ ከቁጥር ሳንጎድል የሚሉ አሁን በለጠ ሊከርም ነው ኤዲሱና ትቪው እያጣደፈው እስከ ተሳስም በባጄ

ቀጥል አቶ አስማማው።

#አስማማው:-የዛሬ አመት ጦርነቱ አቁሞ የሰላም አየር ከተነፈስነ ሁለት ካሳ ቢራ

እልልል ጨብጨብጨብ

አጉረምራሚው ጀማ:-ልጁ ሚኒሻ ስለሆነ ነው እንጂ አሁን አስሜ የአገሩ ሰላም አሳስቦት አሄሄ ስለቱ ቢደርስስ የሁለት ካሳ ቢራ የት ሊያገኝ ነው ቂቂቂ የአረቄ እዳ አለበት እያለች አስካለ ስትፈልገው አደል የምትውል ክክክ

ወዘሮ ብርቄ ቀጥይ:-
#ብርቄ:-አዲሳባ ያለችው ልጄ ቤቷ እስከ ከርሞ ካልፈረሰ አንድ ዶሮ

እልልል ጨብጨብጨብ

አጉረምራሚው ጀማ:-ያቺ እንግዳ ሲሄድባት ፊቷ የማይፈታው ናት?አይደለም የእሷማ ፈርሶባት አረብሀገር ሄዳለይ አሉ የትንሽቱን ነው እንጂ

አቶ ዘነበ ቀጥል:-
#ዘነበ:-ጅማ ያለው ልጄ እስከ ዛሬ አመት ወረሞ ከሆነ አንድ ጠቦት በግ አስገባለሁ

እልልል ጨብጨብጨብ

አጉረምራሚው ጀማ:-አቶ ዘነበ ደሞ ወጉ ሁሉ ግራ ነው ባለፈው መጥቶ እያለ ሀጠራው አካምጅርታ እያለ አልነበር ተያ በላይማ ከወረመ ይኦንግበታል ኪኪኪ ኧረ እንዳይሰማ ቀስ በሉ

ቀጥል ልጅ ኩራባቸው:-

#ኩራ:-የዛሬ አመት ከመካከላችን ስድስት ሰው ብቻ ከሞ ተ አንድ በግና አራት ካሳ ቢራ

የሰፈሩ ሰው:- ኤድያ እንደው ይሄ ደግሞ አንድ ቀን ከአፉ ደና ነገር ሳይወጣው እንዲህ እንዳለ አረጀ

ምኑ ሟርተኛ ነው በእንድማጣው

እናቱ በአራስነቱ ጥላው ወጥታ ነው አሉ እንዲህ ቡኖ የቀረ

አይ ኩራ አረቄ ከቀመሰ በቃ አፉ ድሮን ነው ጥሩ ነገር አይወጣውም

ቆይ እንጂ ልጁን ውሻ አታርጉት እውነቱን ነውኮ

ሲጀመር አምና የተሳለውን ሳያመጣ ለምን እድል ሰጣችሁት አስወጡት

ሂድ ተኛ ሂድ ተኛ አስወጡት ይሄንን ጅል


By Koan AD


@wegoch
@wegoch
@paappii
😁54👍3613🥰1
ነገረ ጠንቋይ. . .

ባልና ሚስት ሶስት ልጆች ወለዱ። ሶስቱም ባልጩት የመሰሉ ጥቁር ነበሩ። ቢቸግራቸው መፍትሔ ፍለጋ ጠንቋይ ቤት ሄዱና ችግራቸውን ነገሩ። ቀይ ልጅ መውለድ ነው ፍላጎታችን አሉት።

ጠንቋዩም "አክራብ አክራብ ኩርማንኩር ወዘተመረ ለቀጨነ" አለና "የምላችሁን ካደረጋችሁ ቀይ ልጅ ለመውለድ ቀላል ነው የናንተ መፍትሔው" አላቸው። "ምን እናድርግ?" አሉት።

"ይኸውላችሁ፣ ስትዳከሉ አቶ ባል የቸንቸሎህን ጫፍ ጫፉን ብቻ አስገባ። ከዚያ የሚወለደው ልጅ ቀይ ነው የሚሆነው" አለ አቶ ጠንቋይ። ባልና ሚስት አመስግነው፣ እጅ ስመውና ከፍለው ወደቤታቸው ሄዱ።

ማታ ላይ ስራ ተጀመረ። ባል በታዘዘው መሠረት በጫፍ በጫፉ 🙈 መደከል ጀመረ! (ቱ! ለኔ)

ሚስት በመሀል "ውዴ!" አለች

ባል "ወዬ!"

ሚስት "ልጁን ትንሽ ብናጠይመውስ?"

ባል 😊😊 ግማሽ ግማሹን ሰደደ (🙈🙈🙈)

ከደቂቃ በኋላ ሚስት አሁንም "ማሬ!"

ባል "ወዬ!"

ሚስት "እኔ የምልህ. . . ልጅ አይደለ? ቢጠቁር ምን ይሆናል?"

* * *

By Gemechu merera fana


@wegoch
@wegoch
@paappii
😁91👍29👎202
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (Leul Mekonnen)
እናንተ የምወድዳችኹ ፤
ስነ-ፅሁፍን የምትወድዱ ፤
የግጥም ነፍስ ያላችኹ ፤
ወንድሞቼ ፤ እህቶቼ ፤ ወዳጆቼ ፤ ታላላቆቼ እና በደስታዬ ደስ የሚላችኹ የዘመን ተጋሪዎቼ ኹሉ ፤ ይቺን የመጀመሪያ ስራዬን ቅድሚያ ገዝታችሁ ፤ ከጓዳ ወደ አደባባይ እንድትሸኙልኝ ስል ፤ የተወደደ የወዳጅነት ግብዣዬን እጋብዛችዃለሁ ።

ከወዲኹ ...
እጅግ እጅግ አመሰግናችዃለሁኝ
ኑሩልኝ !
ቴዎድሮስ ካሳ

____

የመፅሐፍ ቅድመ ሽያጭ ማስታወቂያ
Reserve yours now—it's on pre-order!

ርዕስ /Title - የዱር አበባ / Wild Flower
ዘርፍ / Genres - ስነ-ግጥም /Poetry
ዋጋ/ price - 300 ብር/ birr

የባንክ ቁጥር / Bank Accounts :
ቴዎድሮስ ካሳው አስረሴ
Tewodros Kassaw Asresse
ንግድ ባንክ / CBE - 1000360039847 ወይም 1000292025185 (ናትናኤል እሸቱ)
አዋሽ ባንክ /Awash Bank - 01320885596200
ሲቢኢ ብር / CBE Birr - 0972338625
ቴሌብር/ Tellebirr - 0972338625

[ ማሳሰብያ : ዃላ ለማስታወሻ ይረዳኝ ዘንድ Screenshot አንስታችሁ በውስጥ በሜሴንጀሬ አልያም በቴሌግራም አድራሻዬ @Poet_tedi መላኩን እንዳትረሱት ይሁን ።]
👍191🥰1
ይኸውልህ ሉሌ ፤ ለአንዳንድ ስራዎች ውሏችንም አመሻሻችንም ሃያ ሁለትና አከባቢው ነው። የኔ ጎደኛም(ባለ ታሪኩ ማለት ነው) አውራሪስ አከባቢ ትልቅ የግል ድርጅት አለው። እንደነገርኩህ ሃያ ሁለት በምንውልበት ሰዐት ብዙውን ስራችን በስልክ እየተደዋወልን ስለምንሰራው፣ የሆነች ድራፍትም ይሁን ቢራ የሚሸጥበት ቤት ገብተን ምሳችን በልተን እየጠጣን ውለን ነበር ምናመሸው።

አንድ ቀን በአዲሱ አስፖልት አከባቢ የሆነች አዲስ ቤት አግኝተን እዛው ስንጫወት ውለን አመሸን። ባለቤቲቷ በጣም ጥሩ ጨዋና ስርዓት ያላት ሴት ነበረች። እቤቱ ውስጥ ምታስተናግድና ሂሳብ ምትሰራ ልጅም ነበረች። የታላቅ ወንድሟ ልጅ እንደሆነችና እሷ እንዳሳደገቻት አወራችን። ያስተናገደችን ልጅ ውበቷ ልዩ ነው ፤ ትከየፍባታለህ ። ጓደኛየም ልጅቷን ደስ ብላው ስለ ነበር እየተመላለስን በቃ በዛው ከስተመር ሆንና ፤ ተዛመድን። በሂደትም ከልጅቷ ጋር ክንፍ ያለ ፍቅር ውስጥ ወደቁ። (በነገራችን ላይ ጓደኛየ ባለ ትዳር ነው።)

ከልጅቷ ጋር በፍቅር ላይ እያሉ ለሁለት አመት ግዜ ያህል ከአገር የሚያስወጣ ጉዳይ (በጦርነቱ ግዜ ትግሬ ሲሳደድ ግዜ) ይገጥመውና እስከ ሙሉ ቤተሰቡ ካናዳ ይከርማል። እኛ ጓደኞቹም የምንሰራው ስራ ብዙ ግዜ የሱ ስለነበረ እሱ ከተለየን ቡሃላ መገናኘታችን እየቀዘቀዘ ወደ ሃያ ሁለት የሚያስኬደን ጉዳይም ብዙ ስላልነበር ጀምዓው ተበተነ።

ከሁለት አመት ቡሃላ ፤ ነገር ሲረግብ ፥ ፍሬንድ ሚስትና ልጁን እዛው ትቶ ተመልሶ መጣ። ጀምዓውም እንደገና መሰባሰብ ጀመረ ። አንድ ቅዳሜ ተደዋውለን ምሳ እንብላ እንባባልና አሹ ስጋ ቤት እንሰባሰባለን። እዛው ስንጫወት ዋልን። በግምት ከምሽቱ ሁለት ሰአት አከባቢ ሲሆን መበታተን ጀመርን።ከአሹ እየወጣን እያለ 'ጓደኛየ ምናወራው ነገር ስላለ ግማሽ መንገድ ልሸኝህና ከዛ RIDE ትይዛለህ' ብሎኝ እሱ መኪና ውስጥ ገባሁ።

በጉዞ ላይ አትላስ መብራት ልንደርስ ስንል በተቃራኒው መንገድ Street ላይ የሆነች ልጅ አይቶ ዳር ይዞ "ቲና" እያለ ይጣራል። ልጅቷም ተሻግራ ስትመጣ ያቺ ከሁለት አመት በፊት በፍቅር ክንፍ ያለላት አስተናጋጅ ልጅ ነበረች።( የመጣ ሰሞን ሲፈልጋት ነበር፣ አጋጣሚ የነበረችበት ቤት ሄደን ሌሎች አዳዲስ ሰዎች ናቸው የሚሰሩበት) እኔም ወርጄ አቅፌ ሰላም አልኳት። ወደ መኪናው ግቢ አላት። ገባች።

መኪናውን ከአትላስ ወደ መድሃኔአለም አቅጣጫ እያሽከረከረ ይዞን ሄደ። (ልጅቷ በወቅቱ የStreet ስራ ጀምራ ነበር። የዚ ታሪክ ረጅም ነው ፤ ይቅርብህ )። በቃ ፥ በዚህ አጋጣሚ ጨዋታውን አስቀጥለነው እናመሻለን አለን። እኔና ቲናም በሃሳቡ ተስማምተንና ግብዣውን ተቀብለን ሶስታችን አንድ ላይ አልኮል ስንጠጣ አመሸን። የለሊቱ ከሰዐት አከባቢ ስለደከመኝ ወደቤት ልግባ ብየ RIDE ጠራሁ። ሁለቱም ተያይዘው የነበርንበት አካባቢ Room ይዘው አደሩ።

ከዛ ቡሃላ በተደጋጋሚ የተለያዩ ጊዚያቶች እኔ ባልኖርም እዛች አትላስ ያገኘናት አከባቢ ሄዶ ፒክ ያረጋትና አብረው አምሽተው ያድራሉ። የሆነ ግዜ ግን በተደጋጋሚ ቢሄድም ሊያገኛት አልቻለም። የሚገርምህ ፤ ስልኳ አልነበረውም ፤ እዚህ ስትመጣ ታገኘኛለህ ነበር መልሷ እሱ እንደነገረኝ)

የዚህ ሁሉ ታሪክ አስገራሚውም አስደንጋጩም ነገር የሚፈጠረው እዚህ ላይ ነው።ያቺ ሚስኪን ጨዋ ትሁት የሬስቱራንቱ ባለቤት ፣ የልጅቱ አክስት የነበረችው ሴት ጉርድሾላ Century Mall ለሆነ ስራ ጓደኛየጋ ሄደን በሩ አካባቢ አገኘናት። ትንሽ ጉስቁልቁል ብላለች ወዟም ጠፍቷል። ሰላምታ በደንብ ከተለዋወጥን ቡሃላ ...

"ምነው ታመሽ ነበር እንዴ?"አልኳት

"እረ ደህና ነኝ። ከወንድሜ ልጅ ሞት ቡሃላ ልክ አደለሁም። አጋዤን፣ ያሳደግኳት ልጄን ካጣኋት ቡሃላ መኖር ሁሉ አስጠላኝ ወይኔ ቲናየ" ብላ እምባዋን ታዘራው ጀመር።

"እንዴ ቲና ምን ሆነች? መቼ? ምናምን እያልን መንተባተብ ስንጀምር ...

"ኣጣኋት ። መኪና በላብኝ። አንተ ውጭ ልትሄድ ከተሰናበትከን ቡኋላ በሶስተኛው ወሩ አካባቢ ቦሌ ርዋንዳጋ ልጄ መኪና በላት" ብላ አምርራ ለቅሶውን አቀለጠችው። የዛኔ ድብልቅልቅ አለብኝ። ታድያ ከውጭ ከመጣ ቡሃላ ያገኘናት ማናት????????????!!!

እንደምንም ብየ ሊፈነዳ ያለውን ጭንቅላቴን አረጋግቸ ፤ እሷን መጠየቅ ጀመርኩ ። መች አደጋ እንደደረሰባት? የፖሊስ ምርመራ ሪፖርት መኖሩና አለመኖሩ?የሆስፒታል የሞት ሰርተፊኬት? የት እንደተቀበረች? የመሳሰሉት ግራ እየተጋባችም ቢሆን ጠየቅናት። ሰኀሊተ ምህረት እንደተቀበረች፤ ኧረ ያንን ቀን ወስዳ መቃብሯ ሁሉ አሳየችኝ።

ታድያ ጓደኛየ ከካናዳ ከተመለሰ ቡሃላ ያቺ በተደጋጋሚ ስትገናኘው የነበረችውና አሁን የተሰወረችው 'ቲና' ማናት??? Right now, my friend is not normal, ሉሌ. He already got insane. አልኮል ውስጥ እራሱ ደብቋል ።

ለልዕል ተወልደ የተላከ

@wegoch
@wegoch
@paappii
👍50😱35🤔86🔥1🥰1
Gize Wegoch, [Oct 21, 2024 at 8:57 PM]
አይጠሩ
...........

   በአማት መወደድ ለጥቂት ዕድለኛ ኢትዮጵያውያን ብቻ የተሰጠ ፀጋ ይመስለኛል።በተለይ ደግሞ በቁመት የምትበልጥህን ሴት ልታገባ እየተዘጋጀህ ከሆነ!ነፍሳቸውን ይማርና ጎረቤታችን አብዬ በላቸው
"ፍቅር ምን ድረስ ክፉ ነው?"ተብለው ሲጠየቁ
"እኔና ሰዋለምን እስቲያጋባን ድረስ" ይሉ ነበረ አብረው ሲቆሙ በጡታቸው ትክክል የሚሆኑትን ሚስታቸውን እያሰቡ።የሞቱት አብሯቸው የኖረው አስም በሌሊት አፍኗቸው ነው ቢባልም የመንደራችን 'ፓፓራዚዎች' እንደሚሉት ከሆነ ግን ለሞት ያበቃቸው አስሙ ብቻ ሳይሆን በባለቤታቸው ጡቶች መሃል አፍንጫቸው መታፈኑ ነበር።
እሰቡት 1.50 ሆኜ 1.75 የምትረዝም እጮኛ ስይዝ! አብዬ በላቸው ከነሚስታቸው ድቅን ይሉብኛል። ከመጋባታችን አንድ ወር አስቀድማ ከቤተሰቦቿ ጋር አስተዋወቀችኝ።ያደገችው ከአሽሙረኛ እናቷና ከጉልቤው ወንድሟ ጋር ነው።ውበቷን ያየ የእናቷን ወግ አጥባቂነት እና የወንድሟን ኃይለኝነት መገመት አያቅተውም።ልታስተዋውቀኝ ቤቷ የወሰደችኝ ቀን እናቷ እትየ ዘውዴ ከእግር እስከራሴ አልቢን በሚያስንቅ አይናቸው እንደሽንኩርት ከላጡኝ በኋላ የሚያበሽቅ ሳቃቸውን አስከትለው
"እንዴት ያለ ኮረሪማ አግኝተሻል ሚጡ!ና እስቲ ሳመኝ"ብለው ሱባኤ እንደገባ ገዳምተኛ ወገባቸዉን በነጠላቸዉ አሰሩና ከምድር ወገብ የሚሰፋ ሽክርክሪት መቀነታቸዉን እየቋጩ ጎንበስ አሉ። መና እንደወረደለት ሰዉ ወደ ላይ ቀና  ስል ከመቅፅበት ትከሻዬን እንደቅቤ ቅል እየናጡ አገላብጠው ሳሙኝ።ልጃቸው በሷ እንደወጣች ቁመታቸው ይናገራል።ከፊት ለፊታቸው ስቆም ከአይናቸው ይልቅ ከጡታቸው ጋር ነው የምፋጠጠው።ጃንሆይም እንደሳቸው ጡት መውደቃቸውን እጠራጠራለሁ።እንኳን የሳቸው ጡት ሁለት ልጅ የጠባው ይህች ጉደኛ ሀገር ራሷ ደርግ አይጥ እንደቀመሰው ካልሲ ቦትርፏት፣ኢህአዴግ እንደ ገና ዳቦ በላይ በታች አንድዷት፣የአሁኑ ጉድ በወሬ ፓትራ እስከጥግ ነፋፍቷት...የሳቸውን ጡት ያህል ዝቅ አላለችም።

  ሳሎናቸው ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የቤተሰብ ፎቶ ሳይ "አቤት ግጣም በልክ ሲገኝ!" አሰኘኝ።ባለቤታቸው ከእሳቸው የበለጡ ብቅል አውራጅ ቢጤ ናቸው።ወንዱ ልጃቸው ከሚጡ ትንሽ ይረዝማል።ደፍሬ ሳሎናቸውን የረገጥኩ የመጀመሪያው ስንዝሮ እኔ ሳልሆን አልቀርም።

ወደ ምግብ ጠረጴዛው ስናዘግም አሽሙር የተካነ አፋቸውን አሸራመው እየቃኙኝ
"ሶፋው ላይ እንሁን መሰል ጠረጴዛው አለቅጥ ረጅም ነው" አሉኝ።ጠረጴዛው የረዘመብኝ እንደሁ ሌላ ዝርጠጣ ስለሚከተለኝ ጥያቄአቸውን ተቀብዬ ወደ ሶፋው አመራን።ከመቀመጣችን ሌላ ብቅል አውራጅ ባልቴት እየተንጎማለሉ ዘለቁ።ሚጡ ወደ ጆሮዬ ጠጋ ብላ
"አክስቴ ናት ኃይልሻ" አለችኝ።
እትየ ዘውዴ
"ህብስቴ መጣሽ?ቀረሽ ብየ ነበር'ኮ እመዋ" አሉና አገላብጠው ከሳሟቸዉ በኋላ አቆልቁለው እያዩኝ
"ነይ ሳሚው የሚጡን ባል...እየውልሽ እንዴት ያለውን ምጥን የወንድ አውራ እንዳመጣችው"
"ኧግ!የቢያዝኔ ምትክ...እምጷ...የአባቷ ምትክ...እምጷ...የት አገኘሃት?... እምጷ ይችን መለሎ...እምጷ"
የሞት ሞቴን  ፈገግ ብዬ ከመቀመጤ በእህታቸው እግር ተተክተው ይወጉኝ ገቡ።
"ዋዋዋዋዋ...እንደው ከየት አገኘሃት?ማነበር ያልከኝ ስምህን"

"ኃይሌ"
"ምንድን ነዉ ስራህ?"
 'ገጣሚ ነኝ' ልላቸው ፈለኩና የዘመኔ ገጣምያን  በህሊናየ ድቅን አሉብኝ።
በእዉቄ እንኳን ቁመቱ ጊዜ ጠብቆ የሚጨምረዉ ግጥም ወይም ወግ ሲያነብ ብቻ ነዉ። ምክንያቱም ተመልካቹ ሁሉ ተቀምጦ ስለሚያዳምጠው።
ብዙዎችን በአይምሮዬ ማሰላሰል ስጀምር ገጣሚነቴ ተኖ ጠፍብኝ ።
"ምን አልከኝ ?"ሲሉኝ
"እ የዩኒቨርሲቲ መምህር ነኝ" አልኳቸዉ በደባልነት የያዝኩትን ሙያዬን።
"እ...መምህርነት ሸጋ ነው!...እና ከየት አገኘሃት በል ይችን መለሎ?"
"እህ...ህ...ህ...ትውውቃችን እንኳን ከድሮም ነው...ከትምህርት ቤት"
"ኧረግ ኧረግ ኧረግ ኧረግ!!...መቸም ተፊት ተቀምጣ እየከለለችህ አስቸግራህ ነው እሚሆን...እሂ...ሂ...ሂ...ሂ"
'ጥርስዎት ለሙቅ አይትረፍ!ድዳም'

"ኧረ በነገር አትያዣቸው ህብስቴ ምሳው ይቅረብ" አሉና አማቴ ሰፋ ባለ ትሪ ዶሮ ወጣቸውን በአይብ አጅበው አቀረቡት።
'ሰው ከረዘመ ሞኝነት አያጣውም' የሚለው አባባል እዚህ ቤት አይሰራም።እንደውሃ ሙላት እያሳሳቁ መግደልን ተክነውበታል።

ህይወቴ በረጃጅም ሴቶች ዙሪያ እንዲሽከረከር ማን እንደፈረደብኝ ባላውቅም 8ኛ ክፍል እያለን በደብዳቤ የጠየቅኋት መለሎዋ ማህሌት ራሱ  ደብዳቤውን ለስም ጠሪ ሰጥታ ተማሪዎች ፊት ከማስነበብ የከፋ አልጨከነችብኝም። የልብ ስእል ለመሳል የቀደድኩትን ወረቀት እናቴ ሰብስባ ሶስት እንጀራ ከነ ካሲናዉ እንዳወጣችበት ሳስታዉሰዉ ይደንቀኛል።
በጦር ተወግቶ ለሚደማው ልቤ ማሳያ ይሆነኝ ዘንድ አባቴ በፀሀፊነት ከሚያገለግልበት የሰፈሩ እድር የተቀበለውን ብቸኛ ቀይ እስኪብሪቶ በማገንፈሌ አንድ ፌርሜሎ ከሰል ተቀጣጥሎ ለሳምንት ወጥ መስሪያ የሚሆን በርበሬ ታጥኜ ነበር።ይህን ሁሉ መስዋዕትነት ከፍዬ
"ያም አለ ያም አለ የአተር ገለባ ነው
ሰው ይዋደድ እንጅ ቁመት ለአገዳ ነው" ብዬ መጻፌን ሳስታውስ እንደቂል በራሴ እስቃለሁ።

  ዶሮው ተበልቶ ሲያበቃ ያመጣሁት ውስኪ ተከፈተና አንድ ሁለት እያልን ጨዋታ ቀጠልን።በመሃል አማቴ ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የባለቤታቸውን ፎቶ አዩና አንደ መሳቅም እንደማልቀስም እያደረጋቸው

"አየ....የ...የ...ቢያዝኔ ዛሬ ነው  የሞትክ!አየ የኔ ጠምበለል!"ወዲያው ወደ ሚጡ ዞረው
"አይደለም እንዴ አንች?ዛሬ አይደለሞይ የሞተው?እንዲህ አለምሽን ሳያይ...አይ ቢያዝኔ!" ብለው በተቀመጥኩበት ከአፈር የሚደባልቅ አስተያየት አከሉልኝ።

የቁመቴን ማጠር የኪሴ መወፈር አካካሰው እንጂ እናትየው የዛኑ ቀን ከኔ በሚረዝም በቡሀቃ ማማሰያቸው እያጠደፉ ቢያባርሩኝ እንዴት ደስ ባላቸው!ባስተዋወቀችን በሳምንቱ የኔዋ ጉድ ከሰርጉ በኋላ የምንገባበትን ቤት እናቴ ካላየችው ብላ እየጎተተች አመጣቻቸው።ሳሎኑን በገረፍታ አዩና ምኝታ ቤት ዘው ብለው ገቡ።አልጋው ላይ አፍጥጠው
"ምነው እንዲህ ሰፋ?በራይ ልትወጡበት ነው?ባይሆን ቁመቱን ጨምሩት!" አሉ።የልጃቸውን ቁመት ያህል በእግዚሀሩ እንኳን መመካታቸውን እንጃ!

  ሰርጉ ሳይሰረግ እንዲህ የቋንጃ እከክ የሆኑብኝ ከተሰረገ ወዲያ ሊኖረኝ የሚችለውን ህይወት ሳስበው ሚጡን ማውራት እንዳለብኝ ተሰማኝ።
"እትየ ዘውዴ ከሰርጉ በኋላ ለበዓል ካልሆነ እንዲመጡ አልፈልግም!"አልኩ ምርር ብዬ

"ምን ማለትህ ነው ኃይልሻ?እናቴ'ኮ ናት!"

"ለኔ ደግሞ አማቴ ናቸው!የማይወዱኝ አማቴ!ጣልቃ ገብነትም'ኮ ልክ አለው።አንቺ ለምታገቢኝ የሳቸው አቃቂር አውጭነት ምን ይሉታል?"

"ኢሂ...ሂ...ሂሂሂ...እማዬ'ኮ ተጫዋች ስለሆነች ነው...ደግሞም የምትወደው ሰው ላይ ነው የምትቀልደው...አትቀየማት"ብላ በጥርሷ አዘናጋችኝ።

ሰርጉ 3 ቀን ሲቀረው ለንቦጯን ጥላ መጣች።
"ምን ሆነሽ ነው?" ዝም

"አንቺ ሚጡ ምን ሆነሽ ነው?" ዝም

"አትናገሪም እንዴ?"

"ከእማዬ ጋር ተጣላን"ብላ ለንቦጯን ይብስ ዘረጋችው።

"በምን?ምን ተፈጠረ?"

የስልኳን ፎቶ ማከማቻ ከፍታ አንድ ሂል ጫማ አሳየችኝና
"ይሄን ጫማ ለሰርጌ አደርገዋለሁ ብዬ የዛሬ ወር ነው የገዛሁት።ትናንትና ማታ አይታው 'የዘውዴ መቃብር ሳይማስ ይኸን ለብሰሽ አትሞሸሪም!' " አለችኝ።
Gize Wegoch, [Oct 21, 2024 at 8:57 PM]
👍46😁135🥰1🤔1
'ለምን' ብዬ ልጠይቅ ከማሰፍሰፌ ምክንያታቸው ተገለጠልኝና አስችለኝ ብዬ
"ታዲያ ከሳቸው ደስታ የሚበልጥ ምን አለ ሚጡዬ?በቃ የመረጡልሽን አድርጊ እናትሽ አይደሉ?" ብዬ አባበልኳትና አቅፌአት የጨጓራዬን ጭስ ወደ ባዶው አየር ለቀቅሁት።

የመሞሸሪያችን ቀን እሳቸውን የቻለ ትዕግስቴን ጎረቤቶቻቸውና ወዳጆቻቸው ሲፈታተኑት ዋሉ።እዮብም እንዲህ መፈተኑን እንጃ!ታላቅ ወንድሟ ካሳሁን ጓደኞቹን ሰብስቦ ሰርጌን የጀማሪ ክብደት አንሺ የቅርፅ ዉድድር አስመሰሉት።   በሌባ ጣቱ መሬቱን እየጠቆመ
"ሎ...ሎጋው  ሽቦ...ቦ" ሲል
"ኧረ የምን ሎጋው ሽቦ?እስቲ ሌላ ትከሻ እሚፈትን ዘፈን አምጡ"አሉ  ጎረቤታቸው እትየ አስካል።የቀለም ትምህርቱም ሆነ ህይወት ራሷ ባስተማረችኝ ልፈታው ያልቻልኩት ትልቁ እንቆቅልሽ ሴት ስታርጥ ለምን አሽሙረኛ እንደምትሆን ነው።አዛውንቱን ቀርቶ ወጣቱን የሚያስት ጥርሳቸውን ብልጭ እያደረጉ ያቀነቅኑ ገቡ።
አንች የኔ አበባ ነሽ የኔ አበባ...
አንች የኔ አበባ ነሽ የኔ አበባ(ተቀባይ)
....
መላ ነው ነይ መላ
እነው መላ መላ(ተቀባይ)(2x)
የዘውድነሽን ልጅ ነይ መላ
እነው መላ መላ(ተቀባይ)
ወዴት አገኛት       "      "
አለ እናቷ ጓዳ      ''      "
መታያም የላት      "      "
የኔማ ዘውድነሽ       "        "
እጇ ያረፈበት           "        "
ለአልፎ ሂያጅ ይበቃል  "       "    
ማጠር አያውቅበት  "     "
እየው እየው መላ

አሉና ለ ሁለት ደቂቃ ያህል ትከሻቸው እስኪገነጠል ተንዘፍዝፈው ከከበባቸው ተቀባይ መሃል ወጡ።የሳቸውን መንዘፍዘፍ ተከትሎ አማቴ በኩርፊያ ተነፋፍተው ወደ ጓዳ እያቶሰቶሱ ሲገቡ ታዝቤ ነበር።
በነጋታው  የተከራየነዉን ቬሎ መልሰን በአማቴ ሰፈር በኩል አለፍን...ሰይጣን ሹክ ብሎን ነው መቼስ!እትየ ዘውዴ ቤት ስንደርስ በርከት ያለ ሰው ተሰብስቦ ስላየን  ጠጋ አልን።አማቴ እያማረሩ ለተሰበሰበው ህዝብ ስሞታ ያቀርባሉ።

"ምነው ነገር በኔ መግነኑ?አጭር አምቻ በኔ አልተጀመረ!ምነው ዘቢዳር በርጩማ እሚያህል አምቻ ስታመጣ ምን ተባለ?ደሞ ደግሸ ባበላሁ እኔ ላይ አሽሙር አስካል?እኔ ላይ?... ቁመት ቢረዝም ምን ሊረባ??በቁመት የጎዳውን በጠባይ ክሶት የለ?...እንደአንች አምቻ ነጋ ጠባ ከሚጎረጉጫት ኧረ የሽቶ ጠርሙስ አክሎ መኖር በስንት ጣዕሙ?..."እያሉ የጥያቄ ናዳ ሲያዥጎደጉዱ እትየ ዘቢዳር የተሰበሰበውን ሰው እየገፈታተሩ እትየ ዘውዴ ላይ ደረሱ

"እከከከከከከ!ይች ናት ዘቢዳር!የማን አምቻ ነው በርጩማ አንች?የኔን አምቻ ነዋ ምሽቱ ብብትና ብብቱን ይዛ አልጋ ላይ እምታሰቅለው!አልሰማንም'ኮ አሉ...አልሰማንም...አሁን ማን ይሙት ከአንች አምቻ የሚወደለው እንቅፋት ሆኖ የሰው ጥፍር አይልጥም? " እያሉ ሲውረገረጉ
ሹልክ ብዬ ወጣሁና ከጥቂት እርምጃ በኋላ ያገኘኋቸውን አንድ የኔ ቢጤ አባት ሰላም ብዬ ጥያቄዬን አስከተልኩ።

"አባቴ እንደው መዘጋጃ ቤቱ በየት በኩል ይሆን?"
"ማን ሞቶ ነዉ?" ደንገጥ ብለው ጥያቄዬን በጥያቄ መለሱት።
ቃል አጠሮኝ ጉዞየን ቀጠልኩ።ለካ ፍታትና ቀብር ለሞተ ብቻ ነዉ።

ዘማርቆስ

@wegoch
@wegoch
@paappii
👍43😁187👏4
Forwarded from Studio Anaya (Ribka Sisay)
አዲስ አበባ የምትገኙ ብቻ ከትምህርት ጋር የተገናኙ ማስታወቂያዎችን ለመስራት ከ10-15 አመት ያሉ ሴት እና ወንድ ካስቶች እየመለመልን ስለሆነ 3 የተለያዩ ፎቶዎችን ወላጆች ከስልካቹ ጋር @Ribki30 ላይ ላኩልን።
👍32
እማማ አፀደ የሚባሉ ጎረቤት አሉን የእናቴ ጓደኛ ናቸው። እማማ አፀደ አመም አድርጓቸው ህመማቸው በባሰ ቁጥር እናቴን ጠሏት።

ይሰድቧታል ሌባ ናት ይላሉ።
መሰሪ ናት ይላሉ።
ልትገለኝ ትፈልጋለች ይላሉ።
መርዝ አበላቺኝ ይላሉ ። አትምጣብኝ ብለው ስሞታ ይናገራሉ ሌሊት እቤቴ ልትገባ ነበር ይላሉ ።

ሰው እንዳትመስላችሁ ይላሉ ። እናቴ ቤታቸው መሄድ አቆመች ።

ከቤት መውጣት እያቆሙ ግቢያቸው መዋል ጀመሩ ....

እናቴ እሷ መሆኗን አትንገሩ ብላ ፤ ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸውን ልጅ ፤ ምን ጎደለ ጤናቸው እንዴት ነው እያለች ትሰልላቸዋለች...

ንዴት ሊገድለኝ ይደርሳል ። እቆጣታለሁ << ስምሽን እያጠፉሽ እየሰደቡሽ እየጠሉሽ አትተያቸውም ወይ?>> እላታለሁ!!

<<ጭንቅላታቸው እጢ ወጥቶባቸዋል እሱ ነው ትንሽ ቀየር ያደረጋቸው እንጂ ፤ እሳቸው እንኳን ሳልበድል ብበድላቸው እንኳን በክፉ አያነሱኝም>> ትለኛለች።

ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸው ልጅ በኩል የሚያስፈልጋቸውን መድኃኒት መግዣ ከኛ ወስዳ ... ተበድራም ቢሆን ትገዛላቸዋለች ። እሳቸው ያቺ ምናምንቴ ፣ ድግምታም ያቺ ነጠላ እያሉ ጮክ ብለው እናቴን ሲሰድቧት ይውላሉ ።

ጠላኋቸው !!

አንድ ቀን ለምን ግን እንዲ ስምሽን እያጠፉ እየጠሉሽ እያልፈለጉሽ አልጠላሻቸውም? ብዬ እናቴን ጠየቅኋት።

<<ጓደኛዬ ናቸው! እዚህ ሰፈር ስመጣ እሳቸው ናቸው ያለመዱኝ ። እድር ያስገቡኝ ፥ የሌለኝን እቃ ያዋሱኝ ፥ የተቆረቆሩልኝ ፥ የአረሱኝ ፣የመከሩኝ...

እንዲህ አይባልም እያሉ መንገድ ያሳዩኝ እርሳቸው ናቸው ። ድንገት ታመው ነው የተቀየሩት ።ከሁሉም ጋር ነው መጣላት የጀመሩት እኔ ላይ ትንሽ ጠንከር አሉ እንጂ ...

በክፉ ግዜ እንኳን ወዳጅ ላይ ጠላት ላይ አይጨከንም!!

የጨዋ ሰው ልክ የሚታየው ሲጣሉት ነው ። በፍቅር ግዜ ሰው አይመዘንም ክፉ ግዜ ነው ሰው የሚያጠለው ....

አፀዱ እንዴት አይነት ጥሩ ሰው መሰሉህ ዛሬ ህመም ተጣብቷቸው እን'ጂ ። ስንት ቀን መሰለህ እጦት በሳቸው ሳብያ ከቤታችን የተባረረው ።
አፀደ ደግ 'ሩህሩህ ናቸው...

እናንተ ሳትወለዱ ማንም ሳይኖረኝ ነው ከኔ ጋር የነበሩት...

የአፀደ ውለታ አለብኝ !>>

By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
71👍34🔥6🥰2👏2