ቡርኪናፋሶ በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን የናይጄሪያ ወታደሮች አለመልቀቋ ተገለጸ።
11 የሚደርሱ የናይጄሪያ አየር ሀይል አባላት በሲ-130 የጦር ጄት የአየር ላይ ቅኝት እያደረጉ በነበረበት ወቅት በቡርኪናፋሶ ግዛት ውስጥ ማረፋቸው ተገልጿል።
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት "የአየር ክልሌን ጥሰዋል" በማለት ወታደሮቹን እና የጦር ጄቱን በቁጥጥር ስር አውሏል።
የቡርኪናፋሶ መንግስት ስለ ክስተቱ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ሁለቱ ሀገራት ላለፉት ስድስት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ ውይይት ቢያደርጉም ስምምነት ላይ አለመድረሳቸው ተገልጿል። #dw #politicsnigeria
@ThiqahETH
11 የሚደርሱ የናይጄሪያ አየር ሀይል አባላት በሲ-130 የጦር ጄት የአየር ላይ ቅኝት እያደረጉ በነበረበት ወቅት በቡርኪናፋሶ ግዛት ውስጥ ማረፋቸው ተገልጿል።
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት "የአየር ክልሌን ጥሰዋል" በማለት ወታደሮቹን እና የጦር ጄቱን በቁጥጥር ስር አውሏል።
የቡርኪናፋሶ መንግስት ስለ ክስተቱ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ሁለቱ ሀገራት ላለፉት ስድስት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ ውይይት ቢያደርጉም ስምምነት ላይ አለመድረሳቸው ተገልጿል። #dw #politicsnigeria
@ThiqahETH
❤3🙏1
የቀድሞው የኮንጎ "አማፂ ቡድን" መሪ ሮጀር ሉምባላ የ30 አመት እስር ተፈረደባቸው።
ሉምባላ ከ2002 እስከ 2003 በምስራቅ ኮንጎ ለተፈጸመው ወንጀል በፈረንሳይ ፍርድቤት እስር ተፈርዶባቸዋል።
ሁለተኛው የኮንጎ ጦርነት እየተባለ በሚጠራው ዘመን በጎረቤት ኡጋንዳ እየታገዘ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደፈጸመ ተገልጿል።
ሉምባላ "የፈረንሳይ ፍትህ የእኔን ጉዳይ የመመልከት ስልጣን የለውም" በማለት ፍርድቤት ሳይቀርብ ቆይቷል። #bbc
@ThiqahETH
ሉምባላ ከ2002 እስከ 2003 በምስራቅ ኮንጎ ለተፈጸመው ወንጀል በፈረንሳይ ፍርድቤት እስር ተፈርዶባቸዋል።
ሁለተኛው የኮንጎ ጦርነት እየተባለ በሚጠራው ዘመን በጎረቤት ኡጋንዳ እየታገዘ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደፈጸመ ተገልጿል።
ሉምባላ "የፈረንሳይ ፍትህ የእኔን ጉዳይ የመመልከት ስልጣን የለውም" በማለት ፍርድቤት ሳይቀርብ ቆይቷል። #bbc
@ThiqahETH
❤4👏2😱1
THIQAH
#ለጥንቃቄ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን የግል መረጃ #አደጋ ላይ የጣለ አዲስ የክሮም #Chrome ክፍተት ተገኝቷል። ይህን ተከትሎም ጎግል ለክሮም መረጃ ማፈላለጊያው #Browser በአስቸኳይ ሊተገበሩ የሚገባቸው ለሶስት አደገኛ ክፍተቶች መድፈኛ አዲስ ማሻሻያ #Patch መልቀቁን አስታውቋል። ከእነዚህ ክፍተቶች መካከል አንዱ በተለይ እጅግ አደገኛ ሲሆን፣ የግል መረጃዎችን ለመጥለፍ በመረጃ ጠላፊዎች…
ለመረጃ መንታፊዎች የሚያጋልጡ ጎጅ የስልክ አጠቃቀሞች ምንድን ናቸው?
-ያልተረጋገጡ አፕሊኬሽኖችን በስልካችን መጫን፦ ብዙዎቻችን ከዋናው የሶፍትዌር መደብር (Play Store/App Store) ውጭ ያሉ አፕሊኬሽኖች በተለያዩ ድረ-ገጾች አማካኝነት እንጭናለን። እነዚህ አፕሊኬሽኖች ስልካችንን ለመሰለል/መረጃ ለመሰረቅ የተዘጋጁ ቫይረሶችን ሊይዙ ይችላሉ።
-የሶፍትዌር ማሻሻያዎችን (Updates) አለማድረግ፦ የስልክ አምራቾች በየጊዜው የደህንነት ማሻሻያዎችን ይለቃሉ። እነዚህን ማሻሻያዎች ችላ ማለት ጠላፊዎች በድሮው የሶፍትዌር ስሪት ያሉ ክፍተቶችን ተጠቅመው ወደስልካችን ሰርገው እንዲገቡ ያጋልጣል።
-ለሁሉም አፕሊኬሽኖች "ፈቃድ" መስጠት፦ አንድ አፕሊኬሽን ስንጭን "Allow" የሚል ምርጫ ይጠይቀናል። ለአንድ ፎቶ ማቀናበሪያ አፕሊኬሽን ስልክ ቁጥሮችን፣ ያሉበትን ቦታ እንዲያይ ፈቃድ መስጠት አላስፈላጊ እና ለመረጃ ስርቆት ያጋልጣል።
-ደህንነታቸው ያልተጠበቁ የዋይፋይ (Public Wi-Fi) አጠቃቀም፦ ነፃ የዋይፋይ ኔትዎርኮች በቀላሉ ለመጠለፍ የተመቹ ናቸው። በእነዚህ ኔትዎርኮችን ተጠቅመን የባንክ አካውንት መክፈት/ሚስጥራዊ መረጃዎችን መላላክ ከፍተኛ አደጋ አለው።
-አጠራጣሪ ሊንኮችን መክፈት፦ "ሎተሪ ደርሶዎታል"፣ ወይም "ነፃ የኢንተርኔት ጥቅል" በሚሉ አሳሳች መልዕክቶች ያሉ ሊንኮችን መጫን ስልካችንን ለጠላፊዎች አሳልፎ ይሰጣል።
-ቀላል የይለፍ ቃላትን መጠቀም፦ እንደ "1234"፣ "0000" ወይም የልደት ቀንን የመሳሰሉ በቀላሉ የሚገመቱ የይለፍ ቃላትን መጠቀም ስልካችን በእጃችን ቢሆን እንኳ በሩቅ ሆኖ ለመገመት ለሚሞክር የመረጃ መንታፊ ስራውን ያቀልለታል። #INSA
@ThiqahETH
-ያልተረጋገጡ አፕሊኬሽኖችን በስልካችን መጫን፦ ብዙዎቻችን ከዋናው የሶፍትዌር መደብር (Play Store/App Store) ውጭ ያሉ አፕሊኬሽኖች በተለያዩ ድረ-ገጾች አማካኝነት እንጭናለን። እነዚህ አፕሊኬሽኖች ስልካችንን ለመሰለል/መረጃ ለመሰረቅ የተዘጋጁ ቫይረሶችን ሊይዙ ይችላሉ።
-የሶፍትዌር ማሻሻያዎችን (Updates) አለማድረግ፦ የስልክ አምራቾች በየጊዜው የደህንነት ማሻሻያዎችን ይለቃሉ። እነዚህን ማሻሻያዎች ችላ ማለት ጠላፊዎች በድሮው የሶፍትዌር ስሪት ያሉ ክፍተቶችን ተጠቅመው ወደስልካችን ሰርገው እንዲገቡ ያጋልጣል።
-ለሁሉም አፕሊኬሽኖች "ፈቃድ" መስጠት፦ አንድ አፕሊኬሽን ስንጭን "Allow" የሚል ምርጫ ይጠይቀናል። ለአንድ ፎቶ ማቀናበሪያ አፕሊኬሽን ስልክ ቁጥሮችን፣ ያሉበትን ቦታ እንዲያይ ፈቃድ መስጠት አላስፈላጊ እና ለመረጃ ስርቆት ያጋልጣል።
-ደህንነታቸው ያልተጠበቁ የዋይፋይ (Public Wi-Fi) አጠቃቀም፦ ነፃ የዋይፋይ ኔትዎርኮች በቀላሉ ለመጠለፍ የተመቹ ናቸው። በእነዚህ ኔትዎርኮችን ተጠቅመን የባንክ አካውንት መክፈት/ሚስጥራዊ መረጃዎችን መላላክ ከፍተኛ አደጋ አለው።
-አጠራጣሪ ሊንኮችን መክፈት፦ "ሎተሪ ደርሶዎታል"፣ ወይም "ነፃ የኢንተርኔት ጥቅል" በሚሉ አሳሳች መልዕክቶች ያሉ ሊንኮችን መጫን ስልካችንን ለጠላፊዎች አሳልፎ ይሰጣል።
-ቀላል የይለፍ ቃላትን መጠቀም፦ እንደ "1234"፣ "0000" ወይም የልደት ቀንን የመሳሰሉ በቀላሉ የሚገመቱ የይለፍ ቃላትን መጠቀም ስልካችን በእጃችን ቢሆን እንኳ በሩቅ ሆኖ ለመገመት ለሚሞክር የመረጃ መንታፊ ስራውን ያቀልለታል። #INSA
@ThiqahETH
❤12👏4🙏3😢1
የቦትስዋና ወጣቶች ለዩክሬን ጦርነት እየተመለመሉ እንደሚላኩ ተገለጸ።
ብዛት ያላቸው የሀገሪቱ ወጣቶች በስራ ቅጥር እና በስልጠና ሰበብ ወደ ሩሲያ መላካቸው በምርመራ ተረጋግጧል።
የቦትስዋና መንግስት ወጣቶችን እየመለመሉ በሚልኩ ኤጄንሲዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
ዜጎች ከሀሰተኛ መረጃ እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መንግስት፣ የስራ አጥነት ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰራ ገልጿል። #outlook
@ThiqahETH
ብዛት ያላቸው የሀገሪቱ ወጣቶች በስራ ቅጥር እና በስልጠና ሰበብ ወደ ሩሲያ መላካቸው በምርመራ ተረጋግጧል።
የቦትስዋና መንግስት ወጣቶችን እየመለመሉ በሚልኩ ኤጄንሲዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
ዜጎች ከሀሰተኛ መረጃ እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መንግስት፣ የስራ አጥነት ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰራ ገልጿል። #outlook
@ThiqahETH
❤2🤔2😱1
ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ የተጣለባቸው ሀገራት ብዛት 39 ደረሰ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ20 ሀገራት ላይ የጣሉትን የጉዞ እገዳ አራዝመዋል።
ከሀገራቱ በተጨማሪ የፍልስጤም ባለስልጣናትም የጉዞ ክልከላው እንደሚመለከታቸው ተናግረዋል።
የትራምፕ አስተዳደር ሌሎች አምስት ሀገራትን ሙሉ በሙሉ ያገደ ሲሆን ተጨማሪ 15 ሀገራት ከፊል እገዳ እንደተጣለባቸው ተገልጿል።
በዚሁ ውሳኔ መሰረት ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ የተጣለባቸው ሀገራት ጠቅላላ ብዛት 39 ደርሷል።
ሙሉ በሙሉ ከታገዱት ውስጥ ኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ የመን፣ ኢራ፣ ማይናማር ይገኙበታል።
አዲስ ሙሉ እገዳ የተጣለባቸው አምስት ሀገራት ደግሞ ሶርያ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ማሊ እና ኒጀር ናቸው።
ከፊል እገዳ ከተጣለባቸው 15 ሀገራት ውስጥ ደግሞ አንጎላ፣ ቤኒን እና ሴኔጋል ተካተዋል። #euronews
@ThiqahEth
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ20 ሀገራት ላይ የጣሉትን የጉዞ እገዳ አራዝመዋል።
ከሀገራቱ በተጨማሪ የፍልስጤም ባለስልጣናትም የጉዞ ክልከላው እንደሚመለከታቸው ተናግረዋል።
የትራምፕ አስተዳደር ሌሎች አምስት ሀገራትን ሙሉ በሙሉ ያገደ ሲሆን ተጨማሪ 15 ሀገራት ከፊል እገዳ እንደተጣለባቸው ተገልጿል።
በዚሁ ውሳኔ መሰረት ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ የተጣለባቸው ሀገራት ጠቅላላ ብዛት 39 ደርሷል።
ሙሉ በሙሉ ከታገዱት ውስጥ ኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ የመን፣ ኢራ፣ ማይናማር ይገኙበታል።
አዲስ ሙሉ እገዳ የተጣለባቸው አምስት ሀገራት ደግሞ ሶርያ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ማሊ እና ኒጀር ናቸው።
ከፊል እገዳ ከተጣለባቸው 15 ሀገራት ውስጥ ደግሞ አንጎላ፣ ቤኒን እና ሴኔጋል ተካተዋል። #euronews
@ThiqahEth
❤11😢1😡1
በሱዳን ከ100 የሚበልጡ ንጹሐን በድሮን ጥቃት ተገደሉ።
በኮርዶፋ ግዛት የተፈጸመው ይህ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን አፈናቅሏል።
የሀገሪቱ ጦር ለተፈፀመው የድሮን ጥቃት የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ተጠያቂ ቢያደርግም፣ አማፂ ሀይሉ የሰጠው ምላሽ እንደሌለ ተገልጿል።
ጥቃቱ በህፃናት ትምህርትቤት እና በሆስፒታል ላይ በመከሰቱ የአደጋው መጠን ከፍተኛ ሊሆን ችሏል ተብሏል። #aljazeera
@ThiqahETH
በኮርዶፋ ግዛት የተፈጸመው ይህ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን አፈናቅሏል።
የሀገሪቱ ጦር ለተፈፀመው የድሮን ጥቃት የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ተጠያቂ ቢያደርግም፣ አማፂ ሀይሉ የሰጠው ምላሽ እንደሌለ ተገልጿል።
ጥቃቱ በህፃናት ትምህርትቤት እና በሆስፒታል ላይ በመከሰቱ የአደጋው መጠን ከፍተኛ ሊሆን ችሏል ተብሏል። #aljazeera
@ThiqahETH
😭18🕊2❤1🤔1
የአሜሪካ ሴኔት ለ2026 የመከላከያ በጀት 901 ቢሊየን ዶላር አፀደቀ።
ሴኔቱ በአሜሪካ ታሪክ ከፍተኛ የተባለውን የመከላከያ በጀት አፅድቋል።
ከበጀቱ ውስጥ 4 በመቶው ለዩክሬን የሚሰጥ ድጋፍ ነው። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አዋጁን በፊርማቸው ህግ አድርገው ያፀድቁታል ተብሏል። #samaatv
@ThiqahETH
ሴኔቱ በአሜሪካ ታሪክ ከፍተኛ የተባለውን የመከላከያ በጀት አፅድቋል።
ከበጀቱ ውስጥ 4 በመቶው ለዩክሬን የሚሰጥ ድጋፍ ነው። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አዋጁን በፊርማቸው ህግ አድርገው ያፀድቁታል ተብሏል። #samaatv
@ThiqahETH
❤9😡8🤔3👏2
"እስራኤል በታሪኳ ትልቁን የነዳጅ ሽያጭ ስምምነት ፈጽማለች" - ኔታንያሁ
እስራኤል እና ኢራን የ35 ቢሊየን ዶላር የተፈጥሮ ጋዝ ስምምነት ማድረጋቸው ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ "ለግብጽ የጋዝ አቅርቦት ለማሟላት ስምምነት ላይ ተደርሷል" ብለዋል።
"እስራኤል በታሪኳ ትልቁን የነዳጅ ሽያጭ ስምምነት ፈፅማለች" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የቀጠናው የሀይል ምንጭ በመሆን ለቀጠናው መረጋጋት የበኩላችንን ሚና እንጫወታለን" ሲሉ ገልጸዋል።
"እስራኤል እስከ 2040 የነዳጅ አቅርቦቱን ለማሟላት ዝግጁ መሆኗን ለመግለጽ እወዳለሁ" ብለዋል ኔታንያሁ።
የተፈጥሮ ነዳጁ 600 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ያመነጫል ተብሎ ከሚጠበቀው የሌቪያታን የነዳጅ ማመንጫ እንደሚቀርብ ተናግረዋል።
እስራኤል እና ግብፅ ባሳለፍነው ነሐሴ ተመሳሳይ የኢንቨስትመንት ስምምነት ቢፈራረሙም በጋዛው ጦርነት ሳቢያ በሳምንታት ውስጥ ፈርሷል ተብሏል። #theindependent
@ThiqahETH
እስራኤል እና ኢራን የ35 ቢሊየን ዶላር የተፈጥሮ ጋዝ ስምምነት ማድረጋቸው ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ "ለግብጽ የጋዝ አቅርቦት ለማሟላት ስምምነት ላይ ተደርሷል" ብለዋል።
"እስራኤል በታሪኳ ትልቁን የነዳጅ ሽያጭ ስምምነት ፈፅማለች" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የቀጠናው የሀይል ምንጭ በመሆን ለቀጠናው መረጋጋት የበኩላችንን ሚና እንጫወታለን" ሲሉ ገልጸዋል።
"እስራኤል እስከ 2040 የነዳጅ አቅርቦቱን ለማሟላት ዝግጁ መሆኗን ለመግለጽ እወዳለሁ" ብለዋል ኔታንያሁ።
የተፈጥሮ ነዳጁ 600 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ያመነጫል ተብሎ ከሚጠበቀው የሌቪያታን የነዳጅ ማመንጫ እንደሚቀርብ ተናግረዋል።
እስራኤል እና ግብፅ ባሳለፍነው ነሐሴ ተመሳሳይ የኢንቨስትመንት ስምምነት ቢፈራረሙም በጋዛው ጦርነት ሳቢያ በሳምንታት ውስጥ ፈርሷል ተብሏል። #theindependent
@ThiqahETH
🤔44❤11😢3🕊3😡3😱1
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቬኔዙዌላን የነዳጅ ታንከሮች ላይ እገዳ ጣሉ።
ፕሬዝዳንቱ እገዳውን አስመለክቶ በትሩዝ ሶሻል ገፃቸው ላይ "ቬንዙዌላ እስከዛሬ በደቡብ አሜሪካ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ጦር ተከባለች" ሲሉ አስፍረዋል።
ፕሬዚዳንቱ "ሁሉንም ነዳጅ፣ መሬት እና ካሁን በፊት ከእኛ የሰረቋቸውን ሁሉንም ንብረቶች ለዩናይትድስቴትስ ካልመለሱ ከዚህም በላይ አይተውትይጨመራል፣ በማያውቁት ሁኔታ ይደነግጣሉ" በማለት ገልጸዋል።
አክለው "ህጋዊ ያልሆነው የማዱሮ መንግስት ከተሰረቁ ጣቢያዎች የመነጩ ነዳጆችን እየተጠቀመ ራሳቸውን፣ የእፅ አሸባሪዎችን፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን፣ ግድያ እና እገታን እየደገፈበት ነው" ብለዋል።
"የእኛን ንብረት በመዝረፍና በሽብር፣ በአደንዛዥ እፅ ዝውውር፣ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና በሌሎችም ወንጀሎች የቬኔዙዌላ መንግስት በውጭ የአሸባሪ ድርጅቶች ውስጥ ተካቷል" ሲሉ አስታውቀዋል።
ዶናልድ ትራምፕ በዚሁ አስተያየታቸው "በመሆኑም ዛሬ ሁሉም ከቬንዙዌላ የሚገቡ እና የሚወጡ የነዳጅ ታንከሮች እንድቆሙ እና ሙሉ ማዕቀብ እንድጣልባቸው አዝዣለሁ" ነው ያሉት።
"ወንጀለኛው የማዱሮ አገዛዝ በደካማው የባይደን አስተዳደር ዘመን ወደአሜሪካ የላካቸው በፍጥነት ወደ ቬንዙዌላ እየተመለሱ ነው" በማለት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ መቋረጡን አስረድተዋል።
"አሜሪካ ወንጀለኞችን፣ አሸባሪዎችን ወይም ሌሎች ሀገራትን ለዘረፋ፣ ለስጋት እና ለየትኛውም ጥፋት አትፈቅድም" ያሉት ትራምፕ "በተመሳሳይ መልኩ ጥፋተኛ አገዛዝ ነዳጃችንን፣ መሬታችንን እና ሌሎች ሀብታችንን እንዲወስድብን አንፈቅድም፣ ሁሉም ወደአሜሪካ መመለስ አለባቸው" ሲሉ ገልጸዋል።
@ThiqahETH
ፕሬዝዳንቱ እገዳውን አስመለክቶ በትሩዝ ሶሻል ገፃቸው ላይ "ቬንዙዌላ እስከዛሬ በደቡብ አሜሪካ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ጦር ተከባለች" ሲሉ አስፍረዋል።
ፕሬዚዳንቱ "ሁሉንም ነዳጅ፣ መሬት እና ካሁን በፊት ከእኛ የሰረቋቸውን ሁሉንም ንብረቶች ለዩናይትድስቴትስ ካልመለሱ ከዚህም በላይ አይተውትይጨመራል፣ በማያውቁት ሁኔታ ይደነግጣሉ" በማለት ገልጸዋል።
አክለው "ህጋዊ ያልሆነው የማዱሮ መንግስት ከተሰረቁ ጣቢያዎች የመነጩ ነዳጆችን እየተጠቀመ ራሳቸውን፣ የእፅ አሸባሪዎችን፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን፣ ግድያ እና እገታን እየደገፈበት ነው" ብለዋል።
"የእኛን ንብረት በመዝረፍና በሽብር፣ በአደንዛዥ እፅ ዝውውር፣ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና በሌሎችም ወንጀሎች የቬኔዙዌላ መንግስት በውጭ የአሸባሪ ድርጅቶች ውስጥ ተካቷል" ሲሉ አስታውቀዋል።
ዶናልድ ትራምፕ በዚሁ አስተያየታቸው "በመሆኑም ዛሬ ሁሉም ከቬንዙዌላ የሚገቡ እና የሚወጡ የነዳጅ ታንከሮች እንድቆሙ እና ሙሉ ማዕቀብ እንድጣልባቸው አዝዣለሁ" ነው ያሉት።
"ወንጀለኛው የማዱሮ አገዛዝ በደካማው የባይደን አስተዳደር ዘመን ወደአሜሪካ የላካቸው በፍጥነት ወደ ቬንዙዌላ እየተመለሱ ነው" በማለት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ መቋረጡን አስረድተዋል።
"አሜሪካ ወንጀለኞችን፣ አሸባሪዎችን ወይም ሌሎች ሀገራትን ለዘረፋ፣ ለስጋት እና ለየትኛውም ጥፋት አትፈቅድም" ያሉት ትራምፕ "በተመሳሳይ መልኩ ጥፋተኛ አገዛዝ ነዳጃችንን፣ መሬታችንን እና ሌሎች ሀብታችንን እንዲወስድብን አንፈቅድም፣ ሁሉም ወደአሜሪካ መመለስ አለባቸው" ሲሉ ገልጸዋል።
@ThiqahETH
😡13❤6🤔4
የቤልጅየም አርሶአደሮች የአውሮፓ ህብረት የፈጸመውን ስምምነት ተቃወሙ።
የአውሮፓ ህብረት ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር " የግብርና ምርት ስምምነት(EU Mercosur)" ፈጽሟል።
በቤልጅየም ዋና ከተማ ብራሰልስ የተሰባሰቡት አርሶአደሮቹ ስምምነቱን "ኢፍትሃዊ ውድድርን ይፈጥራል፣ የአውሮፓ ግብርናን ይጎዳል" ሲሉ ተቃውመዋል።
አርሶአደሮቹ የእርሻ ትራክተሮችን ይዘው በመውጣት ወደ ብራሰልስ የሚወስደውን መንገድ ዘግተውታል።
የአውሮፓ አርሶአደሮች ፌደሬሽን 10,000 ተቃዋሚዎች መሳተፋቸውን አስታውቋል። #aa
@ThiqahETH
የአውሮፓ ህብረት ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር " የግብርና ምርት ስምምነት(EU Mercosur)" ፈጽሟል።
በቤልጅየም ዋና ከተማ ብራሰልስ የተሰባሰቡት አርሶአደሮቹ ስምምነቱን "ኢፍትሃዊ ውድድርን ይፈጥራል፣ የአውሮፓ ግብርናን ይጎዳል" ሲሉ ተቃውመዋል።
አርሶአደሮቹ የእርሻ ትራክተሮችን ይዘው በመውጣት ወደ ብራሰልስ የሚወስደውን መንገድ ዘግተውታል።
የአውሮፓ አርሶአደሮች ፌደሬሽን 10,000 ተቃዋሚዎች መሳተፋቸውን አስታውቋል። #aa
@ThiqahETH
❤7👏5😱2🕊1
THIQAH
የቤልጅየም አርሶአደሮች የአውሮፓ ህብረት የፈጸመውን ስምምነት ተቃወሙ። የአውሮፓ ህብረት ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር " የግብርና ምርት ስምምነት(EU Mercosur)" ፈጽሟል። በቤልጅየም ዋና ከተማ ብራሰልስ የተሰባሰቡት አርሶአደሮቹ ስምምነቱን "ኢፍትሃዊ ውድድርን ይፈጥራል፣ የአውሮፓ ግብርናን ይጎዳል" ሲሉ ተቃውመዋል። አርሶአደሮቹ የእርሻ ትራክተሮችን ይዘው በመውጣት ወደ ብራሰልስ የሚወስደውን መንገድ…
የአውሮፓ ሀገራት በአርሶአደሮች ተቃውሞ ስለገጠመው የግብርና ምርት ስምምነት (EU Mercousur) ምን ምላሽ ሰጡ?
የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን "የአውሮፓ ህብረት በአባል ሀገራቱ አርሶአደሮች ጥቅም ላይ መደራደር የለበትም" ሲሉ ተናግረዋል።
ጣሊያን በበኩሏ የስምምነቱ ፊርማ "የአርሶአደሮችን ደህንነት የሚያስጠብቁ አስተማማኝ ሁኔታዎች" እስኪሟሉ ድረስ እንዲዘገይ ጠይቃለች ተብሏል።
ጀርመን እና ስፔን "የአውሮፓን የወጪ ገበያ ያሳድገዋል" በማለት የስምምነቱ ደጋፊዎች መሆናቸው ተገልጿል።
ይሁን እንጂ አርሶአደሮች አሁንም በአውሮፓ ፓርላማ አጠገብ በመገኘት ድንች እና ቲማቲም መንገድ ላይ በመጣል፣ እንጨት በማቃጠል፣ 150 የእርሻ ትራክተሮችን በማጓጓዝ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ይገኛሉ ተብሏል። #anadoluagency
@ThiqahETH
የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን "የአውሮፓ ህብረት በአባል ሀገራቱ አርሶአደሮች ጥቅም ላይ መደራደር የለበትም" ሲሉ ተናግረዋል።
ጣሊያን በበኩሏ የስምምነቱ ፊርማ "የአርሶአደሮችን ደህንነት የሚያስጠብቁ አስተማማኝ ሁኔታዎች" እስኪሟሉ ድረስ እንዲዘገይ ጠይቃለች ተብሏል።
ጀርመን እና ስፔን "የአውሮፓን የወጪ ገበያ ያሳድገዋል" በማለት የስምምነቱ ደጋፊዎች መሆናቸው ተገልጿል።
ይሁን እንጂ አርሶአደሮች አሁንም በአውሮፓ ፓርላማ አጠገብ በመገኘት ድንች እና ቲማቲም መንገድ ላይ በመጣል፣ እንጨት በማቃጠል፣ 150 የእርሻ ትራክተሮችን በማጓጓዝ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ይገኛሉ ተብሏል። #anadoluagency
@ThiqahETH
🤔4❤2😭1
"ከ200 የሚበልጡ የህክምና ባለሙያዎች ተገድለዋል። 507 ባለሙያዎች ሲቆስሉ፣ 59 ጠፍተዋል" - ሪፖርት
በሱዳን ከ2023 ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የህክምና ባለሙያዎች ህይወት ማለፉን የሱዳን ዶክተሮች ጥምረት (SDN) ገልጿል።
ጥምረቱ ባወጣው ሪፖርት "ከ2023 ጀምሮ ቢያንስ 234 የህክምና ባለሙያዎች ተገድለዋል፣ 73 የሚደርሱት ዳርፉር ውስጥ በአር ኤስ ኤፍ ታግተዋል" ብሏል።
ሪፖርቱ አክሎ፣ "507 ባለሙያዎች ሲቆስሉ፣ 59ኙ ጠፍተዋል" ነው ያለው።
ጥምረቱ ባወጣው ሪፖርት አለማቀፍ ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ ድርጅቶች የህክምና ባለሙያዎች ደህንነት እንድጠብቅ ጫና እንዲፈጥሩ ጠይቋል።
በጦርነት ውስጥ የሚገኙ ሀይሎች ግጭቱን እንዲያቆሙ ያሳሰበው ቡድኑ፣ የታገቱት እንዲለቀቁ እና የጠፉት መዳረሻቸው እንዲታወቅ አሳስቧል። #aa
@ThiqahETH
በሱዳን ከ2023 ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የህክምና ባለሙያዎች ህይወት ማለፉን የሱዳን ዶክተሮች ጥምረት (SDN) ገልጿል።
ጥምረቱ ባወጣው ሪፖርት "ከ2023 ጀምሮ ቢያንስ 234 የህክምና ባለሙያዎች ተገድለዋል፣ 73 የሚደርሱት ዳርፉር ውስጥ በአር ኤስ ኤፍ ታግተዋል" ብሏል።
ሪፖርቱ አክሎ፣ "507 ባለሙያዎች ሲቆስሉ፣ 59ኙ ጠፍተዋል" ነው ያለው።
ጥምረቱ ባወጣው ሪፖርት አለማቀፍ ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ ድርጅቶች የህክምና ባለሙያዎች ደህንነት እንድጠብቅ ጫና እንዲፈጥሩ ጠይቋል።
በጦርነት ውስጥ የሚገኙ ሀይሎች ግጭቱን እንዲያቆሙ ያሳሰበው ቡድኑ፣ የታገቱት እንዲለቀቁ እና የጠፉት መዳረሻቸው እንዲታወቅ አሳስቧል። #aa
@ThiqahETH
💔8😭7❤2😱1🕊1
በባንግላዴሽ የወጣቶች ንቅናቄ መሪ መገደሉ ከፍተኛ ህዝባዊ አመፅ ተቀሰቀሰ።
ምርጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ የምትገኘው ባንግላዴሽ ለምርጫ ዕጩ ሁኖ የቀረበው የተማሪዎች ንቅናቄ አስተባባሪ ሻሪፍ ኡስማን ሀዲ ተገድሏል።
የ32 አመቱ ሀዲ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሀሲናን ከስልጣን ባነሳው የተማሪዎች ንቅናቄ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ተብሏል።
ሀዲ በዋና ከተማዋ ዳካ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ለህክምና ወደ ሲንጋፖር ቢያቀናም ከስድስት ቀን በኋላ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
በአስተባባሪው ህልፈት የተበሳጩት ሰልፈኞች ስሙን በመጥራት ተቃውሟቸውን እያሰሙ ሲሆን በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው ተብሏል። #keralanews
@ThiqahETH
ምርጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ የምትገኘው ባንግላዴሽ ለምርጫ ዕጩ ሁኖ የቀረበው የተማሪዎች ንቅናቄ አስተባባሪ ሻሪፍ ኡስማን ሀዲ ተገድሏል።
የ32 አመቱ ሀዲ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሀሲናን ከስልጣን ባነሳው የተማሪዎች ንቅናቄ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ተብሏል።
ሀዲ በዋና ከተማዋ ዳካ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ለህክምና ወደ ሲንጋፖር ቢያቀናም ከስድስት ቀን በኋላ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
በአስተባባሪው ህልፈት የተበሳጩት ሰልፈኞች ስሙን በመጥራት ተቃውሟቸውን እያሰሙ ሲሆን በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው ተብሏል። #keralanews
@ThiqahETH
🙏5🤔3❤2💔1
የአውሮፓ መሪዎች ለዩክሬን 90 ቢሊዮን ዩሮ ለማበደር መስማማታቸው ተገለጸ።
ከወለድ ነፃ ነው የተባለው ብድሩ ለቀጣዮቹ ሁለት አመታት የሀገሪቱን የጦር እና የገንዘብ ፍላጐትን ለማሟላት ያግዛል ተብሏል።
ይሁን እንጂ መሪዎቹ የታገደውን የሩሲያ ሀብት ለዩክሬን መልሶ ግንባታ እንዲውል መወሰን ላይ አልተስማሙም።
210 ቢሊዮን ዩሮ የሚገመት የሩሲያ ሀብት በጦርነቱ ምክንያት እንደያተዘ ህብረቱ አስታውቋል። #abcnews
@ThiqahETH
ከወለድ ነፃ ነው የተባለው ብድሩ ለቀጣዮቹ ሁለት አመታት የሀገሪቱን የጦር እና የገንዘብ ፍላጐትን ለማሟላት ያግዛል ተብሏል።
ይሁን እንጂ መሪዎቹ የታገደውን የሩሲያ ሀብት ለዩክሬን መልሶ ግንባታ እንዲውል መወሰን ላይ አልተስማሙም።
210 ቢሊዮን ዩሮ የሚገመት የሩሲያ ሀብት በጦርነቱ ምክንያት እንደያተዘ ህብረቱ አስታውቋል። #abcnews
@ThiqahETH
😡10❤4🙏4😱2🕊2🤔1
9 ዓመት?
የ8 ዓመት ህፃን የደፈረው ግለሰብ በ9 ዓመት እስራት መቀጣቱን የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳውቋል።
መህዲ መሀመድ ሳዲቅ የተባለ ግለሰብ በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ አለዋብ በተባለ ስፍራ በቀን 19/02/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ የ8 ዓመት ህፃን ከመንገድ ላይ እጇን ይዞ ወደራሱ ሱቅ ይዞ በመግባት አስገድዶ ደፍሯል።
ጉዳዩ በህግ ታይቶ፣ ፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት በተከሰሰበት ወንጀል ፈጻሚው በዘጠኝ ዓመት እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
መረጃው የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ሲሆን፣ በርካቶችም፣ የ8 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ ለደፈረው ግለሰብ የ9 አመት እስራት ቅጣት "ሌሎቹን መሰል ወንጀል ፈጻሚዎችን በርቱ የሚያስብል እንጅ አስተማሪ አይደለም" በሚል እየወቀሱ ናቸው።
@ThiqahETH
የ8 ዓመት ህፃን የደፈረው ግለሰብ በ9 ዓመት እስራት መቀጣቱን የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳውቋል።
መህዲ መሀመድ ሳዲቅ የተባለ ግለሰብ በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ አለዋብ በተባለ ስፍራ በቀን 19/02/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ የ8 ዓመት ህፃን ከመንገድ ላይ እጇን ይዞ ወደራሱ ሱቅ ይዞ በመግባት አስገድዶ ደፍሯል።
ጉዳዩ በህግ ታይቶ፣ ፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት በተከሰሰበት ወንጀል ፈጻሚው በዘጠኝ ዓመት እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
መረጃው የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ሲሆን፣ በርካቶችም፣ የ8 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ ለደፈረው ግለሰብ የ9 አመት እስራት ቅጣት "ሌሎቹን መሰል ወንጀል ፈጻሚዎችን በርቱ የሚያስብል እንጅ አስተማሪ አይደለም" በሚል እየወቀሱ ናቸው።
@ThiqahETH
😡56😭8❤3👏2😱2
THIQAH
"ወደፊት በመጥፎ መንገድ ካልሄደ፣ ቲክቶክ አሁን ላይ ጥሩ ቅርጽ ይዟል" - የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለቲክቶክ ተጨማሪ 90 ቀናት ፈቀዱ። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቲክ ቶክ የተሰኘው የተንቀሳቃሽ ምስል መተግበሪያ "ብሔራዊ ደህንነት ስጋት" ነው በሚል የባይደን አስተዳደር ካገደው በኋላ በ24 ሰዓት ውስጥ በመሻር ወደ አገልግሎት መልሰውታል። "ወደፊት በመጥፎ መንገድ ካልሄደ፣ ቲክቶክ አሁን ላይ…
ቲክቶክ በአሜሪካ ለሽያጭ ለመቅረብ ዝግጁ መሆኑ ተገለጸ።
የቲክቶክ ባለቤት በሆነው የባይትዳንስ ኩባንያና ግዥ በሚፈጸሙት የአሜሪካ ኩባንያዎች አማካኝነት የስምምነት ፊርማ ተፈጽሟል።
በስምምነቱ መሰረት የቲክ ቶክ 50 በመቶ ድርሻ ለአሜሪካ ባለሀብቶች እንደሚሸጥ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በባይደን ተዘግቶ የነበረውን ቲክ ቶክ ከመለሱ በኋላ የአሜሪካ ድርሻ ሊኖረው ይገባል በሚል ለ90 ቀናት ለሶስት ዙር ተራዝሟል።
ባይትዳንስ በበኩሉ በአሜሪካ 170 ሚሊየን በላይ ተከታይ ያለውን የቲክቶክን ድርሻ አልሸጥም ሲል ቢቆይም በመጨረሻ ከስምምነት ላይ ተደርሷል። #techcrunch #cnn
@ThiqahETH
የቲክቶክ ባለቤት በሆነው የባይትዳንስ ኩባንያና ግዥ በሚፈጸሙት የአሜሪካ ኩባንያዎች አማካኝነት የስምምነት ፊርማ ተፈጽሟል።
በስምምነቱ መሰረት የቲክ ቶክ 50 በመቶ ድርሻ ለአሜሪካ ባለሀብቶች እንደሚሸጥ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በባይደን ተዘግቶ የነበረውን ቲክ ቶክ ከመለሱ በኋላ የአሜሪካ ድርሻ ሊኖረው ይገባል በሚል ለ90 ቀናት ለሶስት ዙር ተራዝሟል።
ባይትዳንስ በበኩሉ በአሜሪካ 170 ሚሊየን በላይ ተከታይ ያለውን የቲክቶክን ድርሻ አልሸጥም ሲል ቢቆይም በመጨረሻ ከስምምነት ላይ ተደርሷል። #techcrunch #cnn
@ThiqahETH
❤11😭4😢1🙏1
"የ35,600 ዶላር ብክነት ያደረሱት" የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትርና ባለቤታቸው የ17 አመት እስር ተፈረደባቸው።
በእስር ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ክሃን እና ባለቤታቸው ቡሽራ ቢቢ በስጦታ መልክ የተቀበሉት ወርቅና ጌጣጌጥ በሙስና ኬዝ ክስ እንዲመሰረትባቸው አድርጓቸዋል።
በአዲያላ እስር ቤት የሚገኙት ባለትዳሮቹ በተጠረጠሩበት ወንጀል የ35,600 ዶላር ብክነት ማድረሳቸውን ፍርድ ቤቱ በክስ ዝርዝሩ አስረድቷል።
ክሃን እና ቢቢ የተላለፈባቸውን ፍርድ "የተፈበረከ ክስ" ሲሉ ውድቅ ማድረጋቸውን ጠበቃዎቻቸው ተናግረዋል።
በ2023 ወደእስር የገቡት ክሃን ከ200 በላይ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን ሁሉንም "የፖለቲካ ሴራ" ሲሉ አጣጥለውታል። #trtworld
@ThiqahETH
በእስር ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ክሃን እና ባለቤታቸው ቡሽራ ቢቢ በስጦታ መልክ የተቀበሉት ወርቅና ጌጣጌጥ በሙስና ኬዝ ክስ እንዲመሰረትባቸው አድርጓቸዋል።
በአዲያላ እስር ቤት የሚገኙት ባለትዳሮቹ በተጠረጠሩበት ወንጀል የ35,600 ዶላር ብክነት ማድረሳቸውን ፍርድ ቤቱ በክስ ዝርዝሩ አስረድቷል።
ክሃን እና ቢቢ የተላለፈባቸውን ፍርድ "የተፈበረከ ክስ" ሲሉ ውድቅ ማድረጋቸውን ጠበቃዎቻቸው ተናግረዋል።
በ2023 ወደእስር የገቡት ክሃን ከ200 በላይ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን ሁሉንም "የፖለቲካ ሴራ" ሲሉ አጣጥለውታል። #trtworld
@ThiqahETH
🤔8😢5❤4🕊1
በቻይና የህዝብ ቁጥር በ2 ሚሊየን መቀነሱ ተገለጸ።
የፕሬዝዳንት ዢ ጂፒንግ መንግስት በ2026 በሀገሪቱ የውልደት መጠንን ለመጨር የሚያግዝ መመሪያ ያወጣል ተብሎ ይጠቃል።
ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር መቀነስ የገጠማት ቻይና፣ ከጥር 2025 ጀምሮ ለሚወለዱ ህፃናት 3600 ዩዋን ወይም የ500 ዶላር የወሊድ ማበረታቻ ስጦታ ማቅረብ ጀምራለች።
ህፃናት ሶስት አመት እስኪሞላቸው ድረስ የገንዘብ ድጎማው እንደማይቋረጥ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም በቅድመ መደበኛ ትምህርት ለህፃናት የሚከፈለው ገንዘብ የወላጆችን ጫና ለመቀነስ እንዲቀር ተወስኗል ተብሏል።
1.41 ቢሊየን ህዝብ ያላት ቻይና 1.46 ህዝብ ካላት ህንድ በመቀጠል በአለም ላይ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት ሀገር መሆኗን ስታስቲካዊ መረጃዎች ያመላክታሉ። #miamiherald
@ThiqahETH
የፕሬዝዳንት ዢ ጂፒንግ መንግስት በ2026 በሀገሪቱ የውልደት መጠንን ለመጨር የሚያግዝ መመሪያ ያወጣል ተብሎ ይጠቃል።
ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር መቀነስ የገጠማት ቻይና፣ ከጥር 2025 ጀምሮ ለሚወለዱ ህፃናት 3600 ዩዋን ወይም የ500 ዶላር የወሊድ ማበረታቻ ስጦታ ማቅረብ ጀምራለች።
ህፃናት ሶስት አመት እስኪሞላቸው ድረስ የገንዘብ ድጎማው እንደማይቋረጥ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም በቅድመ መደበኛ ትምህርት ለህፃናት የሚከፈለው ገንዘብ የወላጆችን ጫና ለመቀነስ እንዲቀር ተወስኗል ተብሏል።
1.41 ቢሊየን ህዝብ ያላት ቻይና 1.46 ህዝብ ካላት ህንድ በመቀጠል በአለም ላይ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት ሀገር መሆኗን ስታስቲካዊ መረጃዎች ያመላክታሉ። #miamiherald
@ThiqahETH
❤10🙏3👏1
"ከ70 በሚበልጡ ISIS ወታደራዊ ስፍራዎች ላይ ኢላማ አድርገናል" - ዩናይትድስቴትስ
አሜሪካ በሶሪያ የአይ ኤስ አይ ኤስ ምሽጎች ላይ ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈጸሟን አስታወቀች።
የአሜሪካ ጦር አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር "ከ70 በሚበልጡ የቡድኑ ወታደራዊ ስፍራዎች ላይ ኢላማ አድርገናል" ነው ያሉት።
ኩፐር "በቀጠናው የሚገኙ አጋሮቻችንን እና የአሜሪካ ወታደሮችን በሚያጠቁ አሸባሪዎች ላይ እርምጃ መውሰዳችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።
የአሜሪካ መከላከያ ቢሮ ዋና ፀሐፊ ፔት ሄጌት፣ "የተወሰደው እርምጃ ISIS የሚጠቀምባቸው መሰረተ ልማቶች እና የጦር መሳሪያዎችን ከጥቅም ውጭ አድርጓል" ሲሉ ገልጸዋል።
"ጠላቶቻችንን ገድለናል፣ ማርከናል ወደፊትም ይቀጥላል" ብለዋል ሄጌት።
ISIS ባለፈው ሳምንት በሶሪያ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ባደረሰው ጥቃት ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች ህይወታቸው ሲያልፍ ስድስቱ ቆስለዋል። #ashraqalawusat
@ThiqahETH
አሜሪካ በሶሪያ የአይ ኤስ አይ ኤስ ምሽጎች ላይ ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈጸሟን አስታወቀች።
የአሜሪካ ጦር አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር "ከ70 በሚበልጡ የቡድኑ ወታደራዊ ስፍራዎች ላይ ኢላማ አድርገናል" ነው ያሉት።
ኩፐር "በቀጠናው የሚገኙ አጋሮቻችንን እና የአሜሪካ ወታደሮችን በሚያጠቁ አሸባሪዎች ላይ እርምጃ መውሰዳችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።
የአሜሪካ መከላከያ ቢሮ ዋና ፀሐፊ ፔት ሄጌት፣ "የተወሰደው እርምጃ ISIS የሚጠቀምባቸው መሰረተ ልማቶች እና የጦር መሳሪያዎችን ከጥቅም ውጭ አድርጓል" ሲሉ ገልጸዋል።
"ጠላቶቻችንን ገድለናል፣ ማርከናል ወደፊትም ይቀጥላል" ብለዋል ሄጌት።
ISIS ባለፈው ሳምንት በሶሪያ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ባደረሰው ጥቃት ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች ህይወታቸው ሲያልፍ ስድስቱ ቆስለዋል። #ashraqalawusat
@ThiqahETH
❤13👏5🤔1🕊1
THIQAH
የአውሮፓ ሀገራት በአርሶአደሮች ተቃውሞ ስለገጠመው የግብርና ምርት ስምምነት (EU Mercousur) ምን ምላሽ ሰጡ? የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን "የአውሮፓ ህብረት በአባል ሀገራቱ አርሶአደሮች ጥቅም ላይ መደራደር የለበትም" ሲሉ ተናግረዋል። ጣሊያን በበኩሏ የስምምነቱ ፊርማ "የአርሶአደሮችን ደህንነት የሚያስጠብቁ አስተማማኝ ሁኔታዎች" እስኪሟሉ ድረስ እንዲዘገይ ጠይቃለች ተብሏል። ጀርመን…
የአውሮፓ ህብረት አወዛጋቢውን ስምምነት እስከ ጥር ወር ማራዘሙን ገለጸ።
የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኦርሱላ ቮንደርሊን የአውሮፓ ህብረት ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር የፈጸመውን የግብርና ስምምነት (EU Mercosur) ለቀጣዩ ወር መራዘሙን ገልጸዋል።
ቮንደርሊን ስምምነቱን ለማፅደቅ ለነገ እሁድ ቀጠሮ ቢያዝም፣ አርሶ አደሮች ባሰሙት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ መለወጡን ተናግረዋል። #euractiv
@ThiqahETH
የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኦርሱላ ቮንደርሊን የአውሮፓ ህብረት ከደቡብ አሜሪካ ሀገራት ጋር የፈጸመውን የግብርና ስምምነት (EU Mercosur) ለቀጣዩ ወር መራዘሙን ገልጸዋል።
ቮንደርሊን ስምምነቱን ለማፅደቅ ለነገ እሁድ ቀጠሮ ቢያዝም፣ አርሶ አደሮች ባሰሙት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ መለወጡን ተናግረዋል። #euractiv
@ThiqahETH
❤4👏2😱1🕊1