TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት የሰየመውን ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሽብርተኝነት ስያሜ #ይነሳ #አይነሳ በሚለው ጉዳይ ላይ ዛሬ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በምክር ቤቱ ውስጥ የብልፅና አባላት ሕወሓትን ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ያለመ ዝግ ስብሰባ ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔን ጨምሮ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ…
#Update

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#TPLF

" ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " - ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል።

የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ " የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

ምክር ቤቱ ህወሓትን ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ያነሳው የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ ነው።

በስምምነቱ አንቀጽ 7/2 C መሰረት የፌዴራል መንግሥት በህወሓት / TPLF / ላይ የተጣለውን የሽብርተኝነት ስያሜ በምክር ቤቱ እንዲነሳ ሁኔታዎችን እንደሚያመቻች ይገልጻል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " - ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል። የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ " የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ…
#TPLF

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የዛሬው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር።

ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን #ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል።

5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።

በዚህም #በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት ይነሳ የሚለው የውሳኔ ሃሳብ ፀድቋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔውን ተከትሎ ባሰራጨው መረጃ ፤ " በህወሓትና በፌደራል መንግስት በኘሪቶሪያ የተደረገውን ሥምምነት ለማጽናት ህወሐትን ከሽብርተኝነት ስያሜ ማንሳት #አማራጭ_የሌለው ጉዳይ መሆኑን የውሳኔ ሃሳቡ በቀረበበት ወቅት ተነስቷል " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) እና የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅደስት ሥላሴ ካተድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) መግለፃቸውን የኢኦተቤ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥ እና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ትላንት ከዚህ ዓለም በሞተ ስጋ መለየታቸው መገለፁ ይታወቃል።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ/ም ምሽት ነበር ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ከ፲፯ ዓመታት በፊት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእረ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ የተሾሙ ነበሩ።

ብፁዕነታቸው አስኬማ መላእክት ከሚለበስበት የኤጲስ ቆጶስነት ሹመት በፊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች ሲያገለግሉ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል።

ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ በኒውዮርክ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ከአገልጋይነት እስከ የበላይ ጠባቂነት በአባትነት አገልግለዋል።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ነበሩ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የሚከበሩት እና የሚታወቁት የአካባቢ ጉዳይ ሳይንቲስት ዶክተር ተወልደብርሃን ገብረ እግዚአብሔር የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ተፈፅሟል።

ስርዓተ ቀብራቸው በአዲስ አበባ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ነው የተፈፀመው።

ዶ/ር ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሔር ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ/ም ሕይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የዛሬው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር። ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን #ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል። 5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል። በዚህም #በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ…
#TPLF

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ እንዲሁም የፌዴራል መንግስትን ወክለው ከህወሓት ጋር የተደራደሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ስለ ህወሓት / TPLF ከሽብርተኛ ድርጅትነት ዝርዝር መሰረዝ በተመለከተ ምን አሉ ?

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦

" #ሠላም ሰጥተን የምንቀበለው በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ያሉ ቅሬታዎችን በይቅርታ በማለፍ የትግራይም ማህበረሰብ የሀገራችን አካል በመሆኑ፣ ዜጎች ማግኘት የሚገባቸውን አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የትግራይ ሕዝብ በም/ ቤቱ መቀመጫ አግኝተው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እኩል እንዲወስኑ እና እንዲሳተፉ ዕድል መስጠት የሚያስችል የሠላም ስምምነቱ አካል በመሆኑ የህወሓትን የአሸባሪነት ስያሜ ማንሳት ያስፈልጋል።

ሌሎች ቀሪ ስራዎች አካታች ሀገራዊ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት በሀገራችን ዘላቂ ሠላም ለማስፈን ይሰራል። "

ህወሓት በህ/ተ/ም/ቤ ከአሸባሪ ድርጅትነት በ61 ተቃውሞ ፣ በ5 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
" ከአሸባሪነት መሰረዙን በፅኑ እቃወማለሁ " - ኢዜማ

ኢዜማ የህወሓትን ከአሸባሪነት መሰረዝ " በፅኑ እቃወማለሁ " አለ።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የህ.ወ.ሓ.ት ከሽብርተኝነት መሰረዝን በተመለከተ ውሳኔውን በመቃወም መግለጫው አውጥቷል።

በዚህ መግለጫው ፤ " ህወሓትን ከሽብርተኝነት መሰረዝ ዘላቂ ሰላምን፣ እፎይታንና ቅቡልነትን የሚያመጣ አይደለም " ብሏል።

ፓርቲው የ " ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መሰረዝ የተቃወመባቸውን ምክንያቶች በዝርዝር ያሳወቀ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ፦

- ህወሓት በፕሪቶሪያው ስምምነት አንቀጽ 6 መሠረት ትጥቅ ሙሉ በሙሉ አልፈታም።

- በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የትግራይን የሽግግር መንግሥትን የፌደራሉ መንግሥት በበላይነት እንዲያቋቁም ስምምነት ላይ ቢደረስም አሁንም ህወሓት በብቸኝነት የሽግግር መንግሥቱ አውራ ሆኗል ፤ ይኽም ህወሓት ዳግም የሀገር ስጋት የሚኾንበትን ዕድል እንደመስጠት የሚቆጠር ነው።

- በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ያዘዙ፣ ሰብዓዊ ቀውስ ያደረሱ፣ ዜጎችን በጦርነት እንዲማቅቁ ያደረጉ፣ የሀገር ኢኮኖሚና፣ በአጠቃላይ ኢትዮጵያን ቀውስ ውስጥ የከተቱ የሕወሓት አመራሮች በሕግ አልተጠየቁም።

- በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የሀገር መከላከያ ሠራዊት ሙሉ በሙሉ ትግራይን እንዲቆጣጠር አልተደረገም።

- የተጨፈጨፉ የሰሜን ዕዝ አባላት የመስዋዕትነት ምልክት የሚኾን ሐውልት ወይም ማስታወሻ በሰሜን ዕዝ ዋና ማዘዣ አልተደረገም።

- በህወሓት ቆስቋሽነት ሀገራችን ላይ ለደረሰው ውድመትና ሰቆቃ ፍትሕ እና ካሣ አልተሰጠም የሚሉት ይገኙበታል።

ኢዜማ ህወሓት የሚለው የፖለቲካ ድርጅት ስም በሕግ እንዲታገድ አለመደረጉ ከላይ የተዘረዘሩ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሟሉ ቡድኑ ከሽብርተኝነት ሰርዞ ከተጠያቂነት ነፃ ማድረግ ሊቀለበስ የማይችል ጥፋት ነው ብሏል።

ከዚህ በኋላ በ " ህወሓት " አማካኝነት ለሚደርስ ሀገራዊ ጉዳትም ዋነኛ ተጠያቂዎች ገዢው " የብልጽግና ፓርቲ እና መንግሥት " እንደሚኾኑ ከወዲሁ እንገልጸለን ሲል አሳውቋል።

ምክር ቤቱ ሌላው ቢቀር በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ግዴታዎች አየተፈፀሙ መሆኑን በቅጡ ሳያረጋግጥ፣ ህወሓት በኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት ላይ ለፈጸመው የሀገር ክህደት ወንጀል ተጠያቂ ሳይሆን እና በህወሓት የእብሪት ጦርነት የግፍ ገፈት ቀማሽ ለሆኑ በተለይ በትግራይ፣ በአማራና በአፋር ለሚገኙ ወገኖቻችን ፍትሕ ሳይሰጥ ቡድኑን ከሽብርተኝነት መዝገብ እንዲሰረዝ መወሰኑ ታሪክ ይቅር የማይለው ፍርደ ገምድልነት ሲል ውሳኔውን አውግዟል።

ሕወሓት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አባላትን በመጨፍጨፍ የሀገር ክህደት ፈጽሟል ያለው ኢዜማ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የተከሰተው ጦርነት እና እሱን ተከትሎ ለደረሰው ሀገራዊ ቀውስ ቁጥር አንድ ተጠያቂ ህወሓት ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጿል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia