"35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል" - አሜሪካ
"ዛሬ ሰላምን መስርተናል" - አዘርባጃን
"ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ጉልህ ስራ ተሰርቷል" - አርሜኒያ
አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጸሙ።
የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል የተባለ ስምምነት በዋሽንግተን ፈጽመዋል ተብሏል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ ከአርሜኒያው አቻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን ጋር በዶናልድ ትራምፕ አሸማጋይነት ውይይቱ መካሄዱ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን "ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው" ብለውታል።
አዘርባጃንና አርሜኒያ ከ1980ዎቹ ጀምሮ በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛትጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን "እስከወዲያኛው ይወገዳል" በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ "35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል" ያሉ ሲሆን፣ "የአዘርባጃኑ ፕሬዝዳንት አሊቭ ደግሞ "ዛሬ ሰላምን መስርተናል" ብለዋል።
የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺኒያን በበኩላቸው፣ "ለሁለቱ ጉልህ ሀገራት ግንኙነት ስራ ተሰርቷል" በማለት ገልጸዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። #bbc
@ThiqahEth
"ዛሬ ሰላምን መስርተናል" - አዘርባጃን
"ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ጉልህ ስራ ተሰርቷል" - አርሜኒያ
አርሜኒያና አዘርባጃን በአሜሪካ አማካኝነት የሰላም ስምምነት ፈጸሙ።
የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ለአስርት አመታት የዘለቀውን ግጭት ያስቆማል የተባለ ስምምነት በዋሽንግተን ፈጽመዋል ተብሏል።
የአዘርባጃን ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሌቭ ከአርሜኒያው አቻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሽኒያን ጋር በዶናልድ ትራምፕ አሸማጋይነት ውይይቱ መካሄዱ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሰላም ስምምነቱን "ረጅም ጊዜ የወሰደ ታሪካዊ ስምምነት ነው" ብለውታል።
አዘርባጃንና አርሜኒያ ከ1980ዎቹ ጀምሮ በአወዛጋቢው የናጎርኖ ካራባህ ግዛትጦርነት ውስጥ እንደነበሩ ያስታወሱት ትራምፕ ግጭቱን "እስከወዲያኛው ይወገዳል" በማለት ተናግረዋል።
ትራምፕ፣ "35 አመት ተዋግተዋል፣ አሁን ግን ወዳጆች ሆነዋል" ያሉ ሲሆን፣ "የአዘርባጃኑ ፕሬዝዳንት አሊቭ ደግሞ "ዛሬ ሰላምን መስርተናል" ብለዋል።
የአርሜኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺኒያን በበኩላቸው፣ "ለሁለቱ ጉልህ ሀገራት ግንኙነት ስራ ተሰርቷል" በማለት ገልጸዋል።
በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ሀገራት የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የንግድ ግንኙነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲጀመሩ እና ለተፈፃሚነቱ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። #bbc
@ThiqahEth
❤27🕊9🙏3🤔1
"አሜሪካ ፍልስጤምን ሀገር የማድረግ እቅድ የላትም፣ እዚያ አቅም ያለው መንግስት የለም" - ጄይ ጂ ቫንስ
የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ቫንስ ሀገራቸው ፍልስጤም ሀገር እንድትሆን ፍላጎት የላትም አሉ።
ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ "እዚያ አቅም ያለው መንግስት የለም" በማለት ገልጸዋል።
ቫንስ ይህን ያሉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉባት ባለችው እንግሊዝ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዴቪድ ላሚ ጋር በተገናኙበት ወቅት ነው።
እስራኤል በጋዛ የምትፈጸመውን ግፍ እንድታቆም አሜሪካ ጫና ማድረግ እንዳለባት አሳስበዋል ተብሏል።
እንግሊዝ፣ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና ካናዳ በሁለት ሀገርነት መፍትሄ መርህ ፍልስጤም ሉዓላዊ ሀገር እንድትሆን ጫና እያደረጉ ይገኛሉ። #indiatoday
@ThiqahEth
የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ቫንስ ሀገራቸው ፍልስጤም ሀገር እንድትሆን ፍላጎት የላትም አሉ።
ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ "እዚያ አቅም ያለው መንግስት የለም" በማለት ገልጸዋል።
ቫንስ ይህን ያሉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉባት ባለችው እንግሊዝ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዴቪድ ላሚ ጋር በተገናኙበት ወቅት ነው።
እስራኤል በጋዛ የምትፈጸመውን ግፍ እንድታቆም አሜሪካ ጫና ማድረግ እንዳለባት አሳስበዋል ተብሏል።
እንግሊዝ፣ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና ካናዳ በሁለት ሀገርነት መፍትሄ መርህ ፍልስጤም ሉዓላዊ ሀገር እንድትሆን ጫና እያደረጉ ይገኛሉ። #indiatoday
@ThiqahEth
😡25❤15😱1🙏1🕊1
"ከኛ ተፃራሪ የሚሆን ውሳኔን አንቀበልም" - ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ትራምፕ እና ፑቲን በአካል ሊገናኙ ነው መባሉን ተከትሎ በግል የፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘለንስኪ በዚህ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ልጥፋቸው በውይይቱ እሳቸውም እንዲሳተፉ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንቱ "ኪቭ ያልተካተተችበት የትኛውም ስብሰባ ውጤት አይኖረውም" ብለዋል።
አክለውም፣ "ከኛ ተፃራሪ የሚሆን ውሳኔን አንቀበልም" በማለት ፑቲንና ትራምፕ ብቻ የሚያካሂዱትን ውይይት ነቅፈውታል።
የሁለትዮሽ ንግግሩ የሚያመጣውን ውጤት "የሞተ መፍትሄ" በማለት ገና ከወዲሁ ተቃውመውታል።
"ዩክሬናውያን መሬታቸውን ለወራሪዎች አይሰጡም" ያሉት ዘለንስኪ ሀገራቸው ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። #telegraph
@ThiqahEth
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ትራምፕ እና ፑቲን በአካል ሊገናኙ ነው መባሉን ተከትሎ በግል የፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘለንስኪ በዚህ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ልጥፋቸው በውይይቱ እሳቸውም እንዲሳተፉ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንቱ "ኪቭ ያልተካተተችበት የትኛውም ስብሰባ ውጤት አይኖረውም" ብለዋል።
አክለውም፣ "ከኛ ተፃራሪ የሚሆን ውሳኔን አንቀበልም" በማለት ፑቲንና ትራምፕ ብቻ የሚያካሂዱትን ውይይት ነቅፈውታል።
የሁለትዮሽ ንግግሩ የሚያመጣውን ውጤት "የሞተ መፍትሄ" በማለት ገና ከወዲሁ ተቃውመውታል።
"ዩክሬናውያን መሬታቸውን ለወራሪዎች አይሰጡም" ያሉት ዘለንስኪ ሀገራቸው ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። #telegraph
@ThiqahEth
❤14😡3🤔2😱2😭1
"ከጋዛ ላይ እጃችሁን አንሱ፣ ዘር ማጥፋትን እንቃወማለን፣ የፍልስጤምን ድርጊት እንደግፋለን" - ሰልፈኞች
የለንደን ፖሊስ ከ460 በላይ ተቃዋሚዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።
የፍልስጤም ተሟጋቾች እስራዔል በፍልስጤውያን ላይ የምትፈጽመውን ግፍ ለመቃወም በፓርላማ አዳራሽ ፊት ለፊት መሰባሰባቸው ተገልጿል።
ተቃዋሚዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር መንግስት እስራኤል ላይ ማዕቀብ መጣልን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎችን እንዲወስድ ጠይቀዋል።
በሰልፉ ወቅት "ከጋዛ ላይ እጃችሁን አንሱ"
ዘር ማጥፋትን እንቃወማለን፣ የፍልስጤምን ድርጊት እንደግፋለን" በማለት ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ይህንን ተከትሎ የከተማዋ ፖሊስ ከ460 በላይ የሰልፉ ታዳሚዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።
ዩናይትድ ኪንግደም እንደ "የሽብር ተግባር" በመቁጠር በሀገሯ የሚደረጉ የፍልስጤም መብት ተሟጋቾችን እንቅስቃሴ አግዳለች ተብሏል። #reuters
@ThiqahEth
የለንደን ፖሊስ ከ460 በላይ ተቃዋሚዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።
የፍልስጤም ተሟጋቾች እስራዔል በፍልስጤውያን ላይ የምትፈጽመውን ግፍ ለመቃወም በፓርላማ አዳራሽ ፊት ለፊት መሰባሰባቸው ተገልጿል።
ተቃዋሚዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር መንግስት እስራኤል ላይ ማዕቀብ መጣልን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎችን እንዲወስድ ጠይቀዋል።
በሰልፉ ወቅት "ከጋዛ ላይ እጃችሁን አንሱ"
ዘር ማጥፋትን እንቃወማለን፣ የፍልስጤምን ድርጊት እንደግፋለን" በማለት ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ይህንን ተከትሎ የከተማዋ ፖሊስ ከ460 በላይ የሰልፉ ታዳሚዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።
ዩናይትድ ኪንግደም እንደ "የሽብር ተግባር" በመቁጠር በሀገሯ የሚደረጉ የፍልስጤም መብት ተሟጋቾችን እንቅስቃሴ አግዳለች ተብሏል። #reuters
@ThiqahEth
❤41😡3🕊2👏1🤔1
THIQAH
"ከኛ ተፃራሪ የሚሆን ውሳኔን አንቀበልም" - ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ትራምፕ እና ፑቲን በአካል ሊገናኙ ነው መባሉን ተከትሎ በግል የፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ዘለንስኪ በዚህ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ልጥፋቸው በውይይቱ እሳቸውም እንዲሳተፉ ጠይቀዋል። ፕሬዚዳንቱ "ኪቭ ያልተካተተችበት የትኛውም ስብሰባ ውጤት አይኖረውም" ብለዋል። አክለውም፣ "ከኛ…
"ዩክሬንን ለመቀራመት የሚደረግ ውይይት አዋጭ አይደለም" - የዩክሬን አጋር የአውሮፓ ሀገራት
6 የአውሮፓ ሀገራት የትራምፕንና የፑቲንን የተናጠል ውይይት ተቃወሙ።
ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ፊንላንድ እንዲሁም ፖላንድና እንግሊዝ በመሪዎቻቸው በኩል ባወጡት መግለጫ "የሀገር ሉዓላዊነት የሚባለው ጉዳይ ሊከበር ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።
የዩክሬን አጋር የተባሉት እነዚህ የአውሮፓ ሀገራት "ዩክሬንን ለመቀራመት የሚደረግ ውይይት አዋጭ አይደለም" ብለዋል።
ሀገራቱ "በውይይቱ ዩክሬን መሳተፍ ይኖርባታል" በማለት ጠይቀዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው፣ "የዩክሬን ሰላም ያለዩክሬን ተሳትፎ አይወሰንም" ብለዋል።
"ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄዎች የዩክሬንን እና የአውሮፓን ደህንነት መጠበቅ አለባቸው" ሲሉም ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ "ኪቭ ያልተካተተችበት የትኛውም ስብሰባ ውጤት አይኖረውም" በማለት የሁለቱን መሪዎች ስብሰባ ተቃውመዋል። #politico
@ThiqahEth
6 የአውሮፓ ሀገራት የትራምፕንና የፑቲንን የተናጠል ውይይት ተቃወሙ።
ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ፊንላንድ እንዲሁም ፖላንድና እንግሊዝ በመሪዎቻቸው በኩል ባወጡት መግለጫ "የሀገር ሉዓላዊነት የሚባለው ጉዳይ ሊከበር ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።
የዩክሬን አጋር የተባሉት እነዚህ የአውሮፓ ሀገራት "ዩክሬንን ለመቀራመት የሚደረግ ውይይት አዋጭ አይደለም" ብለዋል።
ሀገራቱ "በውይይቱ ዩክሬን መሳተፍ ይኖርባታል" በማለት ጠይቀዋል። መሪዎቹ በመግለጫቸው፣ "የዩክሬን ሰላም ያለዩክሬን ተሳትፎ አይወሰንም" ብለዋል።
"ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄዎች የዩክሬንን እና የአውሮፓን ደህንነት መጠበቅ አለባቸው" ሲሉም ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ "ኪቭ ያልተካተተችበት የትኛውም ስብሰባ ውጤት አይኖረውም" በማለት የሁለቱን መሪዎች ስብሰባ ተቃውመዋል። #politico
@ThiqahEth
❤17👏4🤔1😢1
"የሱዳንን ህዝብ ጥቅም የሚያስከብር ሲቪል መር አስተዳደር እንዲመሰረት እንፈልጋለን" - አቡዳቢ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሱዳን የርስበርስ ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቀረበች።
አቡዳቢ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆኗን ገልፃለች።
መግለጫው "ሰላምን መረጋጋትን እና የነገን ተስፋ መፈለግ ይገባል" ብሏል። "የተኩስ አቁም እንዲደረስ፣ ንጹሃን እንዲጠበቁ እና በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀናል" ሲል ገልጿል።
መግለጫው አክሎም፣ "የሱዳንን ህዝብ ጥቅም የሚያስከብር ሲቪል መር አስተዳደር እንድመሠረት እንፈልጋለን" ነው የሚለው።
ኤምሬትስ ከሱዳን የሚቀርብባትን ለፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ድጋፍ የመስጠት ውንጀላ "ሆን ተብሎ የተሰራ ፕሮፓጋንዳ" ስትል አጣጥላዋለች። #khaleejtimes
@ThiqahEth
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሱዳን የርስበርስ ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቀረበች።
አቡዳቢ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆኗን ገልፃለች።
መግለጫው "ሰላምን መረጋጋትን እና የነገን ተስፋ መፈለግ ይገባል" ብሏል። "የተኩስ አቁም እንዲደረስ፣ ንጹሃን እንዲጠበቁ እና በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀናል" ሲል ገልጿል።
መግለጫው አክሎም፣ "የሱዳንን ህዝብ ጥቅም የሚያስከብር ሲቪል መር አስተዳደር እንድመሠረት እንፈልጋለን" ነው የሚለው።
ኤምሬትስ ከሱዳን የሚቀርብባትን ለፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ድጋፍ የመስጠት ውንጀላ "ሆን ተብሎ የተሰራ ፕሮፓጋንዳ" ስትል አጣጥላዋለች። #khaleejtimes
@ThiqahEth
❤10🕊5🤔4👏1🙏1
"በሽፋ ሆስፒታል አንድ ጋዜጠኛዬ በእስራኤል ጥቃት ተገድሎብኛል" - አልጀዚራ
"ጋዜጠኛ ሳይሆን የሃማስ የህዋስ መሪ ነበር" - እስራኤል
የ28 አመቱ የአልጀዚራ ጋዜጠኛ አናስ አል ሻሪፍ በምስራቅ ጋዛ በስራ ላይ እያለ መገደሉን አልጀዚራ አስታውቋል።
ጣቢያው ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ "በሽፋ ሆስፒታል አንድ ጋዜጠኛዬ በእስራኤል ጥቃት ተገድሎብኛል" ብሎ፣ "ጥቃቱ በጋዛ የሚካሄደውን ህገወጥ ወረራ በተመለከተ ድምፅ የሚሆኑትን ለማስቆም የተደረገ ሙከራ ነው" በማለት ተቃውሟል።
የእስራኤል ጦር በበኩሉ ሟቹ "ከሀማስ አመራሮች ጋር ቅርብ ግንኙነት ነበረው" በማለት ወንጅሏል።
ጦሩ ባወጣው የማስተባበያ መግለጫ "ጋዜጠኛ ሳይሆን የሃማስ የህዋስ መሪ ነበር" ብሏል።
"በእስራኤል ንጹሃን ላይ በተፈጸሙ የሮኬት ጥቃቶች ላይ እጁ አለበት" ሲል ወቅሷል። ለዚህም የደህንነት እና የሰነድ ማስረጃዎች እንዳሉት ገልጿል።
@ThiqahEth
"ጋዜጠኛ ሳይሆን የሃማስ የህዋስ መሪ ነበር" - እስራኤል
የ28 አመቱ የአልጀዚራ ጋዜጠኛ አናስ አል ሻሪፍ በምስራቅ ጋዛ በስራ ላይ እያለ መገደሉን አልጀዚራ አስታውቋል።
ጣቢያው ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ "በሽፋ ሆስፒታል አንድ ጋዜጠኛዬ በእስራኤል ጥቃት ተገድሎብኛል" ብሎ፣ "ጥቃቱ በጋዛ የሚካሄደውን ህገወጥ ወረራ በተመለከተ ድምፅ የሚሆኑትን ለማስቆም የተደረገ ሙከራ ነው" በማለት ተቃውሟል።
የእስራኤል ጦር በበኩሉ ሟቹ "ከሀማስ አመራሮች ጋር ቅርብ ግንኙነት ነበረው" በማለት ወንጅሏል።
ጦሩ ባወጣው የማስተባበያ መግለጫ "ጋዜጠኛ ሳይሆን የሃማስ የህዋስ መሪ ነበር" ብሏል።
"በእስራኤል ንጹሃን ላይ በተፈጸሙ የሮኬት ጥቃቶች ላይ እጁ አለበት" ሲል ወቅሷል። ለዚህም የደህንነት እና የሰነድ ማስረጃዎች እንዳሉት ገልጿል።
@ThiqahEth
❤9😭4😢1
#AddisAbaba
አዲስ አበባ በመጪዎቹ ዓመታት ኮድ አንድ ታክሲዎችን ትታ ወደ አውቶብስ የትራንስፖርት ስርዓት ልትገባ ስለመሆኗ ተዘገበ።
የከተማዋ የወደፊት የትራንስፖርት ፖሊሲና ስትራቴጂ ከኮድ አንድ ታክሲዎች ይልቅ አውቶብስና ከ25 ሰው በላይ የሚጭኑ ሜትር ታክሲዎችን የሚያበረታታ ስለሆነ ከተማዋ ወደዚያው የትራንስፖርት ስርዓት ትገባለች ሲሉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል።
አንድ አውቶብስ የ8 ታክስዎችን ያህል ይጭናል፣ ከመንገድ መጨናነቅ፣ ከተመጣጣኝ የጉዞ ታሪፍ፣ ከነዳጅ ቁጠባና ከአየር ብክለት አንፃር አውቶብስን ጨምሮ ከ25 ሰው በላይ የሚጭኑ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ለከተማዋ ተመራጭ ነው ብለው፣ ማህበረሰቡ ብዙሃን ትራንስፖርት የመጠቀም ልምዱን እንዲያሳድግ መክረዋል።
ከተማዋ ውስጥ ያሉ ኮድ_አንድ_ታክሲዎች አብዛኛዎቹ አሮጌና የከተማዋን የታክሲ መስፈርት ስለማያሟሉ ጭምር ከትራንስፖርት ስርዓቱ መውጣታቸው ግድ ነው ማለታቸው ተሰምቷል።
ኮድ አንድ ታክሲዎች ከትራንስፖርት አገልግሎት ውጪ ሲሆኑ ሰዎችን ከስራ ገበታ አያፈናቅልም? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ኃላፊው፣ በመንግስት ድጋፍ ኮድ አንድ ታክሲዎችን ከ25 ሰው በላይ ወደ ሚጭኑ ሜትር ታክሲዎች የማሳደግ ሥራ ይሰራል የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
በአዲሱ የትራንስፖርት ፖሊሲና ስትራቴጂ ከ2018 ጀምሮ ከጀሞ በቄራ አድርጎ ፒያሳ የሚደርስ ፈጣን የአውቶብስ መንገድ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ከሁለት ዓመት በኋላም አዲስ አበባ ከታክሲዎች ጋር የማይገናኝ ፈጣን የአውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚኖራት ተጠቁሟል።
@ThiqahEth
አዲስ አበባ በመጪዎቹ ዓመታት ኮድ አንድ ታክሲዎችን ትታ ወደ አውቶብስ የትራንስፖርት ስርዓት ልትገባ ስለመሆኗ ተዘገበ።
የከተማዋ የወደፊት የትራንስፖርት ፖሊሲና ስትራቴጂ ከኮድ አንድ ታክሲዎች ይልቅ አውቶብስና ከ25 ሰው በላይ የሚጭኑ ሜትር ታክሲዎችን የሚያበረታታ ስለሆነ ከተማዋ ወደዚያው የትራንስፖርት ስርዓት ትገባለች ሲሉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል።
አንድ አውቶብስ የ8 ታክስዎችን ያህል ይጭናል፣ ከመንገድ መጨናነቅ፣ ከተመጣጣኝ የጉዞ ታሪፍ፣ ከነዳጅ ቁጠባና ከአየር ብክለት አንፃር አውቶብስን ጨምሮ ከ25 ሰው በላይ የሚጭኑ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ለከተማዋ ተመራጭ ነው ብለው፣ ማህበረሰቡ ብዙሃን ትራንስፖርት የመጠቀም ልምዱን እንዲያሳድግ መክረዋል።
ከተማዋ ውስጥ ያሉ ኮድ_አንድ_ታክሲዎች አብዛኛዎቹ አሮጌና የከተማዋን የታክሲ መስፈርት ስለማያሟሉ ጭምር ከትራንስፖርት ስርዓቱ መውጣታቸው ግድ ነው ማለታቸው ተሰምቷል።
ኮድ አንድ ታክሲዎች ከትራንስፖርት አገልግሎት ውጪ ሲሆኑ ሰዎችን ከስራ ገበታ አያፈናቅልም? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ኃላፊው፣ በመንግስት ድጋፍ ኮድ አንድ ታክሲዎችን ከ25 ሰው በላይ ወደ ሚጭኑ ሜትር ታክሲዎች የማሳደግ ሥራ ይሰራል የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
በአዲሱ የትራንስፖርት ፖሊሲና ስትራቴጂ ከ2018 ጀምሮ ከጀሞ በቄራ አድርጎ ፒያሳ የሚደርስ ፈጣን የአውቶብስ መንገድ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ከሁለት ዓመት በኋላም አዲስ አበባ ከታክሲዎች ጋር የማይገናኝ ፈጣን የአውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚኖራት ተጠቁሟል።
@ThiqahEth
❤20😡11👏3🤔1🕊1
"ህፃናት ከቤተሰቦቻቸው ተነጥለዋል፣ ለያለ እድሜ ጋብቻ ተጋልጠዋል፣ በአማፂ ኃይሎች ለትጥቅ ትግል በኃይል ተመልምለዋል" - የህፃናት አድን ድርጅት
በሞዛምቢክ በጦርነት ከተፈናቀሉት 60 ሺሕ ሰዎች ከ30 የሚሆኑት ህፃናት መሆናቸው ተገለፀ።
በሞዛምቢክ በካቦ ደልጋዶ ግዛት በተከሰተ ግጭት 30,000 ህፃናትን ጨምሮ 60, ሰዎች መፈናቀላቸውን ሴቭ ዘ ችልድረን የተሰኘው አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅት አስታውቋል።
በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በሐምሌ አጋማሽ የተጀመረው ግጭት እስካሁን ድረስ አለመቆሙ ተገልጿል።
ቢሮው ባወጣው መግለጫ በግጭቱ "የታጠቁ ወገኖች የፖሊስ ጣቢያዎችን፣ ትምህርት ቤቶችን እና የጤና ማዕከላትን ኢላማ አድርገዋል" ብሏል።
ከመፈናቀላቸው በተጨማሪ "ህፃናት ከቤተሰቦቻቸው ተነጥለዋል፣ ለያለ እድሜ ጋብቻ ተጋልጠዋል፣ በአማፂ ኃይሎች ለትጥቅ ትግል በኃይል ተመልምለዋል" በማለት አስረድቷል።
በአሁኑ ወቅት ዕለታዊ ድጋፎችን እያቀረበ እንደሚገኝ ገልጿል። #savethechildreninternational
@ThiqahEth
በሞዛምቢክ በጦርነት ከተፈናቀሉት 60 ሺሕ ሰዎች ከ30 የሚሆኑት ህፃናት መሆናቸው ተገለፀ።
በሞዛምቢክ በካቦ ደልጋዶ ግዛት በተከሰተ ግጭት 30,000 ህፃናትን ጨምሮ 60, ሰዎች መፈናቀላቸውን ሴቭ ዘ ችልድረን የተሰኘው አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅት አስታውቋል።
በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በሐምሌ አጋማሽ የተጀመረው ግጭት እስካሁን ድረስ አለመቆሙ ተገልጿል።
ቢሮው ባወጣው መግለጫ በግጭቱ "የታጠቁ ወገኖች የፖሊስ ጣቢያዎችን፣ ትምህርት ቤቶችን እና የጤና ማዕከላትን ኢላማ አድርገዋል" ብሏል።
ከመፈናቀላቸው በተጨማሪ "ህፃናት ከቤተሰቦቻቸው ተነጥለዋል፣ ለያለ እድሜ ጋብቻ ተጋልጠዋል፣ በአማፂ ኃይሎች ለትጥቅ ትግል በኃይል ተመልምለዋል" በማለት አስረድቷል።
በአሁኑ ወቅት ዕለታዊ ድጋፎችን እያቀረበ እንደሚገኝ ገልጿል። #savethechildreninternational
@ThiqahEth
❤7🕊4🤔3
አውስትራሊያ ለፍልስጤም የሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ ገለጸች።
የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ የፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ካናዳ ፍልስጤም ሀገር እንድትሆን ያቀረቡትን እቅድ እንደሚደግፉ ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀረበው የሁለት ሀገርነት መፍትሄ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል።
አልባኔስ ከካቢኔ አባሎቻቸው የሚነሳው ተደጋጋሚ ጥያቄ ይህን ውሳኔ ለማሳለፋ እንዳስገደዳቸው ተመላክቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋዛን ከጦር ቀጠና ማውጣት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። #thewashingtontimes
@ThiqahEth
የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ የፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ካናዳ ፍልስጤም ሀገር እንድትሆን ያቀረቡትን እቅድ እንደሚደግፉ ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀረበው የሁለት ሀገርነት መፍትሄ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል።
አልባኔስ ከካቢኔ አባሎቻቸው የሚነሳው ተደጋጋሚ ጥያቄ ይህን ውሳኔ ለማሳለፋ እንዳስገደዳቸው ተመላክቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋዛን ከጦር ቀጠና ማውጣት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። #thewashingtontimes
@ThiqahEth
❤46👏8😡4
"ፑቲን የሚታመን ሰው አይደለም፣ ከተቻለ ማስወገድ ነው" - ስታርመር
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር የትራምፕ እና ፑቲን ውይይት የተለየ ውጤት እንደማያመጣ ተናገሩ።
ምክንያት ያሉት ደግሞ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባህሪ ተለዋዋጭ ነው በሚል እንደሆነ ተገልጿል።
ስታርመር በአላስካ ይካሄዳል በተባለው የአሜሪካ ትራምፕ እና የሩሲያ አቻቸው ፑቲን የሁለትዮሽ ስብሰባ የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ "ግዴታ መሳተፍ አለባቸው" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "ፑቲን የሚታመን ሰው አይደለም፣ ከተቻለ ማስወገድ ነው" ሲሉ የተደመጡት ስታመር፣ ነገር ግን "የፕሬዝዳንት ትራምፕን ጥረት እንደግፋለን" በማለትም ተናግረዋል።
ኬር ስታርመር ይደረጋል የተባለው የተኩስ አቁም ስምምነት "ፕሬዚዳንት ፑቲን ራሳቸውን የሚያደራጁበት፣ ጦራቸውን የሚያጠናክሩበት እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል" ሲሉ ገልጸዋል። #theindependent
@ThiqahEth
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር የትራምፕ እና ፑቲን ውይይት የተለየ ውጤት እንደማያመጣ ተናገሩ።
ምክንያት ያሉት ደግሞ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባህሪ ተለዋዋጭ ነው በሚል እንደሆነ ተገልጿል።
ስታርመር በአላስካ ይካሄዳል በተባለው የአሜሪካ ትራምፕ እና የሩሲያ አቻቸው ፑቲን የሁለትዮሽ ስብሰባ የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ "ግዴታ መሳተፍ አለባቸው" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "ፑቲን የሚታመን ሰው አይደለም፣ ከተቻለ ማስወገድ ነው" ሲሉ የተደመጡት ስታመር፣ ነገር ግን "የፕሬዝዳንት ትራምፕን ጥረት እንደግፋለን" በማለትም ተናግረዋል።
ኬር ስታርመር ይደረጋል የተባለው የተኩስ አቁም ስምምነት "ፕሬዚዳንት ፑቲን ራሳቸውን የሚያደራጁበት፣ ጦራቸውን የሚያጠናክሩበት እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል" ሲሉ ገልጸዋል። #theindependent
@ThiqahEth
😡23❤9👏4😢1
የኮሎምቢያ ፕሬዚደንታዊ እጩ ህይወታቸው አለፈ።
ከሁለት ወር በፊት ጥቃት የተፈጸመባቸው የኮሎምቢያ ሴናተርና ፕሬዚዳንታዊ ሚጉዌል ኡራይብ መሞታቸው ተገልጿል።
ኡራይብ በ2026 ለሚካሄደው ምርጫ በቦጎታ ግዛት ዘመቻ ላይ እያሉ ጥቃት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
የ39 አመቱ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በሳንቴፌ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቢቆዩም ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም ነው የተባለው።
የኮሎምቢያ አቃቤ ህግ ጥቃቱን አድርሰዋል ተብለው የተጠረጠሩ ስድስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል። #timeslive
@ThiqahEth
ከሁለት ወር በፊት ጥቃት የተፈጸመባቸው የኮሎምቢያ ሴናተርና ፕሬዚዳንታዊ ሚጉዌል ኡራይብ መሞታቸው ተገልጿል።
ኡራይብ በ2026 ለሚካሄደው ምርጫ በቦጎታ ግዛት ዘመቻ ላይ እያሉ ጥቃት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
የ39 አመቱ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በሳንቴፌ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቢቆዩም ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም ነው የተባለው።
የኮሎምቢያ አቃቤ ህግ ጥቃቱን አድርሰዋል ተብለው የተጠረጠሩ ስድስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል። #timeslive
@ThiqahEth
😢9❤7😱3🕊3😭1