TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Lion #Wegagen አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በሽረ እንደስላሴና አካባቢው የሚገኙት ቅርንጫፎቹ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን በዛሬው ዕለት አሳውቋል። በሌላ በኩል ፤ ወጋገን ባንክ በግጭት ምክንያት አገልግሎት ተቋርጦባቸው በቆዩት በአላማጣና በራያ ጥሙጋ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጿል። ባንኩ ሰቲት ሁመራ፣ አዲ ረመፅ ፣ ዳንሻ  እና ተከዜ ቅርንጫፎች ቀደም ብለው አገልግሎት…
ወጋገን ባንክ ትላንት በመቐለ በ28 ቅርንጫፎች ስራ ጀምሯል።

ባንኩ መስጠት የጀመረው አገልግሎት ከባንክ ሂሳብ ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ከክልሉ ውጭ የተላከ ገንዘብ መቀበል ናቸው።

የባንኩ የመቐለ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሃፍቶም ገ/እግዚአብሔር ለቪኦኤ የሰጡት ቃል ፦

" ከፌዴራል ሲስተም ጋር በማያያዝ ማንኛውም ተቀማጭ የነበረውን ደንበኛ ገንዘብ መውሰድ ይችላል በቀን እስከ 1,500 ብር ይሄንን ስንል ከአዲስ አበባ ከሌላም ቦታ በተለይ ከትግራይ ክልል ውጭ ያለው ማንኛውም ገቢ ያደረገ ወደ ሂሳብ እሱን እያየን መክፈል እንችላለን። ከዚህ በተጨማሪ የውጭ ሀዋላም ጀምረናል።

መቐለ የጀመርነው በ28 ቅርንጫፎቻችን ነው፤ ብሩ በጣም ትንሽ ነው፤ ሰጠን ብለንም አናስብም ዞሮ ዞሮ ግን ያሉንን ደንበኞችና ድርጅቶች እነሱን በማስተባበር የተወሰነ ገቢ ስላደረጉልን ይሄንን ገቢ በዓልም ከፊታችን ስላለ ህዝባችን የነበረውን ችግር በመጠኑ በጣም በትንሹ እንኳን ለበዓል ለዶሮም ይሁን፣ ለስጋ ይጠቅማል ከሚለው እሳቤ ስለሆነ ነው ይበቃል የሚል እምነት ግን የለንም።

ከፌዴራል ብር እየጠየቅን ስለሆነ ሲመጣ ህዝባችንን እንክሳለን።

...አሁን ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እሱን እያስተካከልን ነው በዚህ ሁለት ቀን እጀምራለን። በቀጣይ የATM እና ሞባይል ባንኪንግና ኢንተርኔት ባንኪንግ እሱን እየጨረስን ነው ከዚህ በፊት ጉዳት የደረሰባቸውን ኤቲኤሞች የእየተካን ነው፤ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ የATM አገልግሎት እንጀምራለን።"

ወጋገን ባንክ ከመቐለ በተጨማሪ ከዛሬ ጀምሮ ኦዲተሮቹን፣ እቃዎቹን እስከ ዓዲግራት ባለው አካባቢ፤ በሌላው መስመር እስከ መኸኒና ዓብይ ዓዲ ያሉት ቅርንጫፎቹ እንደሚያደርስ ገልጿል። በሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የቀሩት ቅርንጫፎች ስራ እንደሚጀምሩ አሳውቋል።

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
ከዘር ማጥፋት እልቂት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ 2 ሺህ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በመስጠት የተጠረጠረው ግለሰብ ተያዘ።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ በነበረው የዘር ማጥፋት እልቂት፣ ከጥቃት ለማምለጥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ ሁለት ሺሕ #ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፏል በሚል የተጠረጠረው ግለሰብ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መያዙን የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት የሚከታተለው፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጦር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።

የቀድሞው የፖሊስ አባል፣ ፉልጌንሴ ካይሼማ፣ ፍ/ቤቱ በይፋ ክሥ ከመሠረተበት ካለፉት 22 ዓመታት ጀምሮ በሽሽት ላይ ነበር።

በተመድ የተቋቋመው ችሎት፣ ሥራውን ለሩዋንዳ በማስረከቡ፣ ካይሼማ፥ ለሩዋንዳ ተላልፎ እንደሚሰጥ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ካይሼማ ያለበትን ለሚጠቁም፣ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

ሌላው የዘር ማጥፋቱ ጠንሳሽ የተባለው ፌሊሲን ካቡጋ፣ ከ26 ዓመታት ሽሽት በኋላ ከሦስት ዓመት በፊት በፈረንሳይ ውስጥ መያዙ ይታወቃል።

እ.አ.አ በ1994 በሩዋንዳ፣ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800ሺሕ የሚሆኑ ቱትሲዎች መገደላቸው ይታወሳል።

#ቪኦኤ #ሩዋንዳ #Genocide

@tikvahethiopia
#ኤርትራ #ሩስያ

የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን #የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ፤ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ እና ፕሬዚደንት ፑቲን ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ቆይታ የአገሮቻቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት፤ ዐለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ትኩረት በሚሰጧቸው ሁኔታዎች ዙሪያ በስፋት መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡

አያያዘውም ፤ “የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ በሩሲያ ፌዴሬሽን ያደረጉት #የመጀመሪያ ጉብኝት ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ፕሬዚደንት ፑቲን አስምረውበታል” ብለዋል፡፡

“የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ርምጃ ሙሉ በሙሉ አመርቂ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ” ፑቲን መናገራቸው አክለው “በመጪው ሐምሌ ወር ሞስኮ በምታስተናግደው ሁለተኛው የሩሲያ እና የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንዲገኙ ጋብዘዋቸዋል” ብለዋል፡፡

የኤርትራ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገሮች ከፍተኛ የአጋርነት እና የምክክር ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መናገራቸውን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረ መስቀል አመልክተዋል፡፡

#ቪኦኤ
ፎቶ፦ የማነ ገ/መስቀል

@tikvahethiopia
" በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው " - አቶ ንጉሱ ጥላሁን

በአፍሪካ ሀገራት የስራ እድል ፈጠራዎች ላይ ባሉ ፈተናዎች እና ምቹ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር የስራ ፈጠራ ማድረክ በአ/አ አፍሪካ ህብረት ግቢ ውስጥ ተጀምሯል።

ትላንት በነበረው መድረክ ላይ የተሳተፉት የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በየአመቱ 2 ሚሊዮን አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች እየተፈጠሩ ነው ብለዋል።

ለስራ ፈላጊ ዜጎች በተለያየ የስራ ዘርፍ ስራ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ በውጭ ሀገርም ትልቅ እድል እንዳለ አሳውቀዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በየአመቱ በእቅድ ተይዞ ነው የሚሰራው።

ለምሳሌ በ2015 በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭው አለም ለመፍጠር ነው የታቀደው፤ ከዙህ ውስጥ 85 በመቶ በቤት ውስጥ ስራ 15 በመቶ skilled የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ ነው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የዓመቱን ማጠቃለያ እንገመግማለን የአመቱን እቅድ እንደምናሳካ መረጃዎች ያሳያሉ።

ከዛ ባሻገር በውጭ ሀገር ገበያ በርካታ ፍላጎት አለ፤ 2 ሚሊዮን ያህል የስራ ገበያ ፍላጎት አለ።

በአንዳንድ ሀገራት ተወዳዳሪ ሆነን እስከተገኘን ድረስ ዋናው ብቃት ያለው ሰው ፣ ታታሪ ፣ ታማኝ ፣ ምርታማ የሆነ ፣ ስነምግባር ያለው ፤ ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሆነ ሰው ማዘጋጀት ከቻልን ሰፊ እድል አለ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግሥት አዲስ ሰራተኞች የስራ ቅጥር እንደሌለ በገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ የተደረገውን ውሳኔ በተመለከተ አቶ ንጉሱ ተጠይቀው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ ስራ መፍጠር ያለበት መንግሥት ብቻ ነው የሚለው የቆየ አስተሳሰብ መቀየር አለበት ብለዋል።

" እኔ ምረዳው እውነታውም ጭምር መንግሥት ዋነኛ ስራ ቀጣሪ አይደለም። በየትኛውም ዓለም ፤ በየትኛውም ሀገር ዋነኛው ቀጣሪ የግሉ ዘርፍ ነው። መንግሥት የግሉ ዘርፍ ሁኔታዎችን እንዲመቻቹለት ማድረግ ነው የሚጠበቅበት ፤ ይሄንን የስራ እድል ለመፍጠር የማያስችሉ ፖሊሲዎች ፣ መመሪያዎችን አሰራሮችን ማውጣት ፣ የገንዘብ አቅርቦት እንዲሟላ ማድረግ ፣ የቴክኖሎጂ ትስስር ሽግግር እንዲኖር ማድረግ ፣ መሰረተ ልማት ማሟላት ፣ የገበያ ትስስር እንዲኖር ማድረግ የመንግስት ድርሻ ነው " ሲሉ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናግረዋል።

" እነዚህ ሁሉ የተሟሉ ሲሆኑ ፤ አገልግሎት ሲሟላ የግሉ ዘርፍ ይስፋፋል ያድጋል ፣ ኢንቨስትመንት ይሰፋል በዚህ ምክንያት የስራ እድል ይፈጠራል መንግሥት ሁሉንም ጀምሮ የሚጨርስ አይደለም። ዘንድሮ 3.1 ሚሊዮን የስራ እድሎች ተፈጥረዋል እስካሁን ከዚህ ውስጥ በመንግሥት መ/ቤቶች እና ተቋማት የተቀጠረው በጣም ዝቅተኛ ነው ከ3.1 ሚሊዮኑ መቶ ሺህ የማይሞላ ወደ 92 ሺህ ያህል ነው ከወረዳ እስከ ፌዴራል ድረስ ያለው ፤ በመንግሥት የስራ ዘርፍ ያሉት እድሎች ውስን ናቸው ጥቂቶች የሚገቡባቸው ናቸው ፤ ይልቁንም መንግሥት ማድረግ ያለበት ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሮ በርካታ ዜጎች የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው የሚያስችሉ ኢንተርፕራይዞች እንዲሰፉና እንዲያድጉ ማድረግ ነው " ብለዋል።

አቶ ንጉሱ ፤ " በባለፈው ዓመት ከለየነው 6 ሚሊዮን የስራ ፈላጊ ፤ ወደ 650 ሺህ አካባቢው ምሩቅ ነው ፤ ይሄንን ምሩቅ ከቴክኒክና ሙያ እና ከዩኒቨርሲቲ የተመረቀ መንግሥት ሁሉም ቦታ ላይ አስገባዋለሁ ቢል ቦታው የለውም ፤ ይሄን ሁሉ ምሩቅ እና ስራ ፈላጊ መንግሥት ማድረግ ያለበት አሰልጥኖ አብቅቶ የገንዘብ አቅርቦት አመቻችቶ የስራ ቦታ አመቻችቶ የስራ ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቅበታል። " ሲሉ ተደምጠዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#Tigray

በትግራይ ክልል ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎች በረኀብ እንደሞቱ ተገለጸ።

በትግራይ ክልል የሰብአዊ ርዳታ ምግብ በይፋ ከተቋረጠ 90 ቀናትን ያስቆጠረ ሲሆን በዚህም ምክንያት ከአንድ ሺ በላይ ሰዎች በረሀብ እንደሞቱ፣ የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በተለይ ከአምስት ዓመት በታች የኾኑ ሕፃናት እና የዕድሜ ባለጸጋ አረጋውያን፣ ይበልጥ እየተጎዱ መሆኑ ነው የተገለጸው።

በኮሚሽኑ የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ግብረመልስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ገ/እግዚአብሔር አረጋዊ መቼ ሞቱ፣ የት አከባቢ፣ እድሜያቸው የሚሉት የሟቾች መረጃ ከተለያዩ አከባቢዎች፤ ከተፈናቃይ አስተባባሪዎች፤ ከዞንና ከክልል አስተባባሪዎች እየደረሳቸው እንደሆነ አንስተዋል።

በዚህም እስካሁን በተሰበሰበው መረጃ የሟቾች ቁጥር ከ1000 ከፍ ማለቱን አስታውቀው አሁንም ቁጥሩ እየጨመረ መምጣቱን ነው የጠቆሙት።

ዳይሬክተሩ ፥ ተመዝብሯል ከተባለው የእርዳታ እህል ጎን ለጎን ምርመራው እየተካሄደ የህይወት አድን ሥራው እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

የእርዳታ ሰጪ ተቋማት በሚፈልጉት መልኩ መረጃዎችንና ተረጂዎችን የመለየት ሥራ እየተጠናቀቀ መሆኑን የገለጹት አቶ ገ/እግዚአብሔር እርዳታው እስካሁን ባለመጀመሩ በተለይ ተፈናቃዮች በአስከፊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል እያካሄደው ባለው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሥራ ማኅበረሰቡ እና ተፈናቃዮች ዋነኞቹ የሰብአዊ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ሥራቸውን በማቋረጣቸው ከአራት እስከ ሰባት ወራት ለቆየ ጊዜ ሰብአዊ እርዳታ ያለማግኘታቸውን እና በዚህም ቀደም ብሎ የነበረው የሰብአዊ ቀውስ በከፍተኛ ሁኔታ የተባባሰ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

የኢሰመኮ የክትትልና ምርመራ ዳይሬክቶሬት ሰላማዊት ግርማይ እንደገለጹት፥ " ከህክምና ተቋማት እንዲሁም በአካል በመገኘት ባለሞያዎች የተለያዩ መረጃዎች ሰብስበዋል። ነገር ግን ክትትሉና ምርመራ ሂደት ላይ ስለሆነ ቁጥሩን መግለጽ አንችልም፤ ሆኖም ባደረግናቸው ክትትሎች ችግሩ አሳሳቢ መሆኑን ታዝበናል " ብለዋል።

ኮሚሽኑ፥ መንግሥትና የእርዳታ ሰጪ ተቋማት ወቅቱን የጠበቀና ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ወይም ለመብቶች ጥሰት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረገ የሰብዓዊ ድጋፍ በፍጥነት መልሰው እንዲጀምሩ አሳስቧል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#ጋብቻ

እየተጠናቀቀ ባለው በ2015 ዓ/ም የጋብቻ ፍቺ የፈፀሙ እና የተመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ባለትዳሮች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር #በእጥፍ እንደበለጠ ታውቋል።

የአ/አ ሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በሰጡት ቃል፤ " በ2015 ዓ/ም በጀት አመት 4,696 ሰዎች ፍቺ አስመዝግበዋል ፤ አምና መጥተው ያስመዘገቡት 2,937 ሰዎች ነበሩ " ብለዋል።

ምዝገባው ነው የጨመረው እንጂ ፍቺው ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል ሲሉ ዳይሬክተሩ አክለዋል።

የፍቺ ሁኔታ ከእጥፍ በላይ ጭማሪ ቢያሳይም ሂደቱ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የሚከናወን በመሆኑ ትክክለኛውን ቁጥር ለማውቅ አዳጋች እንደሆነ አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል።

" ፍ/ቤት ላይ የሚፈፀመውን ፍቺ እዛው ወቅታዊ ምዝገባውን የማከናወን ስራ በዚህ አመት አቅደን አልተሳካም ሚቀጥለው አመት እየተነጋገርን ነው ፍርድ ቤት ሆነን ምዝገባ የሚከናወንበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለን እንጠብቃለን። " ብለዋል።

" በዚህ መንገድ ትክክለኛውን ዳታ ፍቺ እየጨመረ ነው ወይስ እየቀነሰ ነው የሚለውን ውሳኔ ለመስጠት እንችላለን " ያሉት አቶ ዮሴፍ " አሁን ላይ ግን የኛ ምዝገባ ሰው ፍልጎ ፍቺውን በተለያየ አግባብ ለንብረት ክፍፍል ፣ ከመታወቂያ ዲጂታላይዝ መደረግ ጋር ተያይዞ የጋብቻ ሁኔታ ፍቺ የማስባል እና ሌሎች ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ... በዛ ምክንያት እኛ ጋር ምዝገባው ከአምና ከፍ ብሏል የሚል ድምዳሜ ነው የያዝነው " ሲሉ ተናግረዋል።

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#እስራኤል

ኔታኒያሁ አፍሪካዊያን ስደተኞችን ከእስራኤል ለማስወጣት ለሚያዝ እቅድ ፍቃድ መስጠታቸው ተነገረ።

በትላንትናው ዕለት በቴል አቪቭ ጎዳናዎች ላይ በኤርትራዊያን ስደተኞች መካከል የተፈጠረውን አስከፊ ግጭት ተፈጥሮ ነበር።

ይህን ተከትሎ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ደም በተቃባው ግጭት ላይ የተሳተፉት ስደተኞች በሙሉ በአስቸኳይ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እንደሚፈልጉ አስታውቀዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ አክለውም ሁሉም #አፍሪካዊያን ስደተኞች ከእስራኤል እንዲወጡ ለሚያዝ እቅድ ፍቃድ መስጠታቸውንም ገልጸዋል።

ትላንት ቅዳሜ የፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን አስተዳደርን በሚቃወሙ እና በሚደግፉ ኤርትራዊያን መካከል ግጭት ተነስቷል።

ተቃውሞውና ግጭቱ በእስራኤል ኤርትራ ኤምባሲ ፊት ለፊት ነው የተካሄደው። የእስራኤል የአደጋ አገልግሎት ተቋም 114 ሰዎች በግጭቱ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቋል።

የእስራኤል ፖሊሶች የግጭቱን ተሳታፊዎች ለመበተን የፕላስቲክ ቦምቦችን የተጠቀሙ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ በፖሊሶቹ ላይ ድንጋይ ወርውረዋል።

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፖሊስ ተቃዋሚዎቹ ላይ እሳት መርጨቱን የዘገበ ሲሆን በአጸፋው 27 ፖሊሶች ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል አስታውቋል።

በተያያዘ ሮይተርስ እጃቸው እና ጭንቅላታቸው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች በህጻናት መጫወቻ ሜዳዎች ሲደበቁ መመልከቱን ዘግቧል።

በእስራኤል 20,000 ኤርትራዊያን ጥገኝነት ጠያቂዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኞቹም በህገወጥ መንገድ በግብጽ አድርገው የመጡ ናቸው።

#ቪኦኤ #ኤኤፍፒ #ሮይተርስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#G20 አፍሪካ ህብረት G20ን እንዲቀላቀል ጥሪ ቀረበለት። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የ " አፍሪካ ህብረት " የቡድን 20 አባል እንዲሆን በዛሬው ዕለት ጥሪ ማቅረባቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በሚቀጥለው ወር በሕንድ ፤ ኒው ዴሊ የቡድኑ መሪዎች ጉባኤ ይካሄዳል። ሞዲ ለአፍሪካ ህብረት ጥሪውን ያቀረቡት " ቢ20 የተሰኘው በቢዝነስ ፎረም እና የመስከረም ወሩ ጉባዔ መዳረሻ መድረክ ላይ ማደረጉት…
" አፍሪካ ሕብረት እንዲገኝ ጥሪ አልደረሰንም " - ኤባ ካሎንዶ

አዲሱ የቡድን 20 የበለጸጉ ሀገራት ዓባል ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው የአፍሪካ ኅብረት ቡድኑ በሳምንቱ መጨረሻ በሚያካሂደው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ እንዳልተጋበዘ ገልጿል።

ነገ ዓርብ እና ቅዳሜ በኒው ደሊ የሚካሄደውን ጉባኤ ያዘጋጀችው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ አፍሪካዊው ድርጅት ቡድኑን እንዲቀላቀል ጥሪ አድርገው ነበር።

የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ቃል አቀባይ የሆኑት ኤባ ካሎንዶ፣ ኅብረቱ በጉባኤው ላይ እንዲገኝ ጥሪ እንዳልደረሰው ትናንት ለኤኤፍፒ ተናግረዋል።

19 ሀገራትን እና የአውሮፓ ኅብረትን በዓባልነት ያቀፈው ስብስብ፣ 85 በመቶ የዓለምን የሀገር ውስጥ ምርት እና ከዓለም ሕዝብ ሁለት ሶስተኛውን ይይዛል።

ደቡብ አፍሪካ ከአህጉሪቱ ብቸኛዋ የቡድኑ ዓባል ነች፡፡

“የአፍሪካ ኅብረትን የጋበዝነው ወደፊት ቋሚ ዓባል እንዲሆን ታሳቢ በማድረግ ነው” ሲሉ ሞዲ ከ 10 ቀናት በፊት ተናግረው ነበር።

“የአፍሪካ ኅብረትን በቋሚ ዓባልነት ሞቅ አድርገን ለመቀበል እንጠብቃለን” ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ባለፈው ታህሳስ ተናግረው ነበር፡፡

የቡድን 20 አባላት እነማን ናቸው ?

🇦🇷 አርጀንቲና
🇧🇷 ብራዚል
🇨🇦 ካናዳ
🇨🇳 ቻይና
🇫🇷 ፈረንሳይ
🇩🇪 ጀርመን
🇮🇳 ህንድ
🇮🇩 ኢንዶኔዥያ
🇮🇹 ጣልያን
🇯🇵 ጃፓን
🇰🇷 ደቡብ ኮሪያ
🇲🇽 ሜክሲኮ
🇷🇺 ሩስያ
🇸🇦 ሱዑዲ አረቢያ
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇹🇷 ቱርክ
🇬🇧 ዩናይትድ ኪንግደም
🇺🇸 አሜሪካ
🇪🇺 አውሮፓ ሕብረት ናቸው።

#ኤኤፍፒ #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
መምህራኑ ላለፉት 2 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም አሉ።

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎጃም ዞን፣ ጎንጂ ቆለላ ወረዳ ፣ ላለፉት 2 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለጹ መምህራን የከፋ ችግር ላይ እንደሚገኙ ገለጹ።

መምህራኑ በቁጥር ከ1 ሺሕ በላይ ይሆናሉ።

በወረዳው በሚገኙ 52 የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩት እኚህ መምህራን ፤ ኑሯቸውን የሚገፉት በወርሃዊ ደመወዛቸው ብቻ በመሆኑ ፣ ዩኒቨርሲቲ ለሚማሩ ልጆቻቸው የሚላክ ገንዘብን ጨምሮ ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ እንደተሳናቸው ገልጸዋል፡፡

የቆንጂ ቆለላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት ጌታቸው ደገፋው ችግሩ መሆኑን አምነዋል።

በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር የሒሳብ ሠራተኞች ወደ ቢሮ ገብተው ለመሥራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የተፈጠረ እንደሆነ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት፣ ከመምህራን ማኅበር ጋራ በመነጋገር አዲስ ሠራተኞች ተመድበው ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
" የተሻለ ህይወት ፍለጋ አህጉሩን ጥለው የተሰደዱ አፍሪካውያን የጤና ባለሞያዎች ቁጥር የሚስደነግጥ ነው " - ካሉምቢ ሻንጉላ

አፍሪካ የጤና ባለሙያዎች እጥረት እንዳለባት የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

ድርጅቱ በናሚቢያ ዋና ከተማ ፤ #ዊንድሆክ በዚህ ሳምንት እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ የጤና ባለሞያዎች ፎረም ላይ ነው ይህን ያሳወቀው።

ፎረሙ ላይ የናሚቢያ የጤናና የማህበራዊ አገልግሎት ሚኒስትር ካሉምቢ ሻንጉላ ፥ " #አፍሪካ ያጋጠማት የጤና ባለሙያዎች እጥረት አህጉሪቱ እ.አ.አ በ2030 ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ለማግኘት የያዘችውን እቅድ እንዳታሳካ እንቅፋት ይሆናል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" የተሻለ ህይወት ፍለጋ አህጉሩን ጥለው የተሰደዱ አፍሪካውያን ቁጥር #የሚስደነግጥ_ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ይህን ጉዳይ የአፍሪካ መንግስታትም ሆኑ ታሪካዊ እና ወቅታዊ ሁኔታዎች ተለውጠው ማየት የሚሹ በሙሉ ቅድሚያ ሰጥተው ሊፈቱት የሚገባ ጉዳይ እንደሆነ አስረድተዋል።

የአፍሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ጀነራል ጂን ካሳያ እንዳስታወቁት፣ እ.አ.አ በ2030 ለመድረስ የታቀደውን ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ለማሳካት አፍሪካ ተጨማሪ 1.8 ሚሊየን የጤና ሰራተኞች ያስፈልጓታል።

በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ 1.55 የጤና ባለሙያዎች ለአንድ ሺህ ሰዎች አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ፣ ይህም ለ1 ሺህ ሰዎች 4.55 የጤና ባለሙያዎች እንደሚያስፈልግ የዓለም ጤና ድርጅት ካስቀመጠው ገደብ በታች ነው።

እ.አ.አ በ2023 ብቻ አፍሪካ " 166 ወረርሽኞች "ን መመዝገቧን ያመለከቱት ካሳያ ፤ የአፍሪካ ህብረት አባል አገራት እ.አ.አ በ2030 ሁለት ሚሊየን የቋማዊ የማህበረሰብ የጤና ሠራተኞችን እንዲመለምሉ እንዲያሰለጥኑና ወደ ስራ እንዲያሰማሩ የተወሰነውን ውሳኔ ለማሳካት በጣም ወደኃላ መቅረታቸውንም አመልክተዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ሞተዋል !! " - ዓለም አቀፉ ፍ/ቤት

በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ይፈለጉ የነበሩ የመጨረሻው ሁለት የሩዋንዳ የዘር ፍጅት ተከሳሾች መሞታቸውን ማረጋገጡን በጉዳዩ ላይ የተቋቋመው ችሎት አስታውቋል።

ርያንዱካዮ በሚል ስም ብቻ የሚጠራው እና ቻርለስ ሲኩብዋቦ በሩዋንዳ የዘር ፍጅት ጉዳይ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ ችሎት ሲፈለጉ የነበሩ የመጨረሻዎቹ ተከሳሾች ናቸው።

በብሔራዊ ደረጃ ግን አሁንም ድረስ ከ1 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በመፈለግ ላይ ናቸው።

2ቱ ግለሰቦች ከ30 ዓመት በፊት 800 ሺ ቱትሲዎችን እና ለዘብተኛ ሁትዎችን በጨረሰው የዘር ፍጅት ላይ ተሳትፎ አላቸው በሚል ለሩዋንዳ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ የወንጀል ችሎት በእ.አ.አ 1995 ክስ ቀርቦባቸው ነበር።

ሲኩብዋቦ በእ.አ.አ 1998 በቻድ መሞቱን እና በዛው መቀበሩን እንዲሁም ርያንዱካዮ ደግሞ ወደ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ከሸሸ በኋላ ከዛም ወደ ዛየር ተሻግሮ ኪንሻሳ ላይ በ1998 ሕይወቱ ማለፉን ፍ/ቤቱ አስታውቋል።

በሩዋንዳው የዘር ፍጅት ጉዳይ በዓለም አቀፉ ፍ/ቤት ሲፈለጉ የነበሩ ተከሳሾች ሁሉ መለየታቸውንም ችሎቱ አስታውቋል። #ቪኦኤ

#RwandaGenocide

@tikvahethiopia
#Somalia

• " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም "- ሙርሳል ካሊፍ


ጎረቤት ሶማሊያ በሀገሪቱ የጸጥታ ክፍተት ሊፈጠር ይችላል ስትል አስጠንቅቃ ፤ የአፍሪካ ሰላም አሰከባሪ ኃይሎች ከሶማሊያ ለቀው የሚወጡበትን ፍጥነት እንዲቀንሱ መጠየቋ ተሰምቷል።

ሮይተርስ ተመለከትኳቸው ያላቸው ሰነዶች እንደሚያሳዩት ከሶማሊያ ጋር ድንበር የሚዋሰኑ አጎራባች ሀገሮች፣ ዳግም እያንሰራራ የሚገኘው የአል-ሻባብ ቡድን ስልጣን ሊቆጣጠር ይችላል የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።

በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ሰላም አስከባሪ ኃይል እ.አ.አ በታህሳስ መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ሶማሊያን ለቆ ለመውጣት ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በቁጥር አነስተኛ የሆነ ኃይል በቦታው እንደሚተካ ይጠበቃል።

ሆኖም የሶማሊያ መንግስት ለአፍሪካ ህብረት ሰላም እና ጸጥታ ም/ቤት ጊዜያዊ ሊቀመንበር ባለፈው ወር በላከው ደብዳቤ፣ አሁን ካሉት 4 ሺህ ወታደሮች ግማሽ የሚሆኑትን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ለማስወጣት የተያዘውን እቅድ ወደ መስከረም እንዲያሻግር ጠይቋል።

መንግስት ቀድም ሲል ለህብረቱ አስገብቶት በነበረው እና ሮይተርስ በተመልከተው ሰነድም፣ ሰላም አስከባሪው ኃይል ለቆ የሚወጣበት ጊዜ በሶማሊያ ኃይሎች " ዝግጁነት እና አቅም ላይ እንዲመሠረት " ጠይቆ ነበር።

በተመድ የፀጥታው ም/ቤት ተልዕኮ የተሰጠው ቡድን ባካሄደው የጋር ግምገማም " የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል በችኮላ መውጣታቸው የፀጥታ ክፍተት እንደሚፈጥር " አስጠንቅቋል።

የፓርላማው መከላከያ ኮሚቴ ገለልተኛ አባል የሆኑት ሙርሳል ካሊፍ ፤ " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም " ብለዋል።

ሶማሊያ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ጸጥታ ኃይል ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ደጋፊ የሆኑት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የሰላም አስከባሪውን ኃይል ለመቀነስ የወሰኑት ዘላቂነት ያለው የረጅም ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የማድረጉ ሁኔታ ስጋት ውስጥ ስለከተታቸው መሆኑን አራት የዲፕሎማቲክ ምንጮች እና አንድ የዩጋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ ተናግረዋል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንትና የጠ/ሚ ፅ/ ቤት በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም።

#ሮይተርስ #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Raya እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ሪፖርት መሰረት ከራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በልጧል። 42 ሺህ ዜጎች ቆቦ ፤ 8,300 ሰዎች ሰቆጣ ይገኛሉ። የተፈናቀሉት ከራያ አላማጣ፣ ዛታ፣ ኦፍላ ነው። አብዛኞቹ ህጻናት ፣ ሴቶች ፣ ወጣቶች እና በእድሜ የገፉ አዛውንቶች ናቸው። #UNOCHA @tikvahethiopia
🔈 #የተፈናቃዮችድምጽ

ሚያዚያ ወር በተቀሰቀሰው ግጭት ከኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ዜጎች ዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞን ይገኛሉ።

እነዚህ ወገኖች ላለፉት ሶስት ወራት ያለ በቂ ሰብዓዊ ድጋፍ በመቆየታቸው የከፋ ችግር ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

አጠቃላይ ተፈናቃዮች ከ22 ሺህ ይልቃሉ።

ተፈናቃዮች ምን አሉ ?

- አሳሳቢ የምግብ እና የመጠለያ ችግር አለ።
- እያንዳንዱ በሰው ቤት ተጠግቶ ነው ያለው።
- ቤተዘመድ እያገዛቸው እንጂ ለ3 ወር የከፋ ችግር ላይ ወድቀው ነው የሚገኙት።
- በ3 ወር ምንም የተደረገ ድጋፍ የለም።
- ዋግኽምራ ዞን የተቻለውን ቢያደርግም ከአቅሙ በላይ ነው። ብዙ ሰው ነው ያለው።
- አብዛኛው በረዳ ወቅዷል።
- ዘመድ ያለውም ዘመዱ ጋር ተቸግሮ ነው የሚኖረው።
- እየለመ የሚበላ አለ፣ ጉልበት ያለውም ተቀጥሮ የሚሰራ አለ።
- አንዳንድ እናቶች መጠለያ ተሰጥቷቸው ነበር ግን ልጆቻቸው ሲታመሙ ቤት ተከራይተው ወጥትተዋል። በዚህ ኑሮ ውድነት መኖር አልቻሉም።
- ተፈናቃዮቹ በቄያቸው ቤት እና ስራ ነበራቸው።

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ምን አለ ?

° ከ11 ሺህ ተፈናቃዮች ነው ያሉት።
° አሁን ባለንበት ሁኔታ መጠለያ ማዘጋጀት አንችልም። ድንኳንም የለንም።
° የምንመግበውን ተቸግረን በመጡ ጊዜ ለአንድ ሰው 25 ኪ/ግ ነው  የሰጠነው። ከመጠባበቂያ !
° የሰላሙ ሁኔታ አለ፣ መንገድ ዝግትግት ያለ ነው ሌላ አካል ድጋፍ ላምጣ ቢል እንኳን።
° አካባቢው ዝናብ አጠር ነው። በድርቅ ይጠቃል። የዓምናው ድርቅም ጉዳቱ እንዳለ ነው። ብዙ ሰው ተጎድቷል። አሁን ተፈናቃይ ተጨምሮ ይቅርና በፊትም ብዙ ችግር አለ።
° በህጻናት አድን ድርጅት ካሽ 14 ሺህ በሁለት ዙር ለመስጠት ልየታ እየተደረገ ነው።
° ያሉት ተፈናቃዮች ከኦሮሚያ፣ ከመተማ፣ በሰሜን ጦርነትም ተፈናቅለው ያልሄዱ አሉ።

በአሁኑ ወቅት እርሳቸውም ተፈናቃይ መሆናቸውን የገለጹትና ኮረም ከተማን ለሁለት ዓመት በከንቲባነት የመሩት አቶ ብርሃኑ ኀይሉ፣  የተፈናቀለው ሕዝብ ብዛት ከ22 ሺሕ እንደሚበልጥ ገልጸው ፥ የምግብ አቅርቦቱ እጥረት አሳሳቢ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

" እርዳታ ጠይቀናል። ለ3 ወራት ተከታታይ እርዳታ የለም።  ክልሉ የሰጠን ነገር የለም፤ ጭራሽ አላነገረንም " ብለዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን " መረጃ አለን ፤ ለተፈናቃዮቹ የምግብ አቅርቦት ጥያቄ በቅርቡ ምላሽ ይሰጣል ፤ እርዳታም ይጓጓዛልም " ሲል ገልጸዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ONLF #SOMALIREGION

ከሰሞኑን ተቃዋሚው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ' የሶማሌ ክልል የዜጎች መብት የሚጣስበት እየሆነ ነው " ሲል ከሷል።

ፓርቲው ክልሉ ሶማሌዎች ማንነታቸውን እንዲክዱ የሚገደዱበት እየሆነ ነው ብሏል።

የክልሉን ስያሜና ሰንደቀላማ የመቀየር እቅድ እንዳለ ከአሉባልታ ከፍ ያለ መረጃ አለን ሲሉም፣ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አብዲራህማን መሀዲ ተናግረዋል።

ባለፉት 6 አመታት በክልሉ የጎሳ ግጭቶች ጨምረዋል ሲሉም ወቀሳ አቅርበዋል።

የክልሉ ርዕሰመስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ በበኩላቸው፣ የክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች " እኛ ሶማሌዎች እንጂ ሶማሊያውያን አይደለንም " ማለታቸው ማንነትን እንደመካድ ሊወሰድባቸው አይገባም ብለዋል።

በቀድሞው አስተዳደር ህግን ባልተከተለ መንገድ ተቀይሮ የነበረውን ስያሜና ሰንደቅ አላማ በመተው በህገመንግስቱ የተቀመጠውን ስያሜ መጠቀም የጀመረው የእርሳቸው አስተዳደር መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ሙስጠፋ የኦብነግ ሊቀመንበር የሚመሩት ቡድን ይህንን መግለጫ ያወጣው በክልሉ ችግር ስላለ ሳይሆን " ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ እየተስተዋለ ያለውን ጂኦፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ጥቅም በመፈለግ ነው " ሲሉ ተችተዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia