TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ድርቅ #ትግራይ

" ከምበላባቸው ቀናት #ጦሜን የማድርባቸው ቀናት ይበዛሉ " - የሰንዓለ ነዋሪ

" በድርቅ ምክንያት 6 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ፤ ... 89 ከመቶ ነዋሪ በከባድ የደርቅ አደጋ ላይ ይገኛል " -  ዒስራ ዓዲ ወጀራት ወረዳ

በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዒስራ ዓዲ ወጀራት ወረዳ ባጋጠመው ድርቅ ምክንያት 6 ሰዎች መሞታቸውን የወረዳው የኢኮኖሚ ዘርፍ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

ፅ/ቤቱ ፤ በወረዳው ቀበሌ ገበሬ ማህበራት ያጋጠመው ድርቅ በጊዜው ካልተገታ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ሲል አስጠንቅቋል።

ወ/ሮ ኣልጋነሽ ከበደ በወረዳው የሰንዓለ ነዋሪ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው።

ወ/ሮ ኣልጋነሽ ፤ ከማሳቸው የሚያገኙት ገቢ ከአመት አመት ስለማይመግባቸው ድሮውኑ በሴፍትኔት እገዛ ሲተዳደሩ ነበር።

በጦርነቱ ምክንያት የሴፍትኔት አገልግሎት በመቆሙ የዘንድሮ ድርቅ መቋቋም አቅቷቸዋል። በዛ ላይ አህታቸው በረሃብ ምክንያት በመሞትዋ ሁለት ልጆችዋን የመንከባከብ ሃላፊነት በእሳቸው ላይ ወድቀዋል።

ወ/ሮ ኣልጋነሽ ችግሩ የሚይዙት የሚጨብጡት አሳጥቷቸው ከሚበሉባቸው ጦማቸው የሚያድሩባቸው ቀናት እንደሚበዙ ተናግረዋል።

ከወረዳዋ ሰንዓለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ብቻ ድርቅ ባስከተለው ችግር ቄያቸው ጥለው ከተሰደዱ 40 የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች አንድዋ ወ/ሮ ፎቴን ኣባዲ ናቸው።

በድርቁ ምክንያት ከማሳቸው ያገኙት ገቢ ባለመኖሩ ፣ በዛ ላይ ከምግባረ ሰናይ ተቋማትና መንግስት የሚሰጥ እርዳታ በመቆሙ ቤታቸው ቆልፈው እግራቸው ወደ መራቸው ተሰደዋል። 

ድርቅ ባስከተለው ረብ አስከአሁን 6 ሰዎች መሞታቸው የሚገልፁት የወረዳው የኢኮኖሚ ዘርፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሃሪፈያ ግደይ ፤ የወረዳው 89 ከመቶ ነዋሪ በከባድ የደርቅ አደጋ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።  

የምግባረ ሰናይ ድርጀቶች የፌደራልና የክልሉ መንግስታት ችግሩ በመረዳት ቶሎ እንዲደርሱ ጥሪ ያቀረቡት ሃላፊዋ ፣ በተለይ እናቶችና ህፃናት ታሳቢ ያደረገ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲደረግ ማሳሰባቸውን የትግራይ ቴሌቪዥንን ዋቢ በማድረግ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በትግራይ ያጋጠመው ደርቅ የሚመለከት ተከታታይ መረጃዎችን በማቅረብ ላይ ሲሆን ፤ በክልሉ ምስራቃዊ ዞን ሶስት ወረዳዎች ባጋጠመ የድርቅ አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ የመንግስት አካላት መናገራቸውን መዘገቡ ይታወሳል።
                      
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሺርካ ✦ " 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት (አያት ፣ ልጅ፣ የልጅ ልጅ ፣ የ39 ቀን ጨቅላ) ጨምሮ 17 ስዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል " - የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ✦ " ከሟቾቹ ውስጥ ከ70 ዓመት አዛውንት እስከ 26 ቀን ህጻን ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል " - ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ (ለቪኦኤ) ✦ " ጥቃቱን ያደረሰው አሸባሪው ሸኔ ነው " - የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን (ለቪኦኤ) ✦ " እኛ…
#Update

ቤተክርስቲያኗ ዛሬ ባወጣችው መግለጫ በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እንደምታወግዝና የጸጥታ ተቋማትም ጥቃት እንዲከላለሉ ጥሪ አቀረበች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ፅ/ቤት በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ፦
- በሶሌ ሚካኤል፣
- በዲገሎ ማርያም፣
- በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጿል።

በዚሁ ጥቃት በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው #ተለቅመው መገደላቸውን ፤ ከእነዚህ ውስጥ 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው መታወቁን አመልክቷል።

በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት እንደሚገኙበት ገልጿል።

#በዛሬው_ዕለት ደግሞ በዲገሉ ማርያም ቤተክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን መገደላቸውንና የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት መቃጠሉን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ 3 ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸውን ፅ/ቤቱ አስታውሷል።

የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ እንደሚገኙ የገለፀው ፅ/ቤቱ  " በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም #ርምጃ_እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ በላከው ሪፖርት ማረጋገጡን አመልክቷል።

ይህ ዐይነት ሃይማኖት ተኮር ጥቃት በምእመናን ላይ መድረሱ አግባብነት የሌለውና እምነትን በነጻነት የማራመድ መንግስታዊ መብትን የሚጥስ ነው ያለው ፅ/ቤቱ ፤ መሰል ሕገ ወጥ ጥቃትን ለመከላከልና ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት መብቶቻቸውን ተቋማዊ በሆነ መንገድ ማስከበር እንዲችሉ  ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ድርጊቱን በማውገዝ ችግሩ ከመሠረቱ እንዲፈታ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መፈለግ ሲገባው በዝምታ በማለፉ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ቅሬታ እንደተሰማት ገልጿል።

" ኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ ጥረት እየተደረገ ነው " ያለው ጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመሆን ፅ/ቤቱም ጉዳዩን የሚከታተለው መሆኑን አሳውቋል።

በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የምስራች ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች! አፖሎ የሥራ ዕድል ይዞ መጥቷል፤ የአፖሎ አካውንት ሌሎች እንዲከፍቱ ባደረጉ ቁጥር ኮምሽን ተዘጋጅቷል! ከኮምሽን በተጨማሪም የተለያዩ ጥቅሞች ያገኙበታል። አሁኑኑ ፍጠነው ይመዝገቡ!

የተመዘገባችሁ ተማሪዎች፣ መቼ እንደምትጀምሩ ሪፈራል ኮዳችሁን ጨምሮ በአመለከታችሁበት ስልክ ቁጥር/ በSMS አጭር የስልክ መልዕክት እናሳውቃችኋለን፡፡

ማስፈንጠሪያውን በመጠቀም ይመዝግቡ፦https://apolsup.bankofabyssinia.com/studentAgent/

ከአፖሎ ጋር ተፍ ተፍ በሉ!
ከሥራ በፊት ሥራ ጀምሩ!
ጠቀም ያለ የሪፈራል ኮሚሽንም ያግኙ!
TIKVAH-ETHIOPIA
ኔፓል ሀገሪቱ ላይ " ቲክቶክ " እንዲታገድ ወሰነች። ኔፓል ፤ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚረብሹና የቤተሰብን መዋቅር እንዲሁም ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያውኩ ይዘቶችን ለማጋራት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ያለችውን የቻይናውን " #ቲክቶክ " መተግበሪያ እንዲታገድ ውሳኔ አሳለፈች። ሀገሪቱ ፤ " ቲክቶክ " በማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ያለች ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የሚለቀቁት…
#ቲክቶክ

ለምንድነው ሀገራት " ቲክቶክ " ን ለማገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ?

ከቅርብ ወራት ወዲህ አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ካናዳ ያሉ የህግ አውጪዎች ከፀጥታ እና ደህንነት ስጋት ጋር በማያያዝ ግዙፉን የአጫጭር ቪድዮዎች ማጋሪያ " ቲክቶክ " ን ለማገድ / ለመገደብ የሚያደርጉትን ጥረት ማጠናከራቸውን ኒውዮርክ ታይምስ አስነብቧል።

ዋይትሃውስ እኤአ በፌብሩዋሪ 27 የፌዴራል  ኤጀንሲዎች አፕሊኬሽኑን ከመንግሥት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ላይ እንዲያጠፉ 30 ቀናት ሰጥቷቸው ነበር ፤ እንዲሁም ኒውዮርክን ጨምሮ የተለያዩ ከተሞች የመንግሥት ሰራተኞች " ቲክቶክ " ን እንዳያወርዱ ከልክለዋል።

በተጨማሪም ባይደን በሀገር ደረጃ ከሁሉም መሳሪያዎች ላይ መተግበሪያው እንዲታገድ እንዲያደርጉ የድጋፍ እንቅስቃሴዎች ነበሩ፤ አሁንም አሉ።

ለምንድነው መንግሥታት ቲክቶክን ለማገድ የሚንቀሳቀሱት ?

በተለይ ምእራባውያኑ ቀጥታ ጉዳዩን #ከቻይና ጋር ያገኛኙታል።

የምዕራቡ ዓለም የሕግ አውጪዎች እና ተቆጣጣሪዎች " ቲክቶክ " / ባለንብረቱ የባይትዳንስ የተጠቃሚ መረጃዎችን በቻይና መንግሥት እጅ እንዲገቡ ያደርጋል የሚል አቋም አላቸው።

ለዚህም እንደማያሳያ የሚያደርጉት የቻይና መንግሥት ለደህንነት ጉዳይ መረጃዎችን ለማሰባሰብ በሚስጥር ከቻይና ኩባንያዎች እና ዜጎች መረጃዎችን መውሰድ የሚያስችለው ህግ እንዳለው በመግለፅ ነው።

ቲክቶክ መሰል ክሶችን ለረጅም ጊዜ ውድቅ አድርጓል።

- ህንድ በ2020 ላይ ነው ያገደችው።
- የብሪታኒያ ፣ የፈረንሳይ፣ የኒውዝላንድ ፣ የአውስትራሊያ፣ ካናዳ #ፓርላማዎች ከአባላት ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች እንዲታገድ አድርገዋል።
-  የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በተመሳሳይ ከአባላት ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች ላይ አግዷል። የወረደውንም አስጠፍቷል።
- ካናዳ የመንግሥት መሳሪያዎች ላይ እንዳይሰራ፣ የመንግሥት ሰራተኞችም እንዳያወርዱት አድርጋለች።
- የዴንማርክ መከላከያ ሰራዊት ሰራተኞቹ በሙሉ እንዳይጠቀሙ አድርጓል። ስልካቸው ላይ ተጭኖ የነበረውንም አስጠፍቷል።
- ኖርዌይ በመንግሥት ሰራተኞች ስልክ ላይ እንዳይሰራ አድርጋለች።

በተጨማሪ ፦

* አፍጋኒስታን #ወጣቶችን ከአጓጉል ነገር ለመጠበቅ በሚል 2022 ላይ አድግዳለች።

* ኪርጊስታን በዚህ ዓመት የሀገሪቱን ባህል ወግ እና ስርዓት እየበረዘው ፣ ለልጆች፣ ለወጣቶች የአእምሮ ጠንቅ ነው በማለት አድጋለች።

* ኔፓል እና ሶማሊያም እንዲሁ እንዲታገድ ከወሰኑ ሀገራት መካከል ናቸው።

አሜሪካ ለማገድ እያደረገች ያለችው እንቅስቃሴ አለ ?

ካለፈው ዓመት ህዳር ጀምሮ እጅግ በርካታ ግዛቶች " ቲክቶክ " ን  ከመንግስት መሳሪያዎች አግደዋል።

የዩኒቨርሲቲዎች ለምሳሌ ፦ እንደ ቴክሳስ ፣ ኦውበርን ፣ ቦይስ ስቴት ዩኒቨርሲቲዎች አፕሊኬሽኑ #በዋይፋይ እንዳይሰራ አድርገው አግደዋል።

አሜሪካ ውስጥ ከደህንነት ጋር በተያያዘ ብቻ ሳይሆን ቲክቶክ ሱስ የሚያሲዝ እንደሆነና ወጣቶችን እና ህፃናት ልጆችን አሉታዊ ተፅኖ ያሳድራል በሚል የሚከሱ ግዛቶችም አሉ።

ኮንግረሱ ቲክቶክ እንዲታገድ ይፈልጋል ? እንዲታገድ የሚፈልጉ የኮንግረሱ አባላት አሉ። (ከዚህ ቀደም የቀድሞው ፕሬዜዳንት ትራምፕ የማገድ እንቅስቃሴን እንዲቆም መደረጉ ይታወሳል)

ምንም እንኳን አሜሪካ ውስጥ በመንግሥት መሳሪያዎች ላይ እንዲሁም በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች ዋይፋይ ቲክቶክ ቢታገድም 150 ሚሊዮን ነው ተብሎ ከሚገመተው ተጠቃሚ ላይ እንዲታገድ ለማድረግ ረጅም ሂደት ሊጠይቅ እንደሚችል በዘርፉ ላይ ያሉ ፀሀፊዎች ይናገራሉ።

" ቲክቶክ " በየጊዜው የሚነሱበትን በተለይም የደህንነት እና የቁጥጥር ክሶች ውድቅ ሲያደርግ ቆይቷል።

@tikvahethiopia
' ቤቲንግ ' ሊታገድ ነው ?

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ቤቲንግ " ሊታገድ መሆኑን የሚገልፁ በትክክል ምንጫቸው ያልተገለፁ ፅሁፎች ሲሰራጩ ተስተውሏል።

ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን እየተሰራጩ ያሉት መልዕክቶች ፍፁም ስህተት ናቸው ብሏል በማህበራዊ ትስስር ገፁ ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ።

" ' አንዳንድ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ ቤቲንግ ሊዘጋ ነው ' በማለት የሚያሰራጩት መልእክት ፍጹም ስህተት መሆኑን እንገልፃለን " ያለው አስተዳደሩ " የስፖርት ውርርድ ጨዋታዎችም ሆነ  ሎተሪን   በተመለከተ ማንኛውም መረጃ ከብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ብቻ ማግኘት እንደሚገባ አመልክቷል።

ከዚህ ቀደም ከ ' ቤቲንግ / ስፖርታዊ ውርርድ / ' ጋር በተያያዘ ፤ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር #እንዲታገድ እየሰራ መሆኑን አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል።

ሚኒስቴር መ/ቤቱ  ፤ ከታዲጊዎች እና ወጣቶች ስብዕና ግንባታ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ከሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች አንጻር ነው ዘርፉ #ሊታገድ ይገባል በሚል እየሰራ እንደሆነ አሳውቆ የነበረው።

የስፖርት ውርርድ ' ቁማር ነው ' ብሎ የሚያምነው ይኸው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ፤ በተለያየ ጊዜ ሰርቻቸዋለሁ ባላቸው የዳሰሳ ጥናቶች ቤቲንግ ለወጣቱና ለታዳጊው ዘርፈ ብዙ አደጋ የደቀነ መሆኑን አመላካች መሆኑን ፤ ቁማር ታዳጊዎችን ይሁን አዋቂ ሰዎችን ወዳልተፈለገ መንገድ ሊወስድ የሚችል ማህበራዊ ቀውስ እንደሆነና ማንኛውም ሰው ሰርቶ የመለወጥ እሳቤውን የሚያቀጭጭ፣ ቤተሰብን ጭምር ወደ መበተን ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ መሆኑን አስገንዝቦ ነበር።

ወጣቶች እና ታዲጊዎች ለቤቲንግ ውርርድ ሲሉ ያላቸውን ነገር በሙሉ እስከማውጣት ይደርሳሉ ፤ ወጣቶች ስራን ከመስራት ይልቅ በአቋራጭ መክበር እንዲያስቡ በማድረግ ምርት እና ምርታማነትን የሚቀንስ ተግባር ነው የሚልው መ/ቤቱ ቤቲንግ እንዲታገድ ፍቃድ ለሚሰጡት የንግድ ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተቋማት አስፈላጊውን የግንዛቤ እና የማሳወቅ ስራ ቢሰራም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ባለማድረጋቸው ለውሳኔው መዘግየት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ገልጾ ነበር።

የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ቤቲንግ እንዲታገድ ብርቱ እንቅስቃሴ ማድረግ መጀመሩን ካሳወቀ ወራት ቢቆጠርም እስካሁን በጉዳዩ ላይ አዲስ ነገር የለም።

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን በ ' ቤቲንግ ' ኮሚሽን (15%) በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያስገኛል (ለሀገር) ፣ በርካታ ሰው በተለይ ሴቶችን ቀጥሯል ፣ ለማህበራዊ ጉዳይ ከገቢው ያውላል ፣ ቤት ይከራያል ፣ ገንዘብ ኢኮኖሚ ውስጥ እንዲንቀሳቀስ ያደርጋል ... ይህ ሁሉ ጥቅሞቹ ናቸው ብሎ ያምናል።

" ቤቲንግ " አትራፊ እንደሆነ የሚገልጸው አስተዳደሩ " ጨዋታ " እንጂ " ቁማር " አይደለም ብሎ ያምናል። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎችን አውጥቶ እየሰራ እንደሆነና " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ፤ ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ባይ ነው።

ማህበራዊ ቀውስ ያመጣ እንደሆነ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት አጥንተው ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል በሚል ከሚታገድ በህግ እንዲመራና የማይገባቸው ሰዎች እንዳይጫወቱ ክትትል  ቢደረግ የተሻለ መሆኑ ታምኖበት እየተሰራ እንደሆነ በከወራት በፊት ገልጿል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ " ከጥር 3 ጀምሮ ቤቲንግ ይታገዳል " የሚሉ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች በስፋት ሲሰራጩ የነበረ ሲሆን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ይህ ፍፁም የተሳሳተ ነው ፤ ማንኛውም ቤቲንግ / የስፖርት ውርርድ ነክ መረጃ የሚገኘው ከኔው ነው እንጂ ከሌላ አይደለም ሲል አስገንዝቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
ቀላል የመክፈያ ዘዴ ከቴሌብር !

በቴሌብር ሱፐርአፕ ወይም *127# ግብይት ሲፈፅሙ ከአገልግሎት አቅራቢዎች/ነጋዴዎች በሚደርስዎ የክፍያ መጠየቂያ መልዕክት መሠረት የተጠየቁትን የክፍያ መጠን እና የጠያቂውን ማንነት አረጋግጠው የሚስጥር ቁጥርዎን ብቻ በማስገባት ክፍያዎን መፈጸም ይችላሉ፡፡

ቴሌብር - ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጊዳሚ በምዕራብ ኦሮሚያ ቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ጊዳሚ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን ጸሎት ላይ የነበሩ ዘጠኝ ሰዎች ተወስደው ተገድለዋል። ድርጊቱ የተፈፀመው አርብ ኅዳር 14/2016 ዓ.ም. ሌሊት 8 ሰዓት አካባቢ ነው። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የወንጌል እና ቲዎሎጂ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ለሊሳ ዳንዴል ምን አሉ ? (ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ…
" ቤተክርስቲያን ለፍትህ ድምጿን  ስታሰማ ብትቆይም ምላሽ የተሰጠበት አንድም ጊዜ አልነበረም " - መካነ ኢየሱስ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፤ በኦሮሚያ ክልል ቄሌም ወለጋ ዞን፤ በጊዳሚ ወረዳ በአባላቶቿ ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልከቶ  ዛሬ መግለጫ አውጥታለች።

በመግለጫዋ ፤ በኦሮሚያ ክልል፣ በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፤ መነ ሃሞ በመባል በሚታወቀው ቀበሌ " ቶኩማ መነ ሃሞ " በተሰኘ የመካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን ህዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ በቤተ ክርስቲያን በጸሎት ላይ  ከነበሩት 17 ሰዎች መካከል ማንነታቸው ተጣርቶ ባልታወቁ ታጣቂዎች 9 የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ላይ የጅምላ ግድያ መፈጸሙ በሚዲያዎች መግለፁን ጠቁማለች።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን በሚመለከት መረጃዎችን ለማግኘት የሚቻላትን ሁሉ ስታደርግ የነበረ ቢሆንም፤ መንግስትም ባለው ሃላፊነት መሠረት ሁኔታውን አጣርቶ ለህዝብ ይፋ ያደርጋል በሚል ተስፋ እስካሁን ዝምታን መርጣ መቆየቷን ገልጻለች።

ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የተገደሉት ሰዎች ከፖለቲካ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው ንጹሐን ዜጎች መሆናቸውን የገለፀው ቤተ ክርስቲያኒቱ ድርጊቱን በጽኑ አውህዛ ፤ ኃዘንዋን ገልጻለች።

የዚህ እኩይ ተግባር ሰለባ የሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት፡-

1. ተሊላ ላሜሳ ታሲሳ
2. ቶሊና ላሜሳ ታሲሳ
3. ታምራት ላሜሳ ታሲሳ
4. ቀበና ቡልቻ ጉተማ
5. ጌታቸው ቤከታ ታይሳ
6. ሂካ አያና ያደሳ
7. ጅረኛ ድንገታ ቴሶ
8. ሰለሞን ድንገታ ቴሶ
9. ሲራጅ ደኑ መሆናቸውንና ሁላቸውም በወጣትነት ዕድሜ ክልል ውስጥ የነበሩ እንደሆኑ ገልጻለች።

አምስቱ ከሁለት ቤተሰቦች የሆኑ ወንድማማች ሲሆኑ ከዘጠኙ አራቱ የቤተሰብ ኃላፊዎች ናቸው ብላለች።

ቤተክርስቲያኒቱ በጊዳሚ የተከሰተው ይህ በግፍ መገደል በዓይነቱ የመጀመሪያ እንዳልሆነ ገልጻለች።

ከዚህም በፊት በተለያዩ ቦታዎች፤ ለምሳሌ፦

- ባለፈው ዓመት በምስራቅ ወለጋ በሳሲጋ ወረዳ 15 የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን በዕሁድ የአምልኮ አገልግሎት ላይ እያሉ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በጅምላ ተገድለዋል።

- በምዕራብ ወለጋ ዞን በቦጂ ወረዳ በዕሁድ አምልኮ ላይ የነበሩ ሶስት ወጣቶች በታጣቂዎች ተገድለዋል።

በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች በምእመናን ላይ ተመሳሳይ ድርጊቶች እየተከሰቱ መሆኑን ጠቅሳለች።

ለነዚህ ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለፍትህ ድምጽዋን ስታሰማ ብትቆይም ምላሽ የተሰጠበት አንድም ጊዜ አንዳልነበር አስረድታለች።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌደራል መንግስትና የክልል ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ እና የዳኝነት አካላት ብርቱ ክትትል በማድረግ ህዳር 14/2016 ዓ/ም እና ከዚያም በፊት ላይ የተፈጸመውን በደል እንዲጣራና አጥፊዎቹ ወደ ህግ እንዲቀርቡ ያደርጉ ዘንድ መንግስትን ዳግመኛ አበክራ ጠይቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ከጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም  ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ቀደም ሲል በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። ቀደም ሲል የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ? - ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም - ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም - ኬሮሲን በሊትር…
#እንድታውቁት

የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ #ባለበት ይቀጥላል ተብሏል።

የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባለበት እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ቀደም ሲል የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።

@tikvahethiopia
#ኮሬ #ዳርባማናና

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ዳርባ ማናና ወረዳ 2 ወጣቶች መገደላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአከባቢው ነዋሪዎች ለማወቅ ችሏል።

አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የቀድሞ አማሮ ልዩ ወረዳ ባለሥልጣን ደግሞ ፤ ወጣቶቹ የተገደሉት ሲጠፉ የነበሩ መከላከያ ሠራዊትን ለማስመለጥ ሞክራችኋል ተብለው እንደሆነ ተናግረዋል።

በመንግስት የፀጥታ ኃይል የተገደለው አንደኛው ወጣት ሳሙኤል ሰለሞን እንደሚባልና ይኸው ወጣት ቀጥታ ሞተር ሳይክል ላይ እንደነበር ተመቶ እንደተገደለ ገልጸዋል።

ሌላኛው አቡለ ጸጋዬ የተባለ ወጣት ጉጂ ቦሬ ወደ ተባለ ካምፕ ከተወሰደ ከቀናት በኃላ ስቃይ ተፈፅሞበት መገደሉን ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢው ነዋሪ  በበኩላቸው ፦

* ከመከላከያ ሲኮበልሉ የነበሩ አባሎችን ሲፈልጉ የነበሩ የመንግሥት ሠራዊቶች ሁለት በሞተር ሲጓዙ የነበሩ ወጣቶችን ኮሬ ዞን ሸሮ ቀበሌ ሙራ ማንቻ የሚባል ቦታ ምሽት አራት ሰዓት ላይ እንዳገኟቸው ገልጸዋል።

* አንዱ ከጸጥታ ኃይሎቹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያው እንደሞተ ፣ ሌላኛውን ደግሞ ለማምለጥ ሲሞክር ይዘውት ወደ ሌላ ቦታ ወስደውት እንደነበር ፤ በኃላም እሁድ 7 ሰዓት ላይ እንደተረሸነ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተፈጸመ ስለተባለው ግድያ ምን ምላሽ እንዳላቸው የኮሬ ዞን ምክትል ፖሊስ አዛዥ አቶ ሲዳሞ ማደቦን ጠይቋል።

ምክትል ፖሊስ አዛዡ  ፤ " በዚህ ነገር ላይ እኔ መግለጫ መስጠት አልችልም፣ ምክንያቱም ወጣቶች በሆነውም ባልሆነውም ቅሬታ ሊያቀርቡ ይችላሉ። መንግሥት እንደ መንግሥት እርምጃ ሊወስድ ይችላል " ብለዋል።

አክለውም፣ " የምሰጠው ነገር ከሕግ ጋር ሊጋጭ ስለሚችል ተነጋግረን ነው መረጃ የምንሰጠው " ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ለዞኑ ፓሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አራርሶ ነጋሽ አቅርቧል።

ሁለት ወጣቶች በጸጥታ ኃይል ለምን እንደተገደሉ ሲጠየቁ ከአሥር ደቂቃ በኋላ እንዲደወል ቀጠሮ ቢሰጡም በቀጠሮው ሰዓት በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

በተጨማሪ፦ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና ምላሽ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ። የወከሉት ሕዝብ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እየተተኮሰበት እየተገደለ እንደሆነ እየገለፀልን ነው ፤ በዚህ ጉዳይም ከ10 ደቂቃ በኋላ ደውሉ ብለው ነበር " ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተላከላቸው የጽሑፍ መልዕክትም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ ባለፈ ፦

- የኮሬ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ አየለ ስልክ ባላማንሳታቸው፣

- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ "ስብሰባ ላይ ነኝ" በማለታቸውና በድጋሚ ሲድልወልም ስልክ ባለማንሳታቸው ምላሻቸውን ለማካተት አልቻልንም።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) የክልሉ ቅርንጫፍ በበኩሉ፣ ስለሁለቱ ወጣቶች እስካሁን መረጃ ባይደርሰውም በዞኑ ባለው የጸጥታ ችግር ነዋሪዎች እየተደበደቡ መሆኑን ከዚህ በፊትም እንደተከታተለ አስረድቷል።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia