TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ከሰኔ 11ዱ ጥቃት የተረፉ ወገኖች ችግር ላይ ናቸው ! በምዕራብ ወለጋ ዞን በጊምቢ ወረዳ ፣ ቶሌ ቀበሌ የሚገኙ ነዋሪዎች ከሰኔ 11ዱ ጥቃት የተረፉ ነዋሪዎች አስፈላጊውን የምግብ እርዳታ ስላላገኙ ችግር ላይ ይገኛሉ። ነዋሪዎቹ ቤት ንብረታቸው ከመውደሙ ባሻገር ንግዳቸው እንዲሁም የቀንድ ከብቶቻቸው ስለተዘረፉ የምግብ ችግር እንደገጠማቸው እየተናገሩ ነው። ቤት ንብረታቸው የወደመባቸው ሰዎች ዘመዶቻቸው…
#UN

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምዕራብ ወለጋ የተፈጸመውን አሰቃቂ የጅምላ ግድያ ላይ ባለሥልጣናት ፈጣን፣ ገለልተኛ እና ጥልቅ ምርመራ እንዲያካሂዱ ጠየቀ።

የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ኃላፊ ሚሼል ባችሌት " በቶሌ መንደር የተፈጸመው የጭካኔ ግድያ እና የነዋሪዎች በጥቃቱ ምክንያት ተገድዶ መፈናቀል ዘግንኖኛል " ብለዋል።

ቅዳሜ ዕለት ምዕራብ ኦሮሚያ ውስጥ የተፈጸመው ጥቃት እማኝን ባልደረባቸው እንዳነጋገሩ እና ወደ መንደሩ የገቡት ታጣቂዎች በነሲብ ተኩስ ከፍተው ብዙዎችን እንደገደሉ መረዳታቸውን ገልጸዋል።

ከሟቾቹ አብዛኞቹ #ሴቶች እና #ሕጻናት መሆናቸውን እንዲሁም ቢያንስ 2 ሺ ሰዎች ከአካባቢው ለመሸሽ መገደዳቸውን አመልክተዋል።

4 ሰዓት በፈጀው ጥቃት ታጣቂዎቹ በርካታ ቤቶችን ማቃጠላቸውንም ገልፀዋል።

በጥቃቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች መገደላቸውን አስከሬን አሁንም በመንገዶች ላይ ወድቀው ሊገኙ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ባችሌትም ባለሥልጣናት " ጥቃቱ በአፋጣኝ መጣራቱን፤ ሰለባዎች እና ቤተሰቦቻቸው እውነት፣ ፍትህ እና ካሣ የማግኘት መብታቸውን እንዲሁም አጥፊዎችን በተጠያቂነት መያዛቸውን እንዲያረጋግጡ " ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች በጥቃቱ ወቅት መታገታቸውን እና ያሉበት እንደማይታወቅም አጽንኦት በመስጠት ባለሥልጣናት የታገቱት ነጻነታቸውን እንዲያገኙ አስፈላጊ እና ሕጋዊ ርምጃዎችን እንዲወስዱም ማሳሰባቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
ቪድዮ ፦ በአሜሪካ ሀገር ቴክሳስ በምትሰኝ ግዛት በምትገኘው " አለን " ከተማ አንድ ታጣቂ በገበያ አዳራሽ ውስጥ በፈጸመው ጥቃት ስምንት (8) ሰዎችን በጥይት ገድሏል።

በታጣቂው ከተገደሉት ውስጥ #ሕጻናት ይገኙበታል።

ከተገደሉት በተጨማሪ ሰባት (7) ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታል ህክምና እየደረገላቸው ሲሆን፣ ከመካከላቸው 3ቱ በጽኑ የተጎዱ ናቸው።

ታጣቂው በጅምላ ባገኘው ሰው ላይ በከፈተው ተኩስ ግድያውን የፈጸመ ሲሆን፣ በገበያ አዳራሹ ውስጥ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች ድጋፍ እንዲወጡ ተደርገዋል።

ታጣቂው እዚያው ጥቃቱን በፈጸመበት ስፍራ በፖሊሶች ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን፣ ጥቃቱን የፈጸመው ብቻውን እንደሆነ እንደሚታመን ቢቢሲ ዘግቧል።

እንደ Gun Violence Archive ድረገፅ መረጃ በአሜሪካ ሀገር ከጦር መሳሪያዎች ጋር በተያያዘ በየዓመቱ #አርባ_ሺህ (40,000) ሰዎች የሚሞቱ ሲሆን ይህ በመሳሪያዎች እራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎችን ያካታታል።

ቪድዮ ፦ Fox News

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ " #አራ " ከሚባል ስፍራ 77 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ መገልበጧ መገለጹ ይታወሳል።

በዚህም አደጋ የ5 ዓመት #ሕጻናት እና #ሴቶችን ጨምሮ 16 ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ መገለጹ አይዘነጋም።

የIOM የጅቡቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ታንጃ ፓሲፊክ ፤ የሟቾች ቁጥር ቀደም ሲል ከሰጠው መረጃ ማለትም 16 ከፍ ማለቱንና 21 መድረሱን ተናግረዋል።

የሞቱት ሁሉም #ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል።

23 ሰዎች አሁንም ድረስ የት እንደገቡ እንኳን አይታወቅም ብለዋል።

33 ሰዎች ከአደጋው እንደተረፉ ገልጸዋል።

ይህ አደጋ #38_ኢትዮጵያውን ከሞቱበት አደጋ ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተከሰተ ነው።

በርካታ ሰዎች በተለይም ወጣቶች ህይወታቸውን ለመቀረ ሲሉ በአደገኛው እና ህገወጥ በሆነው መንገድ ሀገራቸውን ጥለው ይሰደዳሉ ፤ በዚህም ህይወታቸውን ባህር ላይ ያጣሉ ፣ ይታሰራሉ፣ በየበረሃው ይንገላታሉ ፣ በደላሎች ታግተው ይሰቃያሉ ።

ሀገር ጥለው በህወጥ መንገድ የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይታይም።

@tikvahethiopia
#Axum #Tigray

" በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው ከባድ ነበር !! "

ወ/ሮ በላይነሽ መኣሾ (የአክሱም ነዋሪ ለድምጺ ወያነ) ፦

" ሰላም በመሆኑ ጥሩ ነው ያለው።  ብርሃን አየን።

በሰላም እየተንቀሳቀስን ነው። #ሕጻናት እየተጫወቱ ነው።

ብዙ ለውጥ ነው ያለው።

በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው እጅግ ከባድ ነበር። አሁን በጣም በጣም ይሻላል ፤ ቢያንስ #እፎይ ብለን  መተኛት እንችላለን።

ቢሆንም ግን #የከፋው_ሰው_አለ ፤ ሰው የሚበላው የሚጠጣውን አጥቶ በጣም ከፍቶታል ፣ የመንግስት ሰራተኛውም ያለፉት ዓመታት ደመወዝ ባለመከፈሉ ለተለያዩ ችግሮች ተጋልጦ ነው ያለው ፣ የተፈናቃዮች ነገርማ #አይወራምሕጻናት ልጆች የሚበሉትን አጥተው በየከተማው #በልመና ነው ተሰማርተው ያሉት። "

#Ethiopia #TigrayRegion #Peace

@tikvahethiopia