Unity Park-አንድነት ፓርክ
563 subscribers
164 photos
1 video
20 links
አንድነት ፓርክ በ 2012 ተቋቋመ ፡፡ ፓርኩ የሚገኘው በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ በሚገኘው ታላቁ ቤተመንግስት ውስጥ ሲሆን ከመቶ ምዕተ ዓመት በላይ የመንግሥት መቀመጫ ሆኖ ቆይቷል፡፡
Download Telegram
ሻለቃ/ጋዜጠኛ ወይንሐረግ በቀለ “የወታደር ልጅ ነኝ” ብላ ስትናገር እጅግ በኩራት ነው። ወታደር መሆን ደግሞ ኩራቱ የትናየት ከፍ እንደሚል አስቡት፡፡ ሳይሰስቱ ሀገር ማፍቀርንና ሳይታክቱ ሕዝብ ማገልገልን ከወታደሮቻችን እንማር! 3/3
ለሠራዊታችን ደም እንለግስ። የዐቅመ ደካሞችን ቤት እናድስ። #አረንጓዴዐሻራችንን እናሳርፍ። የግብርና ምርታማነታችንን እናሳድግ። የየቢሮ ሥራችንን ዐቅም ጨምረን እንሥራ፤ እያንዳንዳችን ከሚጠበቅብን በላይ ስንወጣ፣ ሁሉም ነገር ይስተካከላል!
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሐፈት ቤት ሠራተኞች ለቀረበው ሀገራዊ ጥሪ ምላሽ፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ለመደገፍ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ሊሰጡ ወስነዋል።

#PMOEthiopia
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!
የሰብአዊ ዕርዳታ ወቅታዊ መረጃ፦ ዛሬ ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ወደ ትግራይ ክልል የምግብ ዕርዳታን ይዘው የገቡ የጭነት መኪናዎች 277 ደርሰዋል።

Humanitarian Update: As of August 11, 2021, 277 trucks of food assistance have entered the Tigray Region.
‘እችላለሁ’ የሚለው የድል አድራጊዎች አመለካከት ነው! የ21 ዓመቷ ወጣት የአብሥራ ሺፈራው የዚህ ዓይነቱ የአሸናፊነት እና የጽናት ተምሳሌት ናት። ምንም ዓይነት ተግዳሮት ቢያጋጥማቸው በቆራጥነት የሚጸኑ እንዲህ ያሉ ወጣቶችን በማግኘቴ ደስ ብሎኛል።
#dr.Abiy Ahmed
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ባሰራጩት መልዕክት ፥ "ቃል እንደገባነው እጅን አፍ ላይ የሚያስጭን ገድል መፈፀማችንን የምናበስርበት ጊዜ ቅርብ ነው" አሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ "ጠላት ወደወጥመዳችን እየገባ ነው" ያሉ ሲሆን የማሸነፍ አቅማችም ተጠናክሮ እየወጣ ነው ሲሉ አሳውቀዋል፤ በቅርብ ጊዜ ውስጥም እጅን በአፍ የሚያስጭን ገድል መፈፀማችንን እናበስራለን ብለዋል።

የያዝነው የኢትዮጵያን አምላክ ነው ያሉት ጠ/ ሚኒስትሩ የምንታገለው ለኢትዮጵያ ነው ፤ የሚዋጋው የኢትዮጵያ ጦር ነው ፤ በመጨረሻም ታሪክ እንደሚነግረን አሸናፊዋ ኢትዮጵያ ናት ሲሉ ገልፀዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ጠ/ሚኒስትሩ ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ፦
- በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን የሚዲያ ዘመቻ እና የዴፕሎማሲ ጫና ለመመከት እንዲረባረብ፤
- የውሸት ዜናዎችን እየተከታተለ እንዲያመክን፤
- ህወሓት በሚነዛው ፕሮፖጋንዳ ሳይደናበር፤ የሴራ ትንታኔ ውስጥ የገቡ ከሴራ ትንታኔ በመውጣት ህወሓት ጦርነት የከፈተበትን የዴፕሎማሲና የጦር ግንባር እንዲቀላቀሉ፤
- ሁሉም ለሀገሩ አምባሳደር ሆኖ ለሀገሩ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

* ሙሉ መልዕክቱ ከላይ ተያይዟል።
“የውሸት ፀሐይ ሲጠልቅ የሤረኞች ወጥመድ ይበጠሳል!”