THIQAH
9.39K subscribers
5.11K photos
56 videos
1 file
40 links
ይህ ቲቃህ (ታማኝ) ኢትዮጵያ በ @tikvahethiopia
(ቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ) ሥር የሚተዳደር የኢትዮጵያን ጨምሮ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ገጽ ነው።

ማንኛውንም ጥቆማና አስተያየት @EyobTikuye ማድረስ ይቻላል።
Download Telegram
የኬንያ ባንኮች ብድር የማይመልሱ ግለሰቦች መበራከታቸውን ተከትሎ ለኪሳራ መጋለጣቸው ተገለጸ።

የኬንያ ማዕከላዊ ባንክ (CBK) 10% የነበረውን የወለድ መጠን ከጥር 2025 ጀምሮ ወደ 9.5 ዝቅ አድርጓል።

በሀገሪቱ የሚገኙ የንግድ ባንኮች የሚያቀርቡትን ብድር በ15.4% ቀንሰዋል ተብሏል።
#tukonews

@ThiqahEth
11🤔2😱2😢2
ደቡብ ኮሪያ ወታደሮቿን የድምፅ ማጉያ እንዳይጠቀሙ አዘዘች።

መረጃዎችን ለማስተላለፍ የሚጠቅሙ የድምፅ ማጉያዎች በጊዜያዊነት ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ታግደዋል ተብሏል።

ሴዑል ክልከላ የጣለችው ከሰሜን ኮሪያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ላይ በሰፈሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ላይ ብቻ መሆኑ ተገልጿል። 
#afp

@ThiqahEth
7😢3👏1
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች 20 ተሽከርካሪዎች እርስበርስ በተጋጩበት አደጋ 9 ሰዎች ተጎዱ።

በፉጃይራህ ከተማ በደረሰው አደጋ ከአልሂና ወደ ድባ የሚወስደው መንገድ ሙሉ በሙሉ መዘጋቱ ተገልጿል።

ከትራፊክ መጨናነቅና መንገድ መዘጋት ውጭ የከፋ አደጋ አልደረሰም ተብሏል።

የአደጋ ጊዜ ባለሙያዎች በስፍራው ደርሰው የህክምና አገልግሎት እየሰጡና የትራፊክ ፍሰትን እየተቆጣጠሩ ይገኛሉ ተብሏል።

የአደጋው መንስኤ አንድ ተሽከርካሪ በእሳት ስትቃጠል በፍጥነት የሚጓዝ መኪና በዝግታ ሲጓዙ ከነበሩ ሌሎች መኪናዎች ጋር በመጋጨቱ እንደሆነ ተገልጿል።
#gulfnews

@ThiqahEth
😢74😡2😭1
#Ethiopia #Mpox

"በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች ቁጥር 18 መድረሱ የተረጋገጠ ሲሆን፣ በበሽታው ከተያዙት ታማሚዎች መካከል የአንድ ወር ህፃን ሕይወት አልፏል" - ጤና ሚኒስቴር

ጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ የMpox በሽታ ታማሚ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከተገኘ ጀምሮ እስከ ሰኔ 4 ቀን 2017  ዓ/ም ድረስ 102 የላብራቶሪ ምርመራዎች መደረጋቸውን አስታውቋል።

"በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች ቁጥር 18 መድረሱ የተረጋገጠ ሲሆን፣ በበሽታው ከተያዙት ታማሚዎች መካከል የአንድ ወር ህፃን ሕይወት አልፏል" ብሏል።

እስካሁን ከተያዙት 18 ሰዎች መካከል 5ቱ ሙሉ ለሙሉ ማገገማቸውንም ገልጿል።

በሽታው የተለያዩ ዝርያዎች እንዳሉት፣ ከታማሚዎች በተወሰደ ናሙና የዘረመል ምርመራ ተደርጎ በተገኘው ውጤት ክሌድ 1ቢ (Clade 1b የተባለው የዝርያ አይነት መሆኑን ተረጋግጧል።

"ይህ የቫይረስ ዝርያ በአንጻሩ ከፍተኛ የሚባል የስርጭት መጠን ያለውና በዚህ የቫይረስ ዝርያ ከበሽታው ጋር በተያያዘ የሚከሰት የሞት መጠን በአንጻሩ ከፍተኛ እንደሆነ በሌሎች ሀገራት በተገኘ ልምድ ለማወቅ ተችሏል" ተብሏል።

በሽታውን ለመቆጣጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየተሰራ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፣ የበሽታው ምልክቶች ካጋጠሙ
#በ8335 ወይም 952 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ እንዲሰጥ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@ThiqahEth
7💔5😢2
"አሜሪካ ኢራን የኑክሌር ባለቤት እንድትሆን አትፈቅድም፤ ስምምነቱን የማትቀበለው ከሆነ የኃይል እርምጃ እንወዳለን" - ፕሬዚዳንት ትራምፕ

ትራምፕ አሜሪካ ከመካከለኛው ምሥራቅ ልትወጣ እንደምትችል ጠቆሙ።

ውሳኔው የመጣው በዋሽንግተንና በቴህራን መካከል፣ "በኑክሌር ፕሮግራም" ላይ የተደረጉ ውይይቶች ውጤት ማምጣት ባለመቻላቸው ነው ተብሏል።

"ወታደሮቻችን አካባቢውን ለቀው መውጣት አለባቸው" ያሉት ትራምፕ፣  "ምክንያቱም አደገኛ ቦታ ይሆናል" ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ ባደረጉት ንግግር፣ "አሜሪካ ኢራን የኑክሌር ባለቤት እንድትሆን አትፈቅድም፤ ስምምነቱን የማትቀበለው ከሆነ የኃይል እርምጃ እንወዳለን" ሲሉ ተደምጠዋል።

በተያያዘ መረጃ አሜሪካ በኢራቅ የሚገኘው ኤምባሲዋ የሚገኙ ሰራተኞችን በግማሽ መቀነሷ ተሰምቷል። 
#reuters

#ThiqahEth
11🤔4🕊2
በደቡብ አፍሪካ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ49 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ጠፉ።

ከሞቱት ሰዎች መካከል ከትምህርት ቤት ወደ ቤታቸው በመመለስ የነበሩ ተማሪዎች እንደሚገኙበት የኢስተርን ኬፕ ግዛት ባለስልጣን ኦስካር ማቡያኔ ተናግረዋል።

በጎርፍ አደጋው የተጎዱ ከ500 በላይ የሚደርሱ ሰዎች ወደ ጊዜያዊ መጠለያ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል።

ማቡያኔ በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ መጣሉ ለአደጋው ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
#aljazeera

@ThiqahEth
😢92💔2👏1
"በኢራን ላይ የሚቃጣን ጥቃት አልታገስም" - ሁቲ

የሁቲ አማፂ ቡድን አሜሪካና እስራኤል ኢራንን የሚያጠቁ ከሆነ በጦርነቱ እንደሚሳተፍ አስጠነቀቀ።

ቡድኑ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ "በቀጠናው አዲስ ዙር ግጭት መፈጠሩ አይቀርም" ሲል አስታውቋል።

"በአሜሪካ ለሚጀመር ጥቃት በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ እንገኛለን" ያለው ሁቲ፣ "በኢራን ላይ የሚቃጣን ጥቃት አንታገስም" ሲል አስጠንቅቋል።

"በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ላይ የሚደረግ ጦርነት የኛም ጦርነት ነው" በማለትም አስታውቋል።
#politicalwire

@ThiqahEth
40😡8🤔6🕊3😢1
በአውሮፕላን አደጋ ቢያንስ የ30 ሰዎች ህይወት አለፈ።

242 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ኤይር ኢንዲያ AI171 አውሮፕላን በጉጅራት ከተማ ተከስክሷል።

በአደጋው ህይወታቸው ያለፉ 30 አስክሬን ማንሳቱን ያስታወቀው የህንድ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ሌሎች ተጎጅዎችን የማፈላለግ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
#thestraitstimes

@ThiqahEth
😢192👏1🕊1
THIQAH
በአውሮፕላን አደጋ ቢያንስ የ30 ሰዎች ህይወት አለፈ። 242 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ኤይር ኢንዲያ AI171 አውሮፕላን በጉጅራት ከተማ ተከስክሷል። በአደጋው ህይወታቸው ያለፉ 30 አስክሬን ማንሳቱን ያስታወቀው የህንድ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ሌሎች ተጎጅዎችን የማፈላለግ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል። #thestraitstimes @ThiqahEth
#Update

"ከ100 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል" - የአደጋ ጊዜ ባለሙያዎች

ከህንድ ወደ እንግሊዝ እየተጓዘ የነበረው አዎሮፕላን ባጋጠመው መከስከስ የሟቾች ቁጥር ከ100 በላይ ማሻቀቡ ተገልጿል።

አውሮፕላኑ 242 ተጓዦችን አሳፍሮ እንደነበር የተመለከተ ሲሆን፤ በሕይወት የተረፉ እንዳሉና እንደሌሉ በግልጽ አልተነገረም።

ሆኖም ጉዳት የደረሰባቸውን ተጓዦች ወደ ሆስፒታል ተወስደዋልም ተብሏል።

አውሮፕላኑ የተከሰከሰው በጋራ መኖሪያ ህንፃ ላይ ነው ሲሆን፣ 80% የሚሆነው ሙሉ በሙሉ ወድሟል።  

ከተጓዦቹ መካከል 11ዱ ህፃናት እንደሆኑ ባለሙያዎቹ ተናግረዋል። 
#thenorthweststar

@ThiqahEth
😢135😭2