ተመድ በአልሸባብ ላይ የጣለውን ማዕቀብ አራዘመ
የተመድ የፀጥታው ምክርቤት በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው "የአልሸባብ አሸባሪ ቡድን" ላይ የተጣለበትን ማዕቀብ ገምግሟል።
ሁሉም 15ቱ አባላት የምክር ቤቱ አባላት የድጋፍ ድምፅ ሰጥተዋል።
አልሸባብ የሶማሊያን መንግስት ለመጣል ላለፉት 16 አመታት ሲታገል ቆይቷል።
ከ2024 ጀምሮ በቡድኑ ላይ ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን እንደፈፀመ የገለጸው የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር፣ 220 ጥቃቶችን አድርሶ 868 የሚሊሺያ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። #aa
@ThiqahETH
የተመድ የፀጥታው ምክርቤት በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው "የአልሸባብ አሸባሪ ቡድን" ላይ የተጣለበትን ማዕቀብ ገምግሟል።
ሁሉም 15ቱ አባላት የምክር ቤቱ አባላት የድጋፍ ድምፅ ሰጥተዋል።
አልሸባብ የሶማሊያን መንግስት ለመጣል ላለፉት 16 አመታት ሲታገል ቆይቷል።
ከ2024 ጀምሮ በቡድኑ ላይ ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን እንደፈፀመ የገለጸው የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር፣ 220 ጥቃቶችን አድርሶ 868 የሚሊሺያ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። #aa
@ThiqahETH
❤6👏1
አማራ ባንክ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 35.8 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገለጸ
ባንኩ በተያያዘው 2018 በጀት ዓመት በ5 ወራት ብቻ ከ 3.55 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገቡን አስታውቋል።
የባንኩ አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን እስከ ህዳር 2018 35.8 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ እድገቱም 82 በመቶ መሆኑንም አስረድቷል።
ካፒታል ጋዜጣ ደረሰኝ ባለው መረጃ መሰረት፤ ባንኩ ከታክስ በፊት 1.15 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዝግቧል። 591,884 አዳዲስ የደንበኞችን ሒሳብ በመክፈት አጠቃላይ የደንበኞችን ቁጥር 2.68 ሚሊዮን አድርሷል።
የውጭ ምንዛሪ በማሰባሰብ ረገድ፤ 76.58 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ በመሰብሰብ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ313 በመቶ ብልጫ አለው የተባለ ሲሆን፣ ባንኩ ከተመሰረተ ጀምሮ ያቀረበው አጠቃላይ ብድርና የቅድሚያ ክፍያ ወደ 31.3 ቢሊዮን ብር በማሳደግ በ53.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። #Capital
@ThiqahETH
ባንኩ በተያያዘው 2018 በጀት ዓመት በ5 ወራት ብቻ ከ 3.55 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገቡን አስታውቋል።
የባንኩ አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን እስከ ህዳር 2018 35.8 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ እድገቱም 82 በመቶ መሆኑንም አስረድቷል።
ካፒታል ጋዜጣ ደረሰኝ ባለው መረጃ መሰረት፤ ባንኩ ከታክስ በፊት 1.15 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዝግቧል። 591,884 አዳዲስ የደንበኞችን ሒሳብ በመክፈት አጠቃላይ የደንበኞችን ቁጥር 2.68 ሚሊዮን አድርሷል።
የውጭ ምንዛሪ በማሰባሰብ ረገድ፤ 76.58 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ በመሰብሰብ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ313 በመቶ ብልጫ አለው የተባለ ሲሆን፣ ባንኩ ከተመሰረተ ጀምሮ ያቀረበው አጠቃላይ ብድርና የቅድሚያ ክፍያ ወደ 31.3 ቢሊዮን ብር በማሳደግ በ53.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። #Capital
@ThiqahETH
❤12🙏4🕊2😡1
ገዳ ባንክ የሀብት መጠኑን 10 ቢሊዮን ብር በላይ ማድረሱን ገለጸ
የባንኩ የባለአክስዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው ዛሬ የተካሄደ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ 2024/ 2025 የበጀት ዓመት የስራ ሪፖርቱን አቅርቧል።
በሪፖርቱም ላይ ባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠኑ 10.1 ቢልየን ብር መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ ይህም የእቅዱን 94 በመቶ ያሳካው ነው። ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃጸር 80.4 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየ በሪፖርቱ ተገልጿል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የባንኩ ስራ አስኪያጅ ሁሴን ሀሰን፣ አሁን ላይ ያለው የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ መጠን 7.1 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸዋል። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲወዳደር የ92.5 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አስረድተዋል።
ባንኩ በዲጂታል ባንኪንግ በበጀት ዓመቱ የ4.33 ቢልየን ብር ዝውውር ማድረጉን፣ በአሁኑ ወቅት የባንኩ አጠቃላይ ባለ አክሲዮኖችም 31 ሺህ 518 ማድረሱ ተገልጿል። #TiritaFm
@ThiqahETH
የባንኩ የባለአክስዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው ዛሬ የተካሄደ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ 2024/ 2025 የበጀት ዓመት የስራ ሪፖርቱን አቅርቧል።
በሪፖርቱም ላይ ባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠኑ 10.1 ቢልየን ብር መድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፣ ይህም የእቅዱን 94 በመቶ ያሳካው ነው። ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃጸር 80.4 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየ በሪፖርቱ ተገልጿል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የባንኩ ስራ አስኪያጅ ሁሴን ሀሰን፣ አሁን ላይ ያለው የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ መጠን 7.1 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸዋል። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲወዳደር የ92.5 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አስረድተዋል።
ባንኩ በዲጂታል ባንኪንግ በበጀት ዓመቱ የ4.33 ቢልየን ብር ዝውውር ማድረጉን፣ በአሁኑ ወቅት የባንኩ አጠቃላይ ባለ አክሲዮኖችም 31 ሺህ 518 ማድረሱ ተገልጿል። #TiritaFm
@ThiqahETH
❤7🤔3🙏1💔1😡1
ከ30 የሚበልጡ የየመን ወታደሮች በአማፂ ሀይሎች ተገደሉ።
ከሟቾቹ በተጨማሪ 45 ወታደሮች መቁሰላቸውን አለማቀፍ እውቅና የተሰጠው የሊቢያ መንግስት አስታውቋል።
የሀገሪቱ መንግስት ለደረሰው ጥቃት በሀይደራባት ከተማ የሚንቀሳቀሱትን የኤስ ቲ ሲ ታጣቂዎችን ተጠያቂ አድርጓል ተብሏል። #reuters
@ThiqahETH
ከሟቾቹ በተጨማሪ 45 ወታደሮች መቁሰላቸውን አለማቀፍ እውቅና የተሰጠው የሊቢያ መንግስት አስታውቋል።
የሀገሪቱ መንግስት ለደረሰው ጥቃት በሀይደራባት ከተማ የሚንቀሳቀሱትን የኤስ ቲ ሲ ታጣቂዎችን ተጠያቂ አድርጓል ተብሏል። #reuters
@ThiqahETH
💔6❤4😢3🙏1
THIQAH
ትራምፕ የተኩስ አቁም መደረጉን ቢገልጹም የታይላንድ እና ካምቦዲያ ጦርነት አለመቆሙ ተገለጸ። የካምቦዲያ መንግስት "ታይላንድ ተዋጊ ጄቶችን ጨምሮ ከባባድ የጦር መሳሪያዎችን ተጠቅማ ጥቃት እያደረሰች ነው" ብሏል። ታይላንድ በበኩሏ የካምቦዲያ ጦር "አለማቀፍ ህግን ጥሷል" በማለት የአፀፋ እርምጃ እየወሰደች እንደምትገኝ ተገልጿል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ትናንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ…
"በውይይታችን የሀይል እርምጃዎች እንዲቆሙና ንጹሐን ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች እንዲቀሩ አሳስቢያለሁ" - ማሌዥያ
ማሌዥያ ካምቦዲያ እና ታይላንድ የገቡበትን ጦርነት እንዲያቆሙ አሳሰበች።
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሑፍ ከሁለቱ ሀገራት መሪዎች ጋር የተናጠል የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "በውይይታችን የሀይል እርምጃዎች እንዲቆሙ እና በንጹሐን ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች እንዲቀሩ አሳስቢያለሁ" ብለዋል።
ኢብራሂም "በመጪው ማክሰኞ በሚካሄደው የእስያ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እልባት እንዲበጅለት በአጀንዳ መልክ ይነሳል" ሲሉ ጠቁመዋል።
አምስተኛ ቀኑን በያዘው የታይላንድ እና ካምቦዲያ ጦርነት ከሁለቱም ወገን የሟቾች ቁጥር 48 ሲደርስ ግማሽ ሚሊዮን ሰዎች ተፈናቅለዋል።
ማሌዥያ ከወራት በፊት የነበረውን የሁለቱን ሀገራት ግጭት በማስቆም በዋና ከተማዋ ላምፑር የሰላም ስምምነት እንዲፈጾም ማድረጓ ይታወሳል። #straightstimes
@ThiqahETH
ማሌዥያ ካምቦዲያ እና ታይላንድ የገቡበትን ጦርነት እንዲያቆሙ አሳሰበች።
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሑፍ ከሁለቱ ሀገራት መሪዎች ጋር የተናጠል የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "በውይይታችን የሀይል እርምጃዎች እንዲቆሙ እና በንጹሐን ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች እንዲቀሩ አሳስቢያለሁ" ብለዋል።
ኢብራሂም "በመጪው ማክሰኞ በሚካሄደው የእስያ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እልባት እንዲበጅለት በአጀንዳ መልክ ይነሳል" ሲሉ ጠቁመዋል።
አምስተኛ ቀኑን በያዘው የታይላንድ እና ካምቦዲያ ጦርነት ከሁለቱም ወገን የሟቾች ቁጥር 48 ሲደርስ ግማሽ ሚሊዮን ሰዎች ተፈናቅለዋል።
ማሌዥያ ከወራት በፊት የነበረውን የሁለቱን ሀገራት ግጭት በማስቆም በዋና ከተማዋ ላምፑር የሰላም ስምምነት እንዲፈጾም ማድረጓ ይታወሳል። #straightstimes
@ThiqahETH
❤8👏1😱1😢1
THIQAH
በምያንማር "መንግስት በፈጸመው ጥቃት" 30 ሰዎች ሲሞቱ፣ 70 የሚሆኑት ቆሰሉ። ምያንማርን የሚያስተዳድረው ወታደራዊ መንግስት (ጁንታ) የአማፂዎችን እንቅስቃሴ ለመግታት በራኪን ግዛት የአየር ጥቃት ፈጽሟል። መንግስት የፈጸመው የድሮን ጥቃት በማሩክ ሆስፒታል በማረፉ ንፁሃን ዜጎች መጎዳታቸው ተገልጿል። ሆስፒታሉ ባለ 300 አልጋ ሲሆን፣ በሁሉም አልጋዎች ህሙማን እንደሚገኙበት የሆስፒታሉ ሰራተኞች ተናግረዋል።…
"የሞቱት ንጹሐን አይደሉም፣ የአሸባሪው ቡድን አባላት እና ደጋፊዎች ናቸው" - መንግስት
የማይናማር መንግስት "ከ30 በላይ ንጹሐን" የቀጠፈውን ጥቃት አስተባብሏል።
የወቅቱ የማይናማር መንግስት በራኪን ግዛት በሚገኘው ሆስፒታል ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጦ፣ ነገር ግን "ጥቃቱ ንጹሐን ዜጎች ላይ ያነጣጠረ አልነበረም" ብሏል።
ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለው ወታደራዊ ጁንታ "የሞቱት ንጹሐን አይደሉም፣ የአሸባሪው ቡድን አባላት እና ደጋፊዎች ናቸው" ሲል የደረሰበትን ውንጀላ ውድቅ አድርጓል።
መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ "የራኪን ግዛት ከ2024 ጀምሮ በአርካን አማፂ ኃይሎች (AA) ቁጥጥር ስር ነው የሚገኘው፣ ሆስፒታሉን የሚገለገሉበትም የታጠቁ ሀይሎች ናቸው" ነው ያለው።
ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ በተፈጸመው የአየር ላይ ጥቃት 33 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ፣ 76 መቁሰላቸውና 27 የሚሆኑት በጽኑ ህክምና ክፍል እንደሚገኙ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ተናግረዋል። #anadoluagency
@ThiqahETH
የማይናማር መንግስት "ከ30 በላይ ንጹሐን" የቀጠፈውን ጥቃት አስተባብሏል።
የወቅቱ የማይናማር መንግስት በራኪን ግዛት በሚገኘው ሆስፒታል ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጦ፣ ነገር ግን "ጥቃቱ ንጹሐን ዜጎች ላይ ያነጣጠረ አልነበረም" ብሏል።
ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለው ወታደራዊ ጁንታ "የሞቱት ንጹሐን አይደሉም፣ የአሸባሪው ቡድን አባላት እና ደጋፊዎች ናቸው" ሲል የደረሰበትን ውንጀላ ውድቅ አድርጓል።
መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ "የራኪን ግዛት ከ2024 ጀምሮ በአርካን አማፂ ኃይሎች (AA) ቁጥጥር ስር ነው የሚገኘው፣ ሆስፒታሉን የሚገለገሉበትም የታጠቁ ሀይሎች ናቸው" ነው ያለው።
ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ በተፈጸመው የአየር ላይ ጥቃት 33 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ፣ 76 መቁሰላቸውና 27 የሚሆኑት በጽኑ ህክምና ክፍል እንደሚገኙ የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ተናግረዋል። #anadoluagency
@ThiqahETH
❤8💔2🤔1🕊1
ቤላሩስ ለ123 የፖለቲካ እስረኞች ምህረት አደረገች።
መንግስት ይህን እርምጃ የወሰደው አሜሪካ ቤላሩስ ወደ ውጭ በምትልከው የማዳበሪያ ምርት ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተከትሎ ነው።
በይቅርታ ከወጡት መካከል በ2020 የተደረገውን ፀረ መንግስት ተቃውሞ የመራችው ማሪያ ኮላስኒኮቫ እና የሰላም ኖቤል ተሸላሚው አሌስ ቢያሊያትስኪ እንደሚገኙበት ተገልጿል።
አሜሪካ የፕሬዝዳንት ሉካሽንኮ መንግስት በ2021 ያካሄው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ አይደለም በሚል የቤላሩስ መንግስት ላይ ማዕቀብ ጥላለች።
ፕሬዚዳንት ሉካሽንኮ በዩክሬን ጦርነት ሀገራቸው ለሩሲያ እንደምትወግን በግልጽ ድጋፍ ማሳየታቸው ተገልጿል። #radiofreeeurope #skynews
@ThiqahETH
መንግስት ይህን እርምጃ የወሰደው አሜሪካ ቤላሩስ ወደ ውጭ በምትልከው የማዳበሪያ ምርት ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተከትሎ ነው።
በይቅርታ ከወጡት መካከል በ2020 የተደረገውን ፀረ መንግስት ተቃውሞ የመራችው ማሪያ ኮላስኒኮቫ እና የሰላም ኖቤል ተሸላሚው አሌስ ቢያሊያትስኪ እንደሚገኙበት ተገልጿል።
አሜሪካ የፕሬዝዳንት ሉካሽንኮ መንግስት በ2021 ያካሄው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ አይደለም በሚል የቤላሩስ መንግስት ላይ ማዕቀብ ጥላለች።
ፕሬዚዳንት ሉካሽንኮ በዩክሬን ጦርነት ሀገራቸው ለሩሲያ እንደምትወግን በግልጽ ድጋፍ ማሳየታቸው ተገልጿል። #radiofreeeurope #skynews
@ThiqahETH
❤11👏2🙏2🤔1😭1
"የበቀል እርምጃ እንወስዳለን" - ዶናልድ ትራምፕ
በሶሪያ ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸው ተነግሯል።
አይኤስአይኤስ (ISIS) በማዕከላዊ ሶሪያ ባደረሰው ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች እና አስተርጓሚ የነበረ የሀገሪቱ ዜጋ ሲገደሉ ሌሎች ሶስት ወታደሮች ተጎድለዋል።
ጥቃቱን ያደረሰው የቡድኑ አባል የነበረ ግለሰብ ፓልምይራ ከተማ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በፈጸመው ጥቃት ነው።
ስለክስተቱ አስተያየታቸውን የሰጡት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ጥቃት የደረሰበት አደገኛ ቦታ በሶሪያ መንግስት ስር አይደለም" ብለዋል።
"የሶርያ ፕሬዚዳንት አልሻራም ሀዘኑን ገልጿል" ያሉ ሲሆን "በወታደሮቻችን ላይ ለተፈፀመው ጥቃት የበቀል እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉም አክለዋል። #euronews
@ThiqahETH
በሶሪያ ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸው ተነግሯል።
አይኤስአይኤስ (ISIS) በማዕከላዊ ሶሪያ ባደረሰው ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች እና አስተርጓሚ የነበረ የሀገሪቱ ዜጋ ሲገደሉ ሌሎች ሶስት ወታደሮች ተጎድለዋል።
ጥቃቱን ያደረሰው የቡድኑ አባል የነበረ ግለሰብ ፓልምይራ ከተማ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በፈጸመው ጥቃት ነው።
ስለክስተቱ አስተያየታቸውን የሰጡት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ጥቃት የደረሰበት አደገኛ ቦታ በሶሪያ መንግስት ስር አይደለም" ብለዋል።
"የሶርያ ፕሬዚዳንት አልሻራም ሀዘኑን ገልጿል" ያሉ ሲሆን "በወታደሮቻችን ላይ ለተፈፀመው ጥቃት የበቀል እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉም አክለዋል። #euronews
@ThiqahETH
❤8👏3🤔2😱1😢1
ተመድ በሱዳን የባንግላዴሽ ወታደሮች ላይ የተፈፀመውን ግድያ አወገዘ።
ስድስት የባንግላዴሽ የሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውን የገለፀው ድርጅቱ፣ የሟቾችን ማንነት በምስል ይፋ አድርጓል ተብሏል።
የሰላም አስከባሪዎቹ በተልዕኮ ላይ በነበሩበት ወቅት የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በፈጸመው የድሮን ጥቃት ተገድለዋል።
ወታደሮቿ የተገደሉባት ባንግላዴሽ ሀዘኗን በመግለፅ፣ ከተመድ ጋር አብራ መስራቷን እንደምትቀጥል አስታውቃለች። #aljazeera
@ThiqahETH
ስድስት የባንግላዴሽ የሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውን የገለፀው ድርጅቱ፣ የሟቾችን ማንነት በምስል ይፋ አድርጓል ተብሏል።
የሰላም አስከባሪዎቹ በተልዕኮ ላይ በነበሩበት ወቅት የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በፈጸመው የድሮን ጥቃት ተገድለዋል።
ወታደሮቿ የተገደሉባት ባንግላዴሽ ሀዘኗን በመግለፅ፣ ከተመድ ጋር አብራ መስራቷን እንደምትቀጥል አስታውቃለች። #aljazeera
@ThiqahETH
💔5❤2😱1😢1
በአውስትራሊያ በጀዊሽ ማህበረሰብ በዓል ላይ በተፈጸመ ጥቃት 11 ሰዎች ሲገደሉ፣ 29 ቆሰሉ።
በቦንዲ ቢች ከተማ ሲከበር በነበረው የሀኑካህ በዓል ላይ ሁለት ታጣቂዎች ጥቃት ማድረሳቸውን የከተማዋ ፖሊስ ኦፊሰር ማል ላንዮን ገልጸዋል።
ጥቃቱ የጸረሴማዊነት አካል ነው ቢባልም የአውስትራሊያ መንግሥት "የሽብር ድርጊት" ሲል ፈርጆታል።
ከጥቃት አድራሾቹ አንዱ በተወሰደበት እርምጃ ህይወቱ ሲያልፍ፣ ሌላኛው በቁጥጥር ስር መዋሉን ኦፊሰሩ ተናግረዋል። #rns
@ThiqahETH
በቦንዲ ቢች ከተማ ሲከበር በነበረው የሀኑካህ በዓል ላይ ሁለት ታጣቂዎች ጥቃት ማድረሳቸውን የከተማዋ ፖሊስ ኦፊሰር ማል ላንዮን ገልጸዋል።
ጥቃቱ የጸረሴማዊነት አካል ነው ቢባልም የአውስትራሊያ መንግሥት "የሽብር ድርጊት" ሲል ፈርጆታል።
ከጥቃት አድራሾቹ አንዱ በተወሰደበት እርምጃ ህይወቱ ሲያልፍ፣ ሌላኛው በቁጥጥር ስር መዋሉን ኦፊሰሩ ተናግረዋል። #rns
@ThiqahETH
👏15💔9❤2🤔1😭1
"የሁሉም የስፓርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃዶች ከዛሬ ጀምሮ ተሰርዟል" - አገልግሎቱ
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሁሉም የስፓርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃዶች ከዛሬ (ታህሳስ 6/2018 ዓ/ም) ጅምሮ መሰረዙን አስታውቋል።
የፈቃድ ስረዛው በውርርድ እና በፋይናንስ ዘርፉ ላይ በተካሄደ አገር አቀፍ ግምገማ ላይ ተመስርቶ የህዝብን ጥቅም ለማስከበር የተወሰደ እርምጃ መሆኑንም ገልጿል።
ውሳኔው በስራ ላይ ባሉትና ቀደም ሲል በይፋ በታገዱት በሁሉም የውርርድ ድርጅቶች በእኩልነት ተፈጻሚ ይሆናል ብሏል አገልግሎቱ።
ለስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እና ሲስተም ኦፕሬተሮች/አቅራቢዎች ከታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአካል፣ በዲጂታል ወይም በሌላ መንገድ የሚካሄድ ማንኛውንም የውርርድ ሥራ እንዲያቋርጡ አዟል።
ሁሉም የገንዘብ ማስገቢያ መንገዶች አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ፣ አዲስ ውርርድ መቀበል ፈጽሞ እንደማይቻል አስታውቋል። #ELS
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@ThiqahETH
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሁሉም የስፓርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃዶች ከዛሬ (ታህሳስ 6/2018 ዓ/ም) ጅምሮ መሰረዙን አስታውቋል።
የፈቃድ ስረዛው በውርርድ እና በፋይናንስ ዘርፉ ላይ በተካሄደ አገር አቀፍ ግምገማ ላይ ተመስርቶ የህዝብን ጥቅም ለማስከበር የተወሰደ እርምጃ መሆኑንም ገልጿል።
ውሳኔው በስራ ላይ ባሉትና ቀደም ሲል በይፋ በታገዱት በሁሉም የውርርድ ድርጅቶች በእኩልነት ተፈጻሚ ይሆናል ብሏል አገልግሎቱ።
ለስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እና ሲስተም ኦፕሬተሮች/አቅራቢዎች ከታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአካል፣ በዲጂታል ወይም በሌላ መንገድ የሚካሄድ ማንኛውንም የውርርድ ሥራ እንዲያቋርጡ አዟል።
ሁሉም የገንዘብ ማስገቢያ መንገዶች አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ፣ አዲስ ውርርድ መቀበል ፈጽሞ እንደማይቻል አስታውቋል። #ELS
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@ThiqahETH
👏22❤5😱1😢1😭1
ጆዜ አንቶኒዮ የቺሊ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ።
የቀኝ ዘመም ሪፐብሊካን ፓርቲ ተወካይዋ አንቶኒ በምርጫው 58.17% ድምፅ አግኝተዋል።
ተፎካካሪዋ የቀድሞው የሰራተኛ ሚኒስትር ጃራ ጎት በበኩላቸው፣ 41.8 ድምፅ አግኝተዋል። #anadoluagency
@ThiqahETH
የቀኝ ዘመም ሪፐብሊካን ፓርቲ ተወካይዋ አንቶኒ በምርጫው 58.17% ድምፅ አግኝተዋል።
ተፎካካሪዋ የቀድሞው የሰራተኛ ሚኒስትር ጃራ ጎት በበኩላቸው፣ 41.8 ድምፅ አግኝተዋል። #anadoluagency
@ThiqahETH
❤5😱1🕊1
ዝምባብዌ የውጭ ሀገራት ዜጎች በታክሲ እና በዳቦ ቤት ስራዎች እንዳይሰማሩ ከለከለች።
14 የስራ ዘርፎች የስራ እድል ለመፍጠር በማሰብ ለሀገር ውሰጥ ዜጎች ቅድሚያ እንድሰጥ ተወስኗል።
ከእነዚህም ውስጥ የፀጉር ቤት፣ የውበት ሳሎን፣ የጥበቃ አገልግሎት፣ የቅጥር ኤጀንሲዎች፣የማስታወቂያ ኤጀንሲዎች፣ የብረታብረት ምርት እና የመድኃኒት ችርቻሮ ተካተዋል።
ከዚህ ባለፈም በውጭ ዜጎች የበላይነት የተያዘው የኢንዱስትሪ ዘርፍ 75% የሚሆነው በቀጣዮቹ ሶስት አመታት ለሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮች እንድንሸጋገር መወሰኑ ተገልጿል።
ዝምባብዌ ከፍተኛ ስራ አጥነት ከሚስተዋልባቸው የአፍሪካ ሀገራት በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። #zbc #iol
@ThiqahEth
14 የስራ ዘርፎች የስራ እድል ለመፍጠር በማሰብ ለሀገር ውሰጥ ዜጎች ቅድሚያ እንድሰጥ ተወስኗል።
ከእነዚህም ውስጥ የፀጉር ቤት፣ የውበት ሳሎን፣ የጥበቃ አገልግሎት፣ የቅጥር ኤጀንሲዎች፣የማስታወቂያ ኤጀንሲዎች፣ የብረታብረት ምርት እና የመድኃኒት ችርቻሮ ተካተዋል።
ከዚህ ባለፈም በውጭ ዜጎች የበላይነት የተያዘው የኢንዱስትሪ ዘርፍ 75% የሚሆነው በቀጣዮቹ ሶስት አመታት ለሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮች እንድንሸጋገር መወሰኑ ተገልጿል።
ዝምባብዌ ከፍተኛ ስራ አጥነት ከሚስተዋልባቸው የአፍሪካ ሀገራት በቀዳሚነት ትጠቀሳለች። #zbc #iol
@ThiqahEth
❤15👏4🤔3
ብሌስ ማትረወሊ የዩናይትድ ኪንግደም የስለላ ድርጅት (M16) ዋና ኃላፊ ሆነው ተሾሙ።
ማትረወሊ ተቋሙን ለመምራት የተሾሙ የመጀመሪዋ ሴት ዳይሬክተር መሆናቸው ተገልጿል።
አዲሷ ኃላፊ የምዕራቡ ዲሞክራሲ ላይ ስጋት ላሏቸው የውጭ አካላት ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።
ብሌስ ማትረወሊ ሪቻርድ ሞሬን በመተካት ነው የሀገሪቱ የውጭ የስለላ ድርጅት ኤም 16 ለመምራት ሀላፊነት የተረከቡት። #politico
@ThiqahETH
ማትረወሊ ተቋሙን ለመምራት የተሾሙ የመጀመሪዋ ሴት ዳይሬክተር መሆናቸው ተገልጿል።
አዲሷ ኃላፊ የምዕራቡ ዲሞክራሲ ላይ ስጋት ላሏቸው የውጭ አካላት ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።
ብሌስ ማትረወሊ ሪቻርድ ሞሬን በመተካት ነው የሀገሪቱ የውጭ የስለላ ድርጅት ኤም 16 ለመምራት ሀላፊነት የተረከቡት። #politico
@ThiqahETH
👏5❤2🤔1
የናይጄሪያ ፖሊስ 161 ህገወጥ የእፅ አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
ህገወጥ የአደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪዎቹ የተያዙት በደልታ ክልል አግቦር ከተማ እንደሆነ ገልጿል።
ከተጠርጣሪዎቹ ውስጥ 110 ወንዶች እና 51 ሴቶች መሆናቸውን የደልታ ክልል ፖሊስ ቃል አቀባይ ብራይት እዳፍ ተናግረዋል።
በኢንተለጀንስ በተደገፈው ዘመቻ ብዛት ያላቸው የአደንዛዥ እፆች ከተጠርጣሪዎቹ ጋር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከተያዙት ውስጥ የካናዳ ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች እንደሚገኙበት ቃል አቀባዩ አብራርተዋል። #dailypost
@ThiqahETH
ህገወጥ የአደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪዎቹ የተያዙት በደልታ ክልል አግቦር ከተማ እንደሆነ ገልጿል።
ከተጠርጣሪዎቹ ውስጥ 110 ወንዶች እና 51 ሴቶች መሆናቸውን የደልታ ክልል ፖሊስ ቃል አቀባይ ብራይት እዳፍ ተናግረዋል።
በኢንተለጀንስ በተደገፈው ዘመቻ ብዛት ያላቸው የአደንዛዥ እፆች ከተጠርጣሪዎቹ ጋር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከተያዙት ውስጥ የካናዳ ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች እንደሚገኙበት ቃል አቀባዩ አብራርተዋል። #dailypost
@ThiqahETH
❤5🙏2😢1💔1😡1
የአሜሪካ ጦር በፓስፊክ ውቅያኖስ በፈጸመው ጥቃት የስምንት ሰዎች ህይወት አለፈ።
ሦስት ጀልባዎች ላይ ጥቃት ማድረሱን ያረጋገጠው የአሜሪካ የደቡብ ኮማንድ "ምክንያቱም አደገኛ እፅ እያዘዋወሩ ነበር" ብሏል።
ጦሩ "የእፅ አሸባሪዎችም እርምጃ ተወስዶባቸዋል" በማለት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች የወንጀል ተባባሪ እንጂ ንጹሐን አለመሆናቸውን አስታውቋል።
ዘመቻው በአሜሪካ ጦር ዋና ኃላፊ ፔት ሄጌት ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ተገልጿል።
ስለደረሰው ጥቃት ገለልተኛ ሪፖርት ማግኘት አልተቻለም። #yenisafaq
@ThiqahETH
ሦስት ጀልባዎች ላይ ጥቃት ማድረሱን ያረጋገጠው የአሜሪካ የደቡብ ኮማንድ "ምክንያቱም አደገኛ እፅ እያዘዋወሩ ነበር" ብሏል።
ጦሩ "የእፅ አሸባሪዎችም እርምጃ ተወስዶባቸዋል" በማለት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች የወንጀል ተባባሪ እንጂ ንጹሐን አለመሆናቸውን አስታውቋል።
ዘመቻው በአሜሪካ ጦር ዋና ኃላፊ ፔት ሄጌት ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ተገልጿል።
ስለደረሰው ጥቃት ገለልተኛ ሪፖርት ማግኘት አልተቻለም። #yenisafaq
@ThiqahETH
😡5❤4🕊3🤔1
በሞሮኮ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ37 ሰዎች ህይወት አለፈ።
የሞሮኮ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር "ድንገተኛ ጎርፍ በአንድ ሌሊት 70 መኖሪያ መንደሮችን እና 10 ተሽከርካሪዎችን አውድሟል" ብሏል።
ሚኒስቴሩ "ትምህርትቤቶች ለሶስት ቀናት ዝግ ሆነዋል" ሲል ገልጿል።
አደጋው የተከሰተው ከዋና ከተማዋ ራባት በ320 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የሳፊ ከተማ ነው።
በከተማዋ ከ300 ሺህ በላይ ነዋሪዎች እንደሚገኙ ተገልጿል። #hurriyetdailynews
@ThiqahETH
የሞሮኮ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር "ድንገተኛ ጎርፍ በአንድ ሌሊት 70 መኖሪያ መንደሮችን እና 10 ተሽከርካሪዎችን አውድሟል" ብሏል።
ሚኒስቴሩ "ትምህርትቤቶች ለሶስት ቀናት ዝግ ሆነዋል" ሲል ገልጿል።
አደጋው የተከሰተው ከዋና ከተማዋ ራባት በ320 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የሳፊ ከተማ ነው።
በከተማዋ ከ300 ሺህ በላይ ነዋሪዎች እንደሚገኙ ተገልጿል። #hurriyetdailynews
@ThiqahETH
😭6❤1