TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከረጅም ርቀት በተተኮሰ ከባድ መሳሪያ 2 ህፃናት ልጆቿን ያጣች እናት አለች " - ዶ/ር ሁሴን አደም የህወሓት ኃይሎች በአፋር ያሎ በኩል በሰነዘሩት የከባድ መሳሪያ ጥቃት በአካባቢው ንፁሃን ነዋሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና በርካቶች በያሎ አካባቢ በሚገኘው የህክምና ጣቢያ ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ ተገልጿል። ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸውም ውስጥ ወደ ዱብቲ ጠቅላላ ሆስፒታል መጥተው ህክምና የተከታተሉ…
" የህፃናት ህይወት ተቀጥፏል " - UNICEF

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) ፤" አሁንም በድጋሚ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት የህፃናትን ህይወት ቀጥፏል " ብሏል።

ባለፉት ጥቂት ቀናት በትግራይ ክልል አዋሳኝ በሆነ #የአፋር_ክልል መንደር የተፈፀመ የከባድ መሳሪያ ጥቃት ህፃናትን ገድሏል ፤ በርካቶችንም ቁስለኛ አድርጓል ሲል ድርጅቱ አሳውቋል።

UNICEF በኢትዮጵያ ላሉ ህፃናትና ለወደፊት ህይወታቸው ሲባል ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ሁሉም ወገኖች እንዲስማሙ ተማፅኗል።

UNICEF በመግለጫው ላይ ጥቃት የደረሰበትን የአፋር ክልል መንደር በግልፅ ባይሳውቅም ከቀናት በፊት የህወሓት ኃይሎች በአፋር " ያሎ " በኩል በሰነዘሩት የከባድ መሳሪያ ጥቃት በአካባቢው ንፁሃን ነዋሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና በርካቶች በያሎ አካባቢ በሚገኘው የህክምና ጣቢያ ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ መገለፁ አይዘነጋም።

በጦርነቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተጎዱ ዜጎች ለተሻለ ህክምና ዱብቲ ሆስፒታሉ እንደገቡና ሆስፒታል ከገቡት ውስጥ 2 ህፃናት ልጆቿን ከረጅም ርቀት በተተኮሰ ከባድ መሳሪያ የተገደሉባት እናት እንደምትገኝ መገለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia