TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AdigratUniversity

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ 414 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የማስፋፊያ ግንባታዎች እያካሔደ መሆኑን አስታወቀ። የዩኒቨርስቲው የግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ኪደይ ገብረማርያም ለኢዜአ  እንዳሉት፣ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ተማሪዎች፣መምህራንና የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ ውብና ጽዱ የሆነ አከባቢ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው።

https://telegra.ph/ETH-10-29-4

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AdigratUniversity

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ8ኛ ጊዜ 2,576 ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በትግራይ በነበረው ጦርነት ውድመት ደርሶበት ስለነበር ተማሪዎቹ ቀሪ ትምህርታቸውን በመቐለ ዩንቨርስቲ እንዲያጠቅቁ ተደርጎ ነው ዛሬ እየተመረቁ የሚገኙት።

በሌላ በኩል በቅርቡ ተማሪዎችን ያስመረቀው መቐለ ዩኒቨርስቲ ቀሪ 608 ተመራቂ ተማሪዎችን በ2ተኛ ዙር እያስመረቀ እንደሚገኝ ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
" ለመምህራንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የመጋቢት ጨምሮ የ4 ወራት ደምወዝ ተከፍሏል " - ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ስራ ለመጀመር የሚያስችለው የዩኒቨርሲቲ ካዉንስል ስብሰባ ትላንት በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ አከናውኖ ነበር።

በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው አመራር አባላት ባካሄዱት ውይይት ስራ ለመጀመር የሚያስችል የሶስት ወራት እቅድ ስለማዘጋጀት አስፈላጊነት ስምምነት ተደርሶበታል።

በውይይቱ ወቅት በየደረጃው የተቀናጀ ጥረት በማድረግ ዩኒቨርሲቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን መልሶ ለመቀበል ወደሚችልበት ደረጃ ማድረስ እንደሚቻል ግንዛቤ ተወስዷል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሁሉም ኮሌጆች፣ ትምህርት ክፍሎች፣ ዳይሬክተሮችና ሌሎች ፅ/ቤቶች መደበኛ ስራቸው እንዲጀምሩ መመርያ ተሰጥታል።

ዩኒቨርሲቲው ለመምህራንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የመጋቢት ጨምሮ የአራት ወራት ደምወዝ የከፈለ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

#AdigratUniversity

@tikvahethiopia
#AdigratUniversity

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በላከልን መልዕክት ፦

1. የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ሆናችሁ ላላፉት ሁለት ዓመታት በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድባችሁ የመማር እድል ያላጋጠማችሁ፤

2. በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ መርሃ ግብር ተማሪዎች፤

3. በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛነት ስትማሩ ቆይታችሁ፣ ላለፉት ሁለት አመታት አቛርጣችሁ አሁን ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመመዝገብ የምትፈልጉ ተማሪዎች፤

በዚህ ማስፈንጠሪያ http://197.156.104.178/ በኦንላይን የቅድመ ምዝገባ ቅፅ ከግንቦት 03 አስከ 15/2015 እንድትሞሉ ጥሪ አቅርቦላችኃል።

ዩኒቨርሲቲው ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AdigratUniversity

በጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ስራ ዳግም ለማስቀጠል ሲደራ የነበረው ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለሁሉም መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አደረገ።

ዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎቹን በሙሉ (የድህረ ምረቃ ተማሪዎችን ጨምሮ) ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 01/2015 ዓ.ም እንደሚቀበል አሳውቋል።

በመሆኑም መደበኛ ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በዋናው ግቢ በመገኘት እንዲመዘገሹ ተብሏል።

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦

- የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተማሪ መታወቂያ ካርድ
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላና ትራስ ጨርቅ
- ጉርድ ፎቶግራፍ (4)

የመደበኛ መርሃ ግብር ላልሆኑ ተማሪዎች በቅርቡ ጥሪ እንደሚደረግ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው ጥሪ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity