TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NationalExam

"...በፈተናው ዙሪያ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም አካል አንታገስም" - የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ የካቲት 29/2013 በሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ በክልሉ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም አካል አንታገስም አሉ።

ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ይህን ያሉት ዛሬ በባህርዳር በነበረ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ላይ ትኩረት ያደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው።

ኮሚሽነሩ የክልሉን ሰላም የማይፈልጉ አካላት ፈተናውን እንዳያደናቅፉ በቅንጅትና በልዩ ትኩረት ይሰራልም ብለዋል።

በተጨማሪ ተማሪዎች የረጅም አመት ውጤታቸውን የሚያዩበት ጊዜ በመሆኑ የፀጥታ መዋቅሩ በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።

በተለይም የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ልዩ የፀጥታ ሀይል ስምሪት ይደረጋል ያሉ ሲሆን የፀጥታ ተቋሙ ችግሮች ሲፈጠሩ ፈጣን ውሳኔዎችን መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡

ፈተናውን የሚያውኩ ማንኛውም መረጃ ፈጥኖ ለፖሊስ አካላት መስጠት ከህብረተሰቡ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዛሬው የምክክር መድረክ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱና ትክክለኛ ምንጫቸው ከማይታወቁ መረጃዎች ራሳቸውን በመጠበቅ የተዘጋጁበትን ፈተና እንዲፈተኑ ጥሪ ቀርቧል።

በ2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ምክንያት ሳይሰጥ የቀረው የ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሊሰጥ 10 ቀናት ብቻ ቀርቶታል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NationalExam

የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ከየካቲት 29 ቀን 2013 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በተሳካ መልኩ እንዲጠናቀቅ ከ4 መቶ በላይ የፖሊስ ሀይል አባላት ስምሪት እንደተሰጣቸዉ ለአሃዱ ሬድዮ ኤፍ ኤም 94.3 አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም ይፈጠሩ የነበሩ ችግሮች እንዳይከሰቱ የዲጅታል ደህንነት እና የአካላዊ ደህንነት መፈተሻዎች መዘጋጀታቸዉ ተገልጿል፡፡

ፈተና በሚካሄድባቸዉ ቀናት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ተሟልተዋል ያሉ ሲሆን ለፈታኞች እና ለተቆጣጣሪዎች ማብራሪያ የመስጠት እንዲሁም የመፈተኛ ክፍሎችን ማዘጋጀት በስፋት እየተሰራባቸዉ መሆኑን ሀገር አቅፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለሬድዮ ጣቢያው (አሃዱ FM 94.3) አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NationalExam

በአ/አ ከተማ የ12ኛ ክፍል ፈተና ያለ ምንም እንከን እንዲካሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠየቀ።

ዛሬ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የመማር ማስተማር ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መቀጠል በሚችልበት ጉዳዮች ዙሪያ ከሁሉም ትምህርት ቤቶች ከተውጣጡ ርዕሳነ መምህራንና ሱፐር ቫይዘሮች ጋር ውይይት አካሂዷል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኜ ገብሩ ርዕሰ መምህራን በየትምህርት ቤቱ የሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮችን በበላይነት መከታተል እና ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮችን የሚከታተል የአብይ እና ቴክኒክ ኮሚቴ እንደሚዋቀር አሳውቀዋል።

ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀ ሁሉን ኃላፊነቱን ይወጣ ተብሏል።

በሌላ በኩል ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በየትምህርት ቤቱ የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት ከወዲሁ መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

መረጃው ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትምህርት_ሚኒስቴር የ2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ…
#NationalExam

የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል።

የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።

ፈተናው ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ተብሏል።

የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ከቀናት በፊት መገለፁ ይታወሳል።

የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም።

ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE " የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች…
#NationalExam

መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና " ተሰርቆ ወጥቷል " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን  የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የዘንድሮ " ነው ተብሎ የሚሰራጨው ፈተና በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ እንደሆነ አስረድተዋል። እየተሰራጩ ያሉት ፈተናዎች ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ መሆኑንም አመልክተዋል።

" ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ " መልዕክታቸውን አስተላፈዋል።

የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት " ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው " ሲሉ ለ " ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

የ2014 ዓ/ም የሀገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር የሚሰጥ ይሆናል።

ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንደሰማነው ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ይገኛል ፤ ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
* ብሔራዊ ፈተና የ2014 ዓ/ም 12ኛ ክፍል ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። በዚህም መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች በአካዳሚክ ካላንደራቸው ላይ ማስተካከያ እያደረጉ ይገኛሉ። ይህ እየተደረገ ያለው ተማሪዎች ፈተናቸውን በሚወስዱበት ወቅት በቅጥር ግቢዎቹ ውስጥ ማንኛውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ መገኘት ስለሌለበት ነው። በሌላ በኩል ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት #ለሪፖርተር_ጋዜጣ…
#NationalExam

ለ12ኛ ክፍል የብሄራዊ ፈተና አስፈፃሚዎች ስልጠና ተሰጣቸው።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ማጠናቀቂያ ፈተና አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደተሰጣቸው ገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፈንታ ማንደፍሮ የፈተና አስፈፃሚዎች ትልቅ ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን በመገንዝብ በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ በማሳሰብ ዝርዝር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ፤ የፈተና አስፈፃሚዎች በቂ ትኩረት በመስጠት ያለ ምንም አድልዎ ሙያዊ በሆነ አግባብ እንዲሁም በቁርጠኝነት የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አስገንዝበዋል።

ዝርዝር ስልጠና በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አመራርና በዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

የ2014 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከመጪው መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በሁለት ዙር ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

ፎቶ : የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ተፈታኞች በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ ዕድል ይሰጣቸዋል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በእርግዝና ላይ ላሉ እና ወልደው ህጻንን ጡት እየመገቡ ላሉ ለተመዘገቡ ሴት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የእነርሱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የመፈተኛ ስርዓት በቀጣይ መዘጋጀቱን አሳውቋል። በመሆኑም ተፈታኞቹ ከመስከረም…
#NationalExam

የ2014 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከነገ መስከረም 30 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።

ነገ ፈተናቸውን የሚፈተኑት በመጀመሪያ ዙር ወደ መፈተኛ ማዕከላት / ዩኒቨርሲቲ የገቡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።

ተማሪዎቹ ስለፈተናው አጠቃላይ (ኦረንቴሽን) ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

በፈተና ወቅት መከተል ስላለባቸው የስነምግባር መርሆች፣ የሰዓት አከባበርን በተመለከተ ፣ የተብራራላቸው ሲሆን የመፈተኛ ጣቢያ እና ክፍላቸውን ለይተውም እንዲያውቁ መደረጉን ሰምተናል።

ከተፈታኝ ተማሪዎች በተጨማፊ ፈታኞች፣ ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ገለፃ (ኦረንቴሽን) ተሰጥቷቸዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጥዋት ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2 ድረስ ይሰጣል፤ ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 4 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።

የ12ኛ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናው ጥብቅ በሆነ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ተገልጾልናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተፈታኞች በሙሉ መልካም ፈታናን ይመለኛል!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ እና ነገ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ማእከላት / ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ። ይህ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ጥብቅ በሆነ ህግ መሰጠት ከመጀመሩ ጋር በተያያዘ ፈተናቸውን ጨርሰው የወጡት " የማህበራዊ ሳይንስ " ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የተመለከቱትን እና በቀጣዩ " የተፈጥሮ ሳይንስ " ፈተና ወቅት ሊስተካከለ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች በዝርዝር…
#NationalExam

የ12ኛ ክፍል " የተፈጥሮ ሳይንስ " ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ማዕከላት መግባት ጀምረዋል።

ተማሪዎች ነገ ተጠቃለው የሚገቡ ሲሆን ጥቅምት 07/2015 ዓ.ም ገለጻ (ኦሬንቴሽን) ይሰጣቸዋል።

ከጥቅምት 08 እስከ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ፈተናቸውን ይወስዳሉ።

ከዚሁ ከሁለተኛ ዙር ፈተና ጋር በተያያዘ የባለፉት ክፍተቶች መታረም ያለባቸው ሲሆን፤ ትምህርት ሚኒስቴር  ሴት ተፈታኝ ተማሪዎች ላይ በቀን ሆነ በማታ ምንም አይነት ትንኮሳ እንዳይደርስ እና ፈተናውን ተረጋግተው እንዳይወስዱ የሚያደርጉ ጫናዎች እንዳይፈጠሩ እንዲሁም ምቾታቸውን ሆነ ደህንነታቸውን አደጋ ላይ የሚጥል እንቅስቃሴ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ማደረግ ይኖርበታል።

የፀጥታ ኃይሎች የግቢ መውጫ እና መግቢያ ላይ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ዙርያ ገባው ላይ ቁጥጥራቸውን ማጠንከር እንዳለባቸው የከዚህ ቀደም ተፈታኝ ተማሪዎች ጠቁመዋል። (በአጥር የተከለከሉ ነገሮች እንዳይገቡ)

ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆናችሁ የ2014  የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ሁሉንም የፈተና ህጎችን በማክበር በመረጋጋት፣ በከፍተኛ የራስ መተማመን እንዲሁም በብሩህ ተስፋ ፈተናችሁን እንድትወስዱ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ደግሞ እነዚህ ታዳጊዎች አሁን ለተተገበረው የፈተና ስርዓት/ለዩኒቨርሲቲም  አዲስ በመሆናቸው ማበረታታ እና መደገፍ እንጂ ባልተረጋገጠ መረጃ እንዲረበሹ፣ ተስፋ እንዲቆርጡ፣ በራሳቸውን እንዳይተማመኑ ማድረግ የለባችሁምና ስለምታጋሩት መልዕክት ጥንቃቄ አድርጉ እንላለን።

ተማፅኖ፦ ተፈታኝ ተማሪዎችን ወደ ፈተና ማዕከል በማጓጓዝ ላይ አሽከርካሪዎች በእርጋታ እና በጥንቃቄ ማሸከርከር እንዳትዘነጉ እንማፀናለን።

መልካም ፈተና!
Tikvah Family!

@tikvahethiopia
#NationalExam

2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

በሁለተኛው ዙር ለፈተና የሚቀመጡ የሁሉም ክልል ተማሪዎች መለየታቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ፦

• የመጀመሪያውን ዙር ፈተና በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣

• በሕግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው ለመፈተን ያልቻሉ፣

• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣

• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣

• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣

• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣

• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።

@tikvahuniversity
#NationalExam

" ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን አይፈተንም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጋቢት 20 እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በበይነ መረብ አማካይነት እንደሚከናወን ነው የተገለፀው።

የፈተና ሂደት ላይ ችግር እንዳይፈጠር ተማሪዎች መረጃዎቻቸውን በወቅቱ ማስመዝገብ እንዳለቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የመደበኛ እና የማታው ክፍለ ጊዜ ተማሪዎች ምዝገባ በትምህርት ቤቶች እንደሚካሄድ የተጠቀሰ ሲሆን ተማሪዎች የምዝገባ ሂደቱን ለማካሄድ በአካል መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡

የድጋሚ ተፈታኞች እና የርቀት ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ በተመረጡ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ይካሄዳል።

የምዝገባ ሂደቱ በተጠቀሱት ቀናት ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚከናወን ሲሆን ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን እንደማይፈተን አገልግሎቱ አሳውቋል።

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

ለምዝገባ ምን ያስፈልጋል / ተማሪዎች ምን ማሟላት አለባቸው ?

- መደበኛ ተመዝጋቢዎች ከ9 - 12ኛ ክፍል በተከታታይ ሲማሩ የነበሩ እና በ2015 ዓ.ም  በመማር ላይ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

- የማታ እና የርቀት ተማሪዎች የ11ኛ ክፍል ሶስት ሴሚስተር እንዲሁም ለ12ኛ ክፍል የሁለት ሴሚስተር የትምህርት ማስረጃ ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

- ድጋሜ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም የተፈተኑበትን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ መመዝገብ አለባቸው።

- ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በአካል ተገኝተው በበይነ መረብ መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።

ፈተናው መቼ እና የት ይሰጣል ?

ፈተናው የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተም  ፈተናው በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥና ቀኑ ወደ ፊት የሚገለፅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

Credit : #MoE

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#NationalExam

የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ።

ተቋማቱ አጠቃላይ ያሉበትን ደረጃ እየገመገሙ ናቸው።

ፈተናው የተሳለጠ እንዲሆን ተቋማት በዚህ ሳምንት ተመራቂ ተማሪዎቻቸውን በማስመረቅ በቶሎ ይሸኟቸዋል።

ከሐምሌ 16 ጀምሮ ተቋማት ለ12ኛ ክፍል ፈተና #ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቡ አይዘነጋም።

ከትምህርት ምዘናና ፋተናዎች አገልግሎት ባገኘነው መረጃ መሰረት ፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሐምሌ 16 -17 / 2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ ፤ ሐምሌ 18 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣቸዋል፤  ከሐምሌ ከ19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3ት ቀናት ይሰጣቸዋል ፤ ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ፤ ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል ፤ ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይወስዳሉ ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam

ከነገ ሐምሌ 19 ጀምሮ በሚጀምረው ሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ከፈተና ደንብ ውጭ ማንኛውም እንቅስቃሴ ካደረጉ / ጥፋት ከፈፀሙ ውጤታቸው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ #ሊሰረዝባቸው ይችላል።

ፈተና በከፊል የሚያሰርዙ ጥፋቶችን አጥፍተው የተገኙ ተፈታኞች ጥፋቱ የተመዘገበባቸው ፈተና ውጤት ብቻ ነው የሚሰረዝባቸው።

ተፈታኞች በፈተናው ወቅት የፈፀሙት ጥፋት ሙሉ በሙሉ ፈተናቸውን እንዲያሰርዝ የሚያደርግ ከሆነ  ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ ይሰረዝባቸዋል።

ዝርዝሩን ከላይ ያንብቡ።

@tikvahethiopia
#NationalExam

በባለፈው አመት በጎንደር ከተማ በነበረው ግጭት ምክንያት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይሰጥ የነበረውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ  ፈተና ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናት ወደ ተቋሙ በመግባት ፈተናውን መውሰዳቸው ተገልጿል።

በአጠቃላይ በፀጥታ ችግር ፈተናውን ማጠናቀቅ ሳይችሉ ቀርተው የነበሩ 11 ሺህ 851 ተማሪዎች መስከረም 10/2016 ዓ.ም እና መስከረም 11/2016 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ገብተው ፈተናውን ወስደዋል።

ተማሪዎቹ የኬሚሰትሪ፣ ባዮሎጂ እና የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ፈተና እንደወሰዱ ተጠቁሟል።

ተፈታኝ ተማሪዎች ለክልሉ ሚዲያ (አሚኮ) በሰጡት ቃል ፤ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው በፍጥነት አርሞ ውጤቱ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ይፋ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

በሀገር አቀፍ ፈተናዎች አገልግሎት የፈተና ጣቢያ ኃላፊ ሄነው የተመደቡ አቶ ወንድወሠን ሽፈራው ፤ የተማሪዎች ፈተና ቶሎ ታርሞ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር በኩል መረጃ እንዳላቸው ገልጸዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትም ፤ የተማሪዎቹ ፈተና በፍጥነት ታርሞ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና #ውጤት በፀጥታ እና በሌሎች ምክንያቶች ፈተናቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከወሰዱ በኃላ እንደሚገለፅ ማሳወቁ ይታወሳል።

አገልግሎቱ ከዚህ ቀደም እንዳሳወቀው ከሆነ አሁን ፈተናቸውን የተፈተኑ ተፈታኞች ከመጀመሪያው ዙር ፈተና ተፈታኞች ጋር አንድ ላይ ውጤታቸው ይገለጻል።

በቅርቡ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ማንጠግቦሽ አዳምጤ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፈተናውን የማረም ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረው ምናልባትም እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam

" የ12ኛ ክፍል ፈተና ዝግጅት እየተገባደደ ነው ፤ ... በቀጣይ የፈተናው ሕትመት ይጀመራል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

ለ2016 የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የፀጥታ ችግር በሌላባቸው አካባቢዎች ብቻ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በዛሬው ዕለት አሳውቋል።

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው ሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የተማሪዎች ምዝገባ ተካሂዶ መጠናቀቁን የገለጸው መ/ቤቱ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለብሄራዊ ፈተናው ምዝገባ ማከናወናቸውን ጠቁሟል።

የፀጥታ ችግር ባለባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በዚህ ሣምንት ይከናወናል ብሏል።

የፈተና ዝግጅት ሥራው የሀገሪቱን ሥርዓተ ትምህርት የተከተለ እና ተማሪዎቹን በአግባቡ መመዘን በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን አገልግሎቱ ገልጿል።

የፈተናው ዝግጅት እየተገባደደ መሆኑን አመልክቶ በቀጣይ #የፈተናው_ሕትመት እንደሚጀመር አሳውቋል።

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የመስጫው የጊዜ ሰሌዳ ወደፊት ይፋ እንደሚሆንም የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ኢዜአ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ብሔራዊ_ፈተና

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም ፤ ያንን ለመከላከል ዝግጅት ተደርጓል  " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በበይነ መረብ / #በኦንላይን የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሳይበር ጥቃት እንዳይሰረቅ ዝግጅት መደረጉን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ " በዚህ ዓለም ምንም አይነት ችግር የሌለበት ነገር የለም። ሁሉም ነገር የራሱ የሆነ ችግር / ጉድለት ይኖረዋል ያለን ምርጫች ግን ችግሩን የመከላከል አቅም ጎን ለጎን መገንባት ነው " ብለዋል።

" በበይነ መረብ የሳይበር ጥቃት በመፈጸም ፈተናውን ለመስረቅ ጥረት አያደርጉም ብለን እንጠብቅም " ያሉት ዋና ዳይሬክቲ ፥ " የሳይበር ደህንነት (ሴክዩሪቲ) ስራዎች ፦
° ሞያው ባላቸው ፣
° መሳሪያዎች ባሏቸው
° አቅም ባላቸው ተቋማት በኩል ተገቢ የሆነ ዝግጅት አድርገን እየሰራን ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ፈተናው ብዥታ ለመፍጠር የሚፈልጉ ፣ ፈተናው ላይ ጥቃት ለመፍጠር የሚያስቡ አካላት ማወቅ ያለባቸው ይሄ #የፖለቲካ#የሃይማኖት ጉዳይ አይደለም ማንም ወላጅ ልጁን አስተምሮ የሚያደርስበት ስለሆነ ሁለት ሶስቴ ማሰብ አለባቸው ፤ ተማሪዎቹ ነገ ለሀገር እዳ እንዳይሆኑ ማሰብ ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል።

ከኦንላይን ፈተናው ጋር በተያያዘ ማንም አካል ወላጆችን " ኮምፒዩተር አቅርቡ " አላለም ፤ ሊጠየቁም አይገባም ከተጠየቅም ስህተት ነው ተብሏል።

ፈተና የሚሰጠው መንግሥት በሚያቀርበው አቅርቦት / ኮምፒየተር እንደሆነ ተመላክቷል።

ይህ ማለት የኮምፒዩተር አቅም ኖሯቸው ት/ቤታቸውን ማገዝ የሚፈልጉ ዜጎችን አይችሉም ማለት አይደለም ተብሏል።

የወረቅት ፈተናን በተመለከተ አሁን ላይ ህትመት ወደ መጠናቀቁ ሲሆን ፈተናው ልክ እንዳለፉት ፈተናዎች ደህንነቱ እንዲጠበቅ በቂ ዝግጅት መደረጉ፣ በክፍል ውስጥም ኩረጃ እንዳይኖርና ተማሪዎች በራሳቸውን ሰርተው እንዲያልፉ ካለፈው #በጠነከረ ሁኔታ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተገልጿል።

#Ethiopia
#NationalExam
#Grade12

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#NationalExam

" የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።

ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን አሳውቋል።

ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እንዲሁም በኦንላይን እንደሚሰጥ አረጋግጧል።

ተማሪዎች ይሄን ተገንዝበው ዝግጅታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር " ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራን ነው ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ተደርጓል " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል። ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ…
#ATTENTION🚨

" የበይነ መረብ (ኦንላይን) ተፈታኞች በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይ) እንዲሁም በወረቀት እንደሚሰጥ በዛሬው ዕለት በድጋሚ አሳወቀ።

በሁለቱም መንገድ ለሚሰጠው ፈተና ዝግጅት ተደርጓል ብሏል።

ትላንት እና ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች " የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተና ቀርቷል " እያሉ ለተማሪዎች መናገራቸውን እና የጽሁፍ መልዕክት በቴሌግራም ላይ መለጠፋቸውን የተማሪ ወላጆች እንዲሁም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

እንዲህ ያለው ውሳኔ የሚተላለፈው ከማዕከል ከትምህርት ሚኒስቴር ሆኖ ሳለ ፥ ትምህርት ቤቶቹ ውሳኔውን ማን እንዳሳለፈ በይፋ ያሉት ነገር ሳይኖር በደፈናው " ቀርቷል " የሚል ነገር ብቻ ነው የነገሯቸው።

በኋላም እራሳቸው ት/ቤቶቹ ቀድሞ ያሰራጩትን ያልተረጋገጠ መረጃ በማጥፋት የኦላንይን ፈተናው እንዳልቀረ መልሰው ገልጸዋል።

ዛሬ እሁድ ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው በፍጹም እንዳልቀረ በድጋሜ አረጋግጧል።

ብሔራዊ ፈተናውን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ለመፈተን ዝግጅቱን አጠናቅቆ የተማሪዎችን የመፈተኛ ቀን እየተጠባበቀ እንደሚገኝም አሳውቋል።

" ፈተናውን አስመልክቶ የተሳሳቱ መልዕክቶች በየጊዜው ትክክለኛ የትምህርት ሚኒስቴር ባልሆኑ ገጾች እየተለቀቁ ይገኛሉ " ሲልም ገልጿል።

ለተማሪዎች፣ ወላጆችና አሳዳጊዎች ባስተላለፈው መልዕክት ፈተናው ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት እንደተማሪዎች የቀደመ ምርጫ መሰረት ይሰጣል ብሏል።

አስቀድመው በወረቀት የመረጡ ወደተመደቡበት ዩኒቨርስቲ፣ በበይነ መረብ (ኦንላይን) የመረጡም በተመደቡበት የፈተና ጣቢያ ተገኝተው ፈተናውን እንዲወስዱ በጥብቅ አሳስቧል።

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ተማሪዎች ከላይ በምስሉ እንደተያያዘው አይነት ከሃሰተኛ ወሬ ራሳቸውን በመከላከል ለፈተናው የሚያደርጉትን ዝግጅት እንዲቀጥሉ አሳስቧል።

ለማንኛውም መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ብቻ እንዲከታተሉም አደራ ብሏል።

#TikvahEthiopia
#NationalExam
#MoE

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam

የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች መግባት ጀምረዋል።

ተፈታኞች ከትናንት ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ናቸው።

ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ይሰጣል።

በትግራይ ክልል ፈተናው ከሐምሌ 2 እስከ ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

በትግራይ በቀድሞ ስርዓተ ትምህርት የተማሩና በ2013 እና በ2014 የትምህርት ዘመን መፈተን የነበረባቸው ተፈታኞች ናቸው ፈተናቸውን የሚወስዱት።

ትምህርት ሚኒስቴር የዘንድሮውን ብሔራዊ ፈተና በወረቀት እንዲሁም የተመረጡ ተማሪዎች ደግሞ በኦንላይን እንደሚወስዱት አሳውቋል።

ዘንድሮ ከ700 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተናው ይቀመጣሉ።

የፀጥታ ችግር ባለባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር ፈተና ይዘጋጅላቸዋል።

@tikvahethiopia