ትምህርት ሚኒስቴር
177K subscribers
455 photos
2 videos
46 files
476 links
📚ይህ ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስትር የተማሪዎች መረጃ ማቀበያ ገፅ ነው

📚 This unique channel is prepared by the community request.

Any comment & Paid Ads @Tmhrt_Ministers_bot

《Buy Ads :- https://telega.io/c/tmhrt_ministers1

#ትምህርት_ሚኒስቴር
Download Telegram
ስድስት የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች በዓለም ላይ ካሉ ሁለት ሺህ "ከፍተኛ ደረጃ" ያላቸው ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ለመካተት ቻሉ።

የዩኒቨርሲቲዎች ዓመታዊ ደረጃ የሚያወጣው Center for World University Rankings (CWUR) የተባለ ተቋም የዩኒቨርሲቲዎችን የ2024 ጀረጃ ይፋ አድርጓል።

ደረጃ ከተሰጣቸው 20,966 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ 2,000 ዩኒቨርሲቲዎች ወይም 9 ነጥብ 5 በመቶዎቹ ብቻ "ከፍተኛ" ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

በተቋሙ የ2024 ደረጃ መሠረት፦

1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ➭ 841ኛ
2. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ➭ 1701ኛ
3. መቐለ ዩኒቨርሲቲ ➭ 1748ኛ
4. ጅማ ዩኒቨርሲቲ ➭ 1767ኛ
5. ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ➭ 1886ኛ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ➭ 1982ኛ መሆን ችለዋል።

በዘንድሮው ደረጃ ከቀዳሚ አስር ዩኒቨርሲቲዎች፣ ስምንቱ የዩናይትድ ስቴትስ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

ላለፋት 12 ዓመታት ደረጃ ሲያወጣ የቆየው ተቋሙ፤ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡት የትምህርት ጥራት፣ የምርምር ጥራት እና የፋክሊቲ ደረጃ በመሳሰሉት መለኪያዎች ይገመግማል።

መንግሥታት እና ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት እና የምርምር ውጤቶቻቸውን እንዲያሻሽሉ በማማከር የሚታወቀው ተቋሙ፤ የዩኒቨርሲቲዎችን ዓለም አቀፍ ደረጃ ከአላማ፣ ግልፅነት እና ዘላቂነት መርሆች አንፃር ይመድባል።

የዘንድሮ የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃን ይመልከቱ፦ https://cwur.org/2024.php

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል ተመሠረተ።

ካውንስሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዘርፉን ማስተሳሰር የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

የአመራር ካውንስሉ ጥናትና ምርምር በማድረግ ልዩነት መፍጠር የሚችል የሰው ኃይል ማፍራት ኃላፊነት እንደተጣለበት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገልፀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከ2,000 በላይ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በመንግሥት እና በግል ባለቤትነት ስራ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ከ100 በላይ የሚሆኑት የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መሆናቸውን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ጠቅሰዋል፡፡ #ENA

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር በመተባበር 3ኛ ዙር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) ሰጥቷል።

በወረቀት የተሰጠውን የ IELTS Academic and IELTS General Training ፈተና 25 አመልካቾች መውሰዳቸው ተገልጿል።

በዩኒቨርሲቲው 4ኛ ዙር ፈተና ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም ይሰጣል የተባለ ሲሆን የአመልካቾች ምዝገባ ተጀምሯል።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የጤና ሚኒስቴር አዲስ የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NIMEI) 2016 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የቃል ፈተና የሚሰጥበትን ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡

በከፍተኛ ጥንቃቄ በእጅ የታረመ የፅሁፍ ፈተና ውጤት በዚህ ሳምንት እንደሚጠናቀቀቅ ኮሌጁ አሳውቋል፡፡

የፅሁፍ ፈተና ውጤቱ ከተለጠፈ ከአንድ ሳምንት በኋላ የቃል ፈተናው ሊሰጥ እንደሚችል ኮሌጁ ገልጿል (ከክልል ለሚመጡ ተፈታኞች በቂ ጊዜ ለመስጠት፡፡)

የፈተናው ሒደት ግልፅነት በተሞላበት ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆመው ኮሌጁ፤ ተወዳዳሪዎች የሚኖራቸውን ማንኛውም አይነት ቅሬታ የሚያቀርቡበት ዕድል ይመቻቻልም ብሏል፡፡

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በመጪው ሰኔ ወር የሚሰጠው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ን በድጋሜ ለሚወስዱ ተፈታኞች መልዕክት አስተላልፏል።

1ኛ. በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የነበረና አሁን በድጋሜ ለመፈተን ማመልከት ለሚፈልጉ፤

2ኛ. ከሰኔ 2015 ዓ.ም በፊት #የሕግ_መውጫ_ፈተና ወስደው የማለፍያ ነጥብ ያለገኙ አሁን በድጋሚ ለመውሰድ ለሚፈልጉ ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርስቲያቸው ለትምህርት ሚኒስቴር የተላከላቸው አመልካቾች፤

ምዝገባው እስከ ግንቦት 25/ 2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ገልጿል።

ተፈታኞች በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ብቻ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ ተብሏል።

ሚኒስቴሩ ፦

➡️ ከላይ ከተገለጸው ጊዜ ውጭ የሚቀርቡ የምዝገባ ጥያቄዎች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው አሳስቧል።

➡️ በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያልመጡ አሁን በድጋሜ መፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች የሚጠበቅባቸውን የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር ብቻ መፈጸም አለባቸው ተብሏል።

➡️ ከሰኔ 2015 ዓ/ም በፊት ለሕግ መውጫ ፈተና ተቀምጠው በድጋሜ ለመፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርሲቲያቸው መላኩን በማረጋጥ የሚጠበቅባቸውን #የአገልግሎት_ክፍያ ለዚሁ ጉዳይ ብቻ በተከፈተው የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር ➡️1000553176097 ገቢ በማድረግ ደረሰኙን በግልፅ በሚታይ #ስካን_ኮፒ በማድረግ በ seneexit2016@gmail.com ኢሜል አድራሻ እንዲልኩ ጥሪ ቀርቧል።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎቹን በት/ቤታቸው ለማስፈተን ምን ማሟላት አለባቸው?

በዚህ አመት በኦንላይን የተዘጋጅውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ አገር አቀፍ ፈተናን ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ለማስፈተን ፍላጎት ያለው ማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤት የተደራጀ የኮምፒዉተር ላብራቶሪ ሊኖረው ግድ ይለዋል። ይሄውም
1. ዴስክቶፕ ወይም ላፕቶፕ ኮምፒዉተሮች
2. የዉስጥ ኔትዎርክ ያለዉ (የገመድ) ኔትዎርክ/Local Area Network /
3. የኢንተርኔት መስመር ከበቂ ባንድዊድዝ ጋር እንደ የመፈተኛ ኮምፒዉተር ብዛት
4. የባክ አፕ ፓዎር (ጄኔሬተር)
ጋር አሟልተው መገኘትና ለትምህርት ቢሮዎች በማሳወቅ በቢሮዎች በኩል መሟላቱ ሲረጋግጥ የፈተና ማእከል በመሆን ተማሪዎቹን ማስፈተን እንደሚችሉ እያሳውቅን ለፈተና የሚዘጋጁት ዴስክቶፕ እና ላፕቶፕ ኮምፒዉተሮች ማሟላት ያለበቸዉ ትንሹ ስፔስፊኬሽን እንደሚከተለው ቀርቧል።
1. RAM --------------- 4GB or higher
2. Storage --------------250GB or higher
3. Processor Speed -------- 2.5GHZ or higher
4. Processors ---------- Intel Core i3 or higher
5. OS --------------- Windows 10
6. Browsers ---------------Safe Exam Browser and other
7. Accessories ---------- Keyboards and Mouse for desktop computers.

©ትምህርት ሚኒስቴር

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የተለያዩ የትምህርት ተቋማት ዘንድሮ በኦንላይን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ሞዴል ፈተና እየሰጡ ነው።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ትናንት የሞዴል ፈተና በዩኒቨርሲቲው አፄ ቴዎድሮስ ግቢ ሰጥቷል።

ትምርት ቤቱ በተያዘው የትምህርት ዘመን በሶሻል እና በተፈጥሮ ሳይንስ በድምሩ 57 ተማሪዎችን ለአገር አቀፍ ፈተና እያዘጋጀ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ12ኛ ክፍል ፈተና ያስቀመጧቸውን ተማሪዎች በሙሉ ካሳለፉ ጥቂት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ ነው።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
«በበዓል ቀናት ሆነ ማግስት የሚወጡ የፈተና ሰሌዳ አግባብነት የሌለው ነው!»

የፌዴራል መጅሊስ ዋና ስራ አስኪያጅ


የ2016 E.C. የሪሚዲያል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመፈተኛ የጊዜ ሰሌዳ ከዒድ አል-አዽሓህ ዐረፋ በዓል ቀን ጋር በሚጋጭ መልኩ ከሰኔ 6 እስከ 10 ይሰጣል።


የተማሪዎች የመፈተኛ የጊዜ ሰሌዳ የሙስሊሙን በዓላት ታሳቢ አድርገው መውጣት አለባቸው ያሉት የፌዴራል መጅሊሱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከማል ሃሩን የበዓል ቀናትን ታሳቢ ያላደረገ የፈተና የጊዜ ሰሌዳ አወጣጥ አግባብነት የሌለውና በተማሪዎች የስነልቦና አልፎም የፈተና ውጤታቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ብለዋል።


መጅሊሱ ባሳለፍነው አመት ጀምሮ በዚህ ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስትር ጋር መነጋገሩ የተገለፀ ሲሆን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም ይሰራል ተብሏል። ሀሩን ሚዲያ በጉዳዩ ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴር መረጃዎችን ለመጠየቅ ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካለት ዘግቧል።

©ሀሩን ሚዲያ

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MOE

ሬሜዲያል ተፈታኞች በሙሉ
የትምህርት ሚኒስቴር የሬሚዲያል (የማካካሻ) ትምህርት የማጠቃለያ ፈተናን ከሰኔ 3-10/ 2016 ዓ.ም ድረስ ለመስጠት የፈተና ፕሮግራም ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጅ ሰኔ 9/ 2016 ዓ.ም የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ስለሆነ በዕለቱ ይሰጥ የነበረው ፈተና ሰኔ 11/2016 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡


🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#BahirDarUniversity

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ ሊያደርግ ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው በፀጥታ ችግርና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ጥሪ ሳያደርግ ቆይቷል።

ረቡዕ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም ውይይት ያደረገው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንዲደረግ መወሰኑን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተቋሙ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡

በዚህም ከሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲው በመገኘት መከታተል ይጀምራሉ ተብሏል፡፡

ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ፣ ትምህርት ሚኒስቴር በልዩ ሁኔታ ፈተና እንደሚያዘጋጅላቸውም ታውቋል።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና በአዲስ አበባ ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።

በከተማዋ የ8ኛ ክፍል ፈተና በ182 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለ86,672 ተማሪዎች እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ መግለፁ ይታወቃል።

ተማሪዎች በጠዋቱ የፈተና ክፍለጊዜ የአማርኛ እና የእንግሊዝኛ ፈተናዎችን የሚወስዱ ይሆናል፡፡

የፈተናውን አሰጣጥ የሚያስፈፅሙ ፈታኞች፣ ተቆጣጣሪዎች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች መመደባቸው ተገልጿል።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በአማራ ክልል በቀጠለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከ180 ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና አለመቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለፀ፡፡

ዛሬ የሚጠናቀቀውን የ8ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና ክልል አቀፍ ፈተና በክልሉ ፈተናውን መውሰድ ከነበረባቸው 369,827 ግማሽ ያህሉ ወይም ከከ180 ሺህ በላይ የሚሆኑት ፈተናውን እንዳልወሰዱ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ 99 ሺህ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና እንደማይቀመጡ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

ግጭቱ ባለባቸው የምዕራብ፣ ምስራቅ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች ያሉ ተማሪዎች ዓመቱን በሙሉ ያልተማሩና ጀምረው ያቋረጡ በመሆናቸው ለፈተናው መቀመጥ እንዳልቻሉ ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡

ነሐሴ መጨረሻ ወይም በቀጣዩ ዓመት መስከረም ወር ላይ የይዘት ክለሳ ተደርጎና የማካካሻ ትምህርት ተሰጥቷቸው ተማሪዎቹ ለፈተና ሊቀመጡ እንደሚችሉ ገልፀዋል፡፡

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ2017 በጀት ክፍፍል

የፌደራል መንግሥት ለ2017 በጀት ዓመት ከያዘው 971.2 ቢሊዮን ብር በጀት ውስጥ 39 ቢሊዮን ብር ያህሉ ከመንግሥት ግምጃ ቤት ወጪ ሆኖ ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲከፋፈል መድቧል።

ለፓርላማ በቀረበ የበጀት ረቂቅ ሰነድ ላይ እንደሚታየው 13 ዩኒቨርሲቲዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ተመድቦላቸዋል።

ራስ ገዙ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመንግሥት መደበኛ በጀት 1.9 ቢሊዮን ብር ተመድቦለታል። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ባህርዳር ዩኒቨርስቲ 1.8 ቢሊዮን ብር ተመድቦለታል።

ከመንግሥት ግምጃ ቤት 1.7 ቢሊዮን ብር የሚሰጠው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በክፍፍሉ ሦስተኛውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የሚያገኝ ይሆናል። ጅማ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች በአራተኛ እና በአምስተኛነት ይከተላሉ።

የፌደራል መንግሥት በጀትን የሚያዘጋጀው የገንዘብ ሚኒስቴር፤ ባለፈው ግንቦት ወር መጀመሪያ ባካሄደው የበጀት ስሚ መርሐግብር ዩኒቨርሲቲዎች “በተቀመጠላቸው ጣሪያ መሰረት” የበጀት ዕቅዳቸውን አስተካክለው እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቶ እንደነበር አይዘነጋም። #ኢትዮጵያ_ኢንሳይደር

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም አጋማሽ ጀምሮ ትምህርት እንዲጀምሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው‼️

🗣ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

በመጪው ዓመት ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም አጋማሽ ጀምሮ ትምህርት እንዲጀምሩ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ።የበጀት ዓመቱ የመጨረሻ የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።

በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አፈፃፀም በስፋት ውይይት የተደረገበት መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገልጸዋል።

በ2016 በጀት ዓመት ከማኅበረሰቡ በተገኘ ድጋፍ በትምህርት ለትውልድ መርሐ ግብር 22 ሺህ የሚደርሱ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታና ጥገና መከናወኑን አስታውቀዋል።በተለይም ለተማሪዎች የሚሰጠው የሪሚዲያል ፈተና መጀመሩን በማስታወቅ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መሰጠት እንደሚጀምር ተናግረዋል።ሐምሌ ወር መጀመሪያ አካባቢ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት እንደሚጀምር የገለጹት ሚኒስትሩ÷ ፈተናውን የተሳለጠ ለማድረግ ለፈታኝ መምህራን በቂ ሥልጠና እየሰተጠ መሆኑንም ገልጸዋል።

ዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በወረቀትና በኦንላይን የሚሰጥ መሆኑን ተከትሎ ለዚህ የሚረዳ በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።በክረምት ወራት 62 ሺህ መምህራንን በሚያስተምሩት ትምህርትና የማስተማር ሥነ ዘዴ ዙሪያ ሥልጠና ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።ሚኒስቴሩ በክረምት ከያዛቸው ሥራዎች መካከል የዩኒቨርሲቲዎች ዕድሳት ሥራ አንዱ በመሆኑ ተግባሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#BahirDarUniversity

በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ለመከታተል ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ሐምሌ 22 እና 23/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ሪፖርት ማድረጊያ ቦታዎች፦

➧ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በፖሊ ካምፓስ
➧ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ ዓባይ ካምፓስ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ የ12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው
➧ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ
➧ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በአረፋ በዓል ምክንያት በቀን 9/10/2016 ዓ.ም ሳይሰጥ የዋለው የሬሜዲያል ፈተና ሰኞ (በ10/10/2016 ዓ.ም) በፊዚክስ እና ማክሰኞ (በ11/10/2016 ዓ.ም) በኬሚስትሪ ፈተና እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡ (ትምህርት ሚኒስቴር)

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ በ2017 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን መዝግበው የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች 1332 የማስተማር ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል።

43 ት/ቤቶች በራሳቸው ጊዜ መቀጠል ስላልቻሉ ፈቃዳቸው መሰረዙን አመልክቷል።

150 ት/ቤቶች ጉዳያቸው በሂደት ላይ ያለ በመሆኑ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል።

41 ትምህርት ቤቶች ደግሞ የትምህርት ፖሊሲውን ባለመጠበቅና ስታንዳርዱን ባለማሟላታቸው ፍቃዳቸው የተሰረዘ መሆኑ ተመላክቷል።

የትምህርት ቤቶቹ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

🔻የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ 🫥

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
🔻https://t.me/Tmhrt_Ministers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM