ትምህርት ሚኒስቴር
97.9K subscribers
281 photos
2 videos
81 files
44 links
ቀዳሚ የተማሪዎች የመረጃ ምንጭ 🇪🇹
Share and Support Us🙏

ማስታወቂያ ለማስነገር በዚህ ያናግሩን
@Adis_probot
Download Telegram
Forwarded from Maraki News
ይመዝገቡ!

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ቀርተዋል።

የተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ የካቲት 30/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።

የመደበኛ እና ማታ መርሐግብር ተማሪዎች ምዝገባ 👉 በትምህርት ቤቶች

የግል | የርቀት | የበይነመረብ ተማሪዎች ምዝገባ 👉 በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ እና በትምህርት ጽ/ቤቶች

በ2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ870 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ይጠበቃል።
@Adis_media
@Adis_media
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Maraki News
በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ በመግባት፣ በመኮረጅና የተለያዩ የፈተና ስነ-ምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሠረዙን እና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑንም ጠቅሷል።

ከየካቲት 6 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119 ሺህ 145 ተፈታኞች ፈተናውን መውሰዳቸው ተጠቁሟል።

ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ሪፎርሞች አንዱ የሆነው መውጫ ፈተና ተመራቂዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ተገቢውን እውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውንና ብቁ መሆናቸውን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ ፈተናው በጥብቅ ዲስፕሊን የሚመራ መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@Adis_media
@Adis_media
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ከ12 እስከ 20 ሺህ ብር ድረስ በእጃቸው ይዘው የተገኙ ተማሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ዋሉ። - ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጋጥሞኛል ካለው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ምሽት የማይገባ ገንዘብ ከኤ.ቲ.ኤም. ማሽን ወጪ መደረጉ ተገልጿል፡፡

ካጋጠመው ችግር ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና ማኅበረሰብ አካላት ገንዘብ ወጪ ሲያደርጉና ወደ ሌላም ሲያስተላልፉ እንደነበር ተነግሯል።

ይህንን ተከትሎ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ያወጡና ያስተላለፉ እንዲመልሱ ተቋማት እያሳሰቡ ይገኛሉ፡፡

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ የነበረ መሆኑን የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጥበቃና ደህንነት ዳይሬክተር ኮማንደር አባዲር ዩያ ገልጸዋል፡፡

ያጋጠመውን የንግድ ባንክ ሲስተም ችግር ተጠቅመው የራሳቸው ያለሆነ ገንዘብ ከATM ለማውጣት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተማሪዎች እንደነበሩ ጠቅሰዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ጥበቃና ደህንነት ተማሪዎች ከዋናው ግቢ እንዳይወጡ ቁጥጥር ሲያደርግ እንደነበረ አመላክተው፣ ሆኖም በተለያዩ ምክንያትና መንገድ የወጡ ተማሪዎች ከግቢ ውጪ ካሉ ማሽኖች ብር የወሰዱ መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡

በተማሪ እጅ ይገኛል ተብሎ የማይገመት ከ12 እስከ 20 ሺህ ብር ድረስ በእጃቸው ይዘው የተገኙ ተማሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮማንደር አባዲር ጠቁመዋል፡፡

አያይዘውም ንግድ ባንክ ያጋጠመውን ችግር ተከትሎ ተሳስተው ገንዘብ የራሳቸው ያደረጉ ተማሪዎች በአስቸኳይ ብሩን ሳያጠፉ እንዲመልሱ አሳስበዋል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተመዝግበዋል፡፡ - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ የተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 3-30/2016 ዓ.ም መከናወኑ ይታወቃል፡፡

በዚህም ፈተናውን ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ መካሔዱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ ተካሒዶ መጠናቀቁን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በዚህ ሳምንት እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡

የፈተና ዝግጅት ሥራው ተማሪዎቹን በአግባቡ ለመመዘን በሚያስችል መልኩ ጠቀሱት ኃላፊው፤ በቀጣይ የፈተናው ሕትመት ይጀመራል ብለዋል።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ወደፊት ይፋ ይሆናል ተብሏል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
ከንግድ ባንክ በወሰዱት ገንዘብ ላፕቶፕ እና ዘመናዊ ስልኮችን የገዙ ተማሪዎች ገንዘቡ መመለስ አለበት መባሉን ተከትሎ ጭንቅ ላይ ናቸዉ ተባለ!

ቢቢሲ በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች ያሉ ተማሪዎችን በማናገር ባገኘው መረጃ መሠረት በርካታ ተማሪዎች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺዎች የሚቆጠር የራሳቸው ያልሆነ ብር ከባንኩ ለመውሰድ ችለው ነበር።

ችግሩ ከተከሰተ በኋላ ባንኩ ከዩኒቨርስቲዎች እና ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ገንዘቡን ለማስመለስ እያደረገ ባለው ጥረት፣ ጥቂት የማይባሉ ተማሪዎች በእጃቸው ላይ የቀረውን ብር መመለሳቸው ቢነገርም ለተለያዩ ጥቅም ያዋሉት ግን ግራ በመጋባት በቀጣይ የሚመጣውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ በተፈጠረው ችግር የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ የወሰዱ ተማሪዎች ሂደቱን “ሥራ” በሚል ቃል ነበር የገለጹት። ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪም “እኔ ወደ 150 ሺህ ብር ሠርቻለሁ። 300 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ የሠሩ ተማሪዎች አሉ። . . . ቀድሞ የሰማ [የሲስተም ብልሽቱን] ብዙ ሠርቷል” ብሏል።

ተማሪው አክሎም በዕለቱ “150 ሺህ ብር ‘ሠርቼ’ ነበር። ሁሉንም ብር ተመላሽ አድርጊያለሁ። ወደ ሌላ ባንክ ያዘዋወሩ ጓደኞቼ ግን ጭንቀት ላይ ናቸው” ሲል የተፈጠረውን ሁኔታ መግለጹን ከዘገባው ተመልክተናል። ንግድ ባንክ በገንዘብ ዝውውር ሥርዓቱ ላይ ብልሽት ከማጋጠሙ በፊት በሂሳቡ ውስጥ የነበረው ከ5 ሺህ ብር በታች እንደነበረ የሚገልጸው ይህ ተማሪ፣ የተፈጠረውን ክፍተት እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ 150 ሺህ ብር መውሰዱን አምኗል። ባንኩ ችግሩ መከሰቱን ተከትሎ ያላግባብ ብር የወሰዱ ደንበኞቹ ተመላሽ እንዲያደርጉ ባሳሰበው መሠረት እና ከዩኒቨርስቲው በኩል በወጣው ማስጠንቀቂያ ምክንያት ተማሪው ገንዘቡን መመለሱን ተናግሯል።

በድንገት እጃቸው ላይ የገባውን ከፍተኛ መጠን ያለውን ገንዘብ የተለያዩ እቃዎች የገዙበት ወይም ከንግድ ባንክ አካውንታቸው ወደ ሌላ ባንክ ገንዘብ ያዘዋወሩ ተማሪዎች ደግሞ ከፍተኛ ጭንቀት ላይ ይገኛሉ።

ተማሪው እንደሚለው የሲሰተም ብልሽት ባጋጠመበት ወቅት ካላቸው ገንዘብ በላይ ወደ ሌላ ባንክ ገንዘብ ያዘዋወሩ ተማሪዎች የባንክ ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ በመደረጉ ገንዘቡን ለመመለስ ባለመቻላቸው በግራ መጋባት ጭንቀት ውስጥ ይገኛሉ ብሏል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲው ተማሪ እንደሚለው ብዙ ጓደኞቹ በወሰዱት ገንዘብ የተለያዩ ውድ ነገሮችን በመግዛታቸው ገንዘቡን መልሰው ማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ ስላሉ ጭንቀት ላይ ይገኛሉ ይላል።

በተለይ ላፕቶፕ እና ዘመናዊ ስልኮችን የገዙ ተማሪዎች ጥቂት አለመሆናቸውን የሚጠቅሰው ተማሪው “100ሺህ ብር የሠራ አንድ ልጅ በሁለተኛው ቀን ላፕቶፕ እና ስማርት ስልክ ገዝቷል” በመግዛቱ እጁ ላይ የሚመልሰው ገንዘብ እንደሌለ ገልጿል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
Forwarded from Maraki News
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።

የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡

ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡
@Adis_media
@Adis_media
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
አንድ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ የግድ ሊያውቃቸው የሚገቡ የማትስ ፎርሙላዎች!!!


1. Pythagorean theorem: a² + b² = c²

2. Quadratic formula: x = (-b ± √(b² - 4ac)) / 2a

3. Distance formula: d = √((x₂ - x₁)² + (y₂ - y₁)²)

4. Slope-intercept form of a line: y = mx + b

5. Point-slope form of a line: y - y₁ = m(x - x₁)

6. Midpoint formula: ((x₁ + x₂)/2, (y₁ + y₂)/2)

7. Law of sines: a/sin A = b/sin B = c/sin C

8. Law of cosines: c² = a² + b² - 2ab cos C

9. Sum of angles in a triangle: A + B + C = 180°

10. Area of a triangle: A = (1/2)bh

11. Volume of a sphere: V = (4/3)πr³

12. Volume of a cylinder: V = πr²h

13. Volume of a cone: V = (1/3)πr²h

14. Surface area of a sphere: A = 4πr²

15. Surface area of a cylinder: A = 2πr² + 2πrh

16. Surface area of a cone: A = πr² + πrs, where s is the slant height

17. Binomial theorem: (a + b)ⁿ = Σ(n choose k)a^(n-k)b^k, where Σ is the sum from k=0 to n, and (n choose k) is the binomial coefficient

18. Fundamental theorem of calculus: ∫a^b f(x) dx = F(b) - F(a), where F is the antiderivative of f

19. Derivative of a constant: d/dx(c) = 0

20. Power rule for derivatives: d/dx(xⁿ) = nx^(n-1)

21. Product rule for derivatives: d/dx(fg) = f'g + fg'

22. Quotient rule for derivatives: d/dx(f/g) = (f'g - fg')/g²

23. Chain rule for derivatives: d/dx(f(g(x))) = f'(g(x))g'(x)

24. Mean value theorem: if f is continuous on [a,b] and differentiable on (a,b), then there exists c in (a,b) such that f'(c) = (f(b) - f(a))/(b-a)

25. Intermediate value theorem: if f is continuous on [a,b], then for any y between f(a) and f(b), there exists c in [a,b] such that f(c) = y

26. Rolle's theorem: if f is continuous on [a,b] and differentiable on (a,b), and if f(a) = f(b), then there exists c in (a,b) such that f'(c) = 0

27. Integration by substitution: ∫f(g(x))g'(x) dx = ∫f(u) du, where u = g(x)

28. Integration by parts: ∫u dv = uv - ∫v du

29. L'Hopital's rule: if lim(x → a) f(x)/g(x) = 0/0 or ∞/∞, then lim(x → a) f(x)/g(x) = lim(x → a) f'(x)/g'(x)

30. Taylor series: f(x) = Σ(n=0 to ∞) f^(n)(a)/n!(x-a)^n, where f^(n) is the nth derivative of f

31. Euler's formula: e^(ix) = cos(x) + i sin(x)

32. De Moivre's theorem: (cos x + i sin x)^n = cos(nx) + i sin(nx)

33. Fundamental trigonometric identities: sin² x + cos² x = 1, 1 + tan² x = sec² x, 1 + cot² x = csc² x

34. Double angle formulas: sin 2x = 2sin x cos x, cos 2x = cos² x - sin² x, tan 2x = (2tan x)/(1 - tan² x)

35. Half angle formulas: sin(x/2) = ±√((1 - cos x)/2), cos(x/2) = ±√((1 + cos x)/2), tan(x/2) = ±√((1 - cos x)/(1 + cos x))

36. Sum-to-product formulas: sin A + sin B = 2sin((A+B)/2)cos((A-B)/2), cos A + cos B = 2cos((A+B)/2)cos((A-B)/2), sin A - sin B = 2cos((A+B)/2)sin((A-B)/2), cos A - cos B = -2sin((A+B)/2)sin((A-B)/2)

37. Product-to-sum formulas: cos A cos B = (1/2)(cos(A-B) + cos(A+B)), sin A sin B = (1/2)(cos(A-B) - cos(A+B)), sin A cos B = (1/2)(sin(A+B) + sin(A-B)), cos A sin B = (1/2)(sin(A+B) - sin(A-B))

38. Hyperbolic functions: sinh x = (e^x - e^-x)/2, cosh x = (e^x + e^-x)/2, tanh x = sinh x/cosh x

39. Inverse trigonometric functions: arcsin x, arccos x, arctan x

40. Logarithmic identities: log(xy) = log x + log y, log(x/y) = log x - log y, log x^n = n log x

41. Exponential identities: e^x+y = e^x e^y, (e^x)^n = e^(nx), e^0 = 1

42. Binomial coefficients: (n choose k) = n!/(k!(n-k)!)

43. Pascal's triangle: each entry is the sum of the two entries above it

44. Fermat's little theorem: if p is a prime and a is not divisible by p, then a^(p-1) ≡ 1 (mod p)

45. Chinese remainder theorem: if m₁, m₂, ..., mₙ are pairwise coprime integers and a₁, a₂, ..., aₙ are any integers, then there exists an integer x that satisfies the system of congruences x ≡ a₁ (mod m₁), x ≡ a₂ (mod m₂), ..., x ≡ aₙ (mod mₙ)
@Timihirt_Minister
ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓት ተግባራዊ ሊደረግ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም ተቋማት በፋይናንስ አጠቃቀማቸው እንጂ በአፈፃፀም ተጠያቂ የሚሆኑበት ስርዓት አልነበረም፡፡

ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተቋማት በአፈፃፀማቸው ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር መተግበር እንደሚጀምር በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡ 

በዚህም በተጠያቂነት የአሰራር ስርዓት መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPI) ላይ ውል በማድረግ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ ገልፀዋል።

የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓቱ ተመዝነው የተሻለ አፈጻጻም ያስመዘገቡ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዕውቅና እንዲያገኙ እንዲሁም ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸው ደግሞ የማስተካከያ ዕርምጃዎች የሚወስዱበት አግባብ የሚፈጠርበት መሆኑንም አስረድተዋል።
@Timihirt_Minister
የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መካከለኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ፈተናዎቹ በተጠቀሱት ቀናት በጠዋት እና ከሰዓት መረሐግብር እንደሚሰጡ ቢሮው ያወጣው የድርጊት ጊዜ ሰሌዳ ያሳያል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?

2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ በርካቶች ጥያቄ አድርሰውናል።

12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ እንዳደረጉ መገለፁም ይታወሳል፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ለማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?

ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ አሳውቋል።
@Timihirt_Minister
በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎች እያንዳንዳቸው የአገልግሎት ክፍያ 500.00 (አምስት መቶ) ብር ብቻ የሚከፍሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

በዚህም ተፈታኞች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000553176097 በመጠቀም እስከ ማክሰኞ ሚያዚያ 15/2016 ዓ.ም ድረስ ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ተፈታኞች የከፈሉበትን ደረሰኝ ኮፒ በኢሜይል አድራሻ antedefar@gmail.com እና lakbt2013@gmail.com መላክ ይኖርባቸዋል።

(ተጨማሪ መረጃ ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ።)
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር

የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ በየነ ተዘራ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ለ15 ቀናት በኦንላይን፣ በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ለመስጠት እየተሠራ እንደሆነም ገልፀዋል፡፡

ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡

የሪሚዲያል ትምህርት ከታህሳስ ጀምሮ እስከ ሰኔ 2016 ዓ.ም መጨረሻ እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን ውጤታቸው 30 በመቶ በዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት ሒደት እና 70 በመቶ በማዕከል በሚዘጋጅ ፈተና የሚለይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
ፈተናው በኦላይን ይሰጣል

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።

የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
@Timihirt_Minister