TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ🔝

‹‹እኛ ተማሪዎች ለህዝባችን አንድነት ምሰሶ ፤ #ለችግሮቻችን መፍቻ ቁልፍ እንጂ ለቁርሾዎች መነሻ መሆን የለብንም። ተማሪዎች ህዝባችንን #በድህነት ያስቀሩ ድክመቶቻችን የምንቀርፍ ኃይሎች እንጂ የቁርሾ መመስረቻዎች መሆን አንፈልግም፡፡›› የደብረ ማርቆስ ተማሪዎች

ተማሪዎቹ በትላንትናው ዕለት ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ #አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦች ተነስተዋል፡፡

• የአማራ እና ኦሮሞ ህዝቦች አንድነት #ለኢትዮጵያውያን ደኅንነት እንዲሆን አሻራችንን እናሳርፋለን ። እኛ አንድ ህዝቦች ነን ። አንድ ህዝብ መሆናችን ዩኒቨርሲቲዎች ምሳሌ እንዲሆኑ እንሰራለን ።

• እኛ ተማሪዎች ህዝባችንን በድህነት ያስቀሩ ድክመቶቻችን የምንቀርፍ ሀይሎች እንጂ የቁርሾ መመስረቻዎች መሆን አንፈልግም።

• ወደ ቤተሰቦቻችን ይዘን የምንመለሰው #ፍቅር እና #መፍትሄን እንጂ #ልዩነት አይሆንም።

• የምንማረው ህዝባችንን በፍቅር ለመምራት ነው ፤ #አንድነታችንን የሚያሳጡ ሀሳቦች እንዳይተባበሩ እናድርግ።

• ደም የመተካኪያ ፍሬ እንጂ ከዛሬ በኋላ የልዮነት ሀሳብ ሁኖ #ለሚከፋፍሉን እድል ሰጥቶ ወደኋላ የሚመልሰን ሊሆን አይገባም።

በደም ተለያይተን በድህነት ውስጥ መኖር በለውጡ ትውልድ አይቀጥልም፤ የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ግቢያቸው ላይ በማድረግ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia