አቡ ሩሐማ - Abu Ruhama
971 subscribers
784 photos
137 videos
22 files
911 links
➧«ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ»፡፡ (ማኢዳ፥3)
Download Telegram
"ኢየሱስ ተሰቅሎ አንዴ ድነናል፣ መጨረሻችንም ገነት መሆኑን እናውቃለን" የምትሉ ወንጌላውያን ክርስቲያኖች ለምን ቤተ ክርስቲያን እንደምትሄዱ አይገባኝም። እንደ አምነታችሁ ከሆነ ስራም አያስፈልጋችሁም፣ እኛንም በመስበክ መባተል አይጠበቅባችሁም..! ለምንስ ትደክማላችሁ?ግን እንዴው ለህሊናችሁ እንዲሆን ቁርአን እንዳለው በትክክል "የገነት ነን" የሚለውን ካረጋገጣችሁ እስኪ ከልባችሁ ሞትን ተመኙ..! አንዳችሁም እንደማትመኙት ውስጣችሁ ያውቀዋል። ለስራ የደከመ ሰነፍ ግለሰብ እንጅ አቅል ያለው ሰው እንዴት ይህንን ሀሳብ በህይወቱ ተቀብሎ እንደሚኖረው ሳስበው እራሱ ይገርመኛል።

___
https://t.me/Yahyanuhe
👍2
የእግዚአብሔርን ምስጢር የሚከልሉ ሰማያት?
...
“ስለምን እግዚአብሔር እነዚህን ሰማያት ፈጠራቸው፣ሲፈጥራቸውስ ወደ ውጭ የሚያስወጣ የሚያሳይ በር፣መስኮት ሳያወጣላቸው ቀረ ቢሉ፤ዛሬ ከውጭ የሚመጣ እንግዳ ወደ እልፍኝ ገብቶ ወደ ጓዳ አልፎ ዕቃ ማየት እንዳይገባው ከዚያ ቀጥሎ የሚፈጥራቸው መላዕክትና ደቂቀ አዳም ምስጢሩን እንዳያዩ እንዳያውቁ ነው።”

[መፅሐፈ አክሲማሮስ ዘእሑድ 18 ገፅ 21]
...
https://t.me/AhmedResponse
👍1
⚠️ከአምስት ነገሮች በፊት አምስት ነገሮች!

ረሱል (▫️) እንዲህ ብለዋል፦

﴿اغْتَنِمْ خَمْسًا قبلَ خَمْسٍ: شَبابَكَ قبلَ هِرَمِكَ، وصِحَّتَكَ قبلَ سَقَمِكَ، وغِناكَ قبلَ فَقْرِكَ، وفَراغَكَ قبلَ شُغْلِكَ، وحَياتَكَ قبلَ مَوْتِكَ.﴾

“አምስት ነገሮች ወዳንተ ከመምጣታቸው በፊት በአምስት ነገሮች ቅደማቸው። ወጣትነትህን እርጅና ከመምጣቱ በፊት፣ ጤንነትህን በሽታ ከመምጣቱ በፊት፣ ሀብትህን ድህነት ከመምጣቱ በፊት፣ ትርፍ ግዜህን ትርፍ ግዜ ከማጣትህ በፊት፣ ህይወትህን ሞት ከመምጣቱ በፊት።”

📚 ሸይኽ አልባኒ በሶሂህ አተርጊብ ውስጥ ሶሂህ ብለውታል: 3355

☑️በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦

⬛️https://bit.ly/4ayf0xJ

⬛️https://bit.ly/486xnrS

⬛️https://bit.ly/41zEZkk

⬛️https://bit.ly/4arMbTx

⬛️https://bit.ly/41tIUPv

⬛️https://bit.ly/3UTTSwh
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ምሳሌያዊ አገላለጾች
• ════•════•
ክቡር ቁርዓን
۞ اللَّهُ نُورُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ مَثَلُ نُورِهِ كَمِشْكَاةٍ فِيهَا مِصْبَاحٌ ۖ الْمِصْبَاحُ فِي زُجَاجَةٍ ۖ الزُّجَاجَةُ كَأَنَّهَا كَوْكَبٌ دُرِّيٌّ يُوقَدُ مِن شَجَرَةٍ مُّبَارَكَةٍ زَيْتُونَةٍ لَّا شَرْقِيَّةٍ وَلَا غَرْبِيَّةٍ يَكَادُ زَيْتُهَا يُضِيءُ وَلَوْ لَمْ تَمْسَسْهُ

➳‹‹ አላህ የሰማያትና የምድር አብሪ ነው፡፡ የብርሃኑ ምሳሌ በውስጧ መብራት እንዳለባት (ዝግ) መስኮት፣ መብራቱ በብርጭቆ ውስጥ የኾነ፣ ብርጭቆይቱ ፍፁም ሉላዊ ኮከብ የምትመሰል፣ ምሥራቃዊው ምዕራባዊም ካልኾነች ከተባረከች የወይራ ዛፍ ዘይቷ እሳት ባይነካውም እንኳ ሊያበራ የሚቀርብ ከኾነች (ዘይት) የሚቃጠል እንደ ሆነ (መብራት) ነው፡፡ ››❨ኑር፥ 35❩
●*●*●*●*●*️●*️●
ባይብል
➳‹‹ ጨው መልካም ነው ጨው ዐልጫ ቢኾን ግን በምን ይጣፈጣል።›› ❨ሉቃስ 14፥34❩

➾ ‹‹በምሳሌ ይተካከላሉን? አትገሰጹምን?››
❨ሁድ:24❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/sunah13
👍2🔥1
ይድረስ ለክርስቲያን ሴት ሰባኪያን!
• ════•════•
➳ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና። ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
❨1ኛ ቆሮንቶስ 14፥34-35❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍21
Forwarded from የመዳን መንገድ (ኢብኑ-ያሲር ሸሪዓዊ የውይይት መድረክ Chanel📚📚)
እውን በክርስትና የአጎት ልጅ ማግባት ክልክል ነውን?

በክርስትና የአጎት ልጅ ማግባት ክልክል እንደሆነ አስመስለው #የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች እንደሚሉት  እስልምናን ለመውቀስ ይሞክራሉ
እስኪ የነሱን መፅሀፍ ምን እንደሚል አብረን እንየው፡-
-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_

① ☞ እንበረምም #የአጎቱን ልጅ ዮካብድን አገባ አሮንና ሙሴንም ወለደችለት የእንበረምም የሕይወቱ ዘመን መቶ ሠላሳ ሰባት ዓመት ነው። (ኦሪት ዘጸአት ም 6 ቁ 20)

እንደምንመለከተው እንበረምም የአጎቱን ልጅ ዮካብድን አግብቶ ሙሴንና አሮንን እንደወለደ እናያለን፡፡
-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_

② ☞ ይስሐቅም ያዕቆብን ጠራው ባረከውም እንዲህ ብሎም አዘዘው። ከከነዓናውያን ሴቶች ልጆች ሚስትን አታግባ ተነሣና ወደ እናትህ አባት ወደ ባቱኤል ቤት ወደ ሁለቱ
ወንዞች መካከል ሂድ ከዚያም #ከእናትህ #ወንድም ከላባ ሴቶች # ልጆች ሚስትን አግባ።(ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 28-1:2)

እዚህም ጋር ይስሐቅ እንደምታዩት ያዕቆብ የእናቱን ወንድም (የአጎቱን) ሴት ልጆች እንዲያገባ ሲያዘው እንመለከታለን፡፡ ታ
-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_

③☞ (ኦሪት ዘሌዋውያን 18: 6–18)
ላይ እግዚያብሄር ለትዳር የተከለከሉ የሴት አይነቶችን ሲጠቅስ የአክስት ወይም የአጎት ልጅ አልተካተተም።
ያ ማለት ደግሞ የአጎት (የአክስት) ልጅ ማግባት ይፈቀዳል ማለት ነው፡፡
-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_

እስልምና ብቻ ነው እንዴ የአጎትን ልጅ ማግባት የፈቀደው?
ታዳያ ለምን ይሆን ክርስቲያን ወገኖቻችን ለምን ይሆን የአጎትን ልጅ ማግባት የሚከለክሉት?
ስለዚህ ክርስቲያን ወገኖቻችን ሆይ እስልምናን በጭፍን ከመናገራቹ በፊት የኛስ መፅሀፍ ምን ይላል ብላችሁ መፅሀፋችሁን አንብቡት፡፡
አንዳንዶች እንዲህ ከመፅሀፍ ቅዱስ የኦሪት ጥቅስ ስንሰጣቸው የኦሪት ህግ እኮ በእየሱስ ተሽሯል ይላሉ ነገር ግን እየሱስ ይሄንን ንግግራቸውን አጥብቆ ይቃወማል፡፡
እየሱስ እንዲህ ይላል፡-
""እኔ ህግና ነብያትን ልተገብር እንጅ ልሽር አልመጣሁም""፡፡
(ማቴወስ 5፡17)
እየሱስ እኔ ህግ አልሽርም እያላችሁ ነው፡፡
ስለዚህ እየሱስ ምንም ህግ ሊሽር እንዳልመጣ እየነገራችሁ ለምን አትተገብሩትም።ለምን ለነፍሳችሁ ደስ የሚላችሁን ብቻ ተግብራችሁ ያልተመቻችሁ ትተዋላችሁ።
-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_-_
አላህ ወደ  ቀጥተኛው መንገድ ይምራችሁ
✍️ሰለምቴው ወድም ሙስጠፋ ነኝ

@Alfurqan12b
@Alfurqan12b     
ወሰላሙ አለይኩም
                                               
👏2👍1
عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ قَالَ اللَّهُ أَعْدَدْتُ لِعِبَادِي الصَّالِحِينَ مَا لاَ عَيْنٌ رَأَتْ، وَلاَ أُذُنٌ سَمِعَتْ، وَلاَ خَطَرَ عَلَى قَلْبِ بَشَرٍ ‏.”

አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነብዩ”ﷺ” እንዲህ ብለው አሉ፦ አላህም እንዲህ አለ፦ እኔ ለደጋግ ባሮቼ አይን አይቶት የማያውቅ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅና በሰው ልቦና ውል ብሎ የማያውቅ ጸጋን አዘጋጅቻለው። ❨ቡኻሪ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 123❩
▣ የተፈፀሙ የነብዩ ትንቢቶች ▣
📌️ የጊዜ መፍጠን(ከጊዜ ውስጥ በረካ መጥፋት)
➣ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡-
ቂያማ ሊቆም አካባቢ ጊዜ ይፈጥናል አመት ልክ እንደ ወር ወሩ ልክ እንደ ሳምንት፣ ሳምንት ልክ እንደ አንድ ቀን፣ አንድ ቀን ልክ እንደ አንድ ሰዐት ፣አንድ ሰዐት
ልክ እንደ እሳት ብለጭታ ይሆናል። ❨ቲርሚዚ:2332❩
●*●*●*●*●*️●*️●
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
የሰጠኸኝን ቃል?

የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ።”
  — ዮሐንስ 17፥8

ክርስቲያኖች ሲናገሩ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው ይላሉ!
ስለሆነም ኢየሱስ ራሱን የቻለ የአምላክ ሁለተኛ አካል ነው የሚል ድምዳሜ ይደርሳሉ!

የእኔ ጥያቄ
:-ኢየሱስ የእግዚአብሔር ቃል ከሆነና የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑም የተነሳ ኢየሱስ ራሱን የቻለ የእግዚአብሔር ሁለተኛ አካል ከሆነ! ከላይ ባለው ጥቅስ ኢየሱስ የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁ ሲል የትኛውን ቃል ነው የሰጣቸው?

:-ኢየሱስ ለሐዋርያቱ የሰጣቸው ቃልስ ከኢየሱስ እና ከእግዚአብሔር የተለየ ራሱን የቻለ የእግዚአብሔር ሌላኛው አካሉ የማይሆንበት ምክንያት ምንድን ነው?

:-ኢየሱስ ለሐዋርያት የሰጣቸው ቃል ራሱን የቻለ የእግዚአብሔር ሌላኛው አካሉ ከሆነ ደግሞ ሥላሴ የሚለው ትምህርት ቀርቶ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እና ኢየሱስ ለሐዋርያት የሰጣቸው የእግዚአብሔር ቃል አራት አካል ሊሆኑ ነው?

ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ።
https://t.me/ewnet_lehulum
👍1
Forwarded from የመዳን መንገድ (ኢብኑ-ያሲር ሸሪዓዊ የውይይት መድረክ Chanel📚📚)
📮 እንቁጣጣሽ ማን ኣመጣሽ

🔭 "ጳጉሜ" የሚለው ቃል "ኤጳጉሚኖስ" ከሚለው ከግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ "ተጨማሪ" ወይም "የተጨመረ" ማለት ነው።

🔜 ጳጉሜ የወር ስም ሲሆን በነባሮች 12 ወራት ላይ የተጨመረ 13ኛ ወር ነው።

🔜 ይህም ወር በነሐሴ እና በመስከረም መካከል የሚገኝ የመጨረሻው ወር ነው።

🔜 ጳጉሜ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በዘመነ ዮሐንስ ስድስት ቀናት ሲኖሩት በዘመነ ሉቃስ ዘመነ-ማቴዎስ እና በዘመነ -ማርቆስ ደግሞ አምስት ቀናት ይሆናል።

🔜 ልብ በሉ ይህ ወር ከግሪክ ሄለኒዝም ጊዜ ከአሌክሳንድርያ ወደ ኢትዮጵያ የገባ እንጂ በዕብራውያን አቆጣጠር ላይ 12 ወራት ብቻ ነው ያለው።

♻️ አላህም የወሮች ቁጥር በእርሱ መጽሐፍ በለውሀል መህፉዝ ማለትም በጥብቁ ሰሌዳ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው፦

📖 قال الله تعلى:- ﴿ ﺇِﻥَّ ﻋِﺪَّﺓَ ﭐﻟﺸُّﻬُﻮﺭِ ﻋِﻨﺪَ ﭐﻟﻠَّﻪِ ﭐﺛْﻨَﺎ ﻋَﺸَﺮَ ﺷَﻬْﺮًۭﺍ ﻓِﻰ ﻛِﺘَٰﺐِ ﭐﻟﻠَّﻪِ ﻳَﻮْﻡَ ﺧَﻠَﻖَ ﭐﻟﺴَّﻤَٰﻮَٰﺕِ ﻭَﭐﻟْﺄَﺭْﺽَ ﻣِﻨْﻬَﺂ ﺃَﺭْﺑَﻌَﺔٌ ﺣُﺮُﻡٌۭ ۚ ﺫَٰﻟِﻚَ ﭐﻟﺪِّﻳﻦُ ﭐﻟْﻘَﻴِّﻢُ ۚ ﻓَﻠَﺎ ﺗَﻈْﻠِﻤُﻮﺍ۟ ﻓِﻴﻬِﻦَّ ﺃَﻧﻔُﺴَﻜُﻢْ ۚ ﻭَﻗَٰﺘِﻠُﻮﺍ۟ ﭐﻟْﻤُﺸْﺮِﻛِﻴﻦَ ﻛَﺂﻓَّﺔًۭ ﻛَﻤَﺎ ﻳُﻘَٰﺘِﻠُﻮﻧَﻜُﻢْ ﻛَﺂﻓَّﺔًۭ ۚ ﻭَﭐﻋْﻠَﻤُﻮٓﺍ۟ ﺃَﻥَّ ﭐﻟﻠَّﻪَ ﻣَﻊَ ﭐﻟْﻤُﺘَّﻘِﻴﻦَ ﴾
سورة التوبة [ 9:36]

📖  አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር በአላህ መጽሐፍ ዉስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን  አሥራ  ሁለት # ወር ነው፤ ከነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፤ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው፤ በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ፤
[ሱረቱ ተውባህ 9፥36]

🔜 ይህ የሚያሳየው የኢትዮጵያው ዘመን መለወጫ በልምድ ከግሪክ የመጣ ሰርጎገብ እንጂ አገር በቀል አይደለም።

🔜 ከዚያም ባሻገር መለኮታዊ ትእዛዝ ያለው ሳይሆን ሰው ሰራሽ ቢድዓ ነው ዓመተ-ምህረትን ያማከለ ዘመነ-ሉቃስ ዘመነ-ዮሐንስ ዘመነ-ማቴዎስ እና ዘመነ -ማርቆስ ሰው ሰራሽ ትምህርት ነው።

♻️ በዛ ላይ የባእድ አምልኮ የሚፈፀምበት ቀን ነው።

🔭 በጳጉሜ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች ዶሮዎች ድመቶች ጥንቸሎች ወዘተ... ታርደው ይጣላሉ።

🔜 በደም የተነከሩ ሳንቲሞች ብሮች ጌጣ-ጌጦች እና የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።

♻️ ይህ ቀን ሲያልቅ የቀኑ መጨረሻ በጉጉት ስለሚጠበቅ "እንቁ" ተባለ።

♻️ የሚያመጣው ጣጣና መዘዝ ደግሞ "ጣጣሽ" ተባለ በጥቅሉ "እንቁ-ጣጣሽ" ተባለ።

📌 ጥንቆላና ድግምት ከትልቁ ሽርክ የሚመደቡ የፈጣሪያችንን የአላህን ሃቅ የሚነካ ትልቅ በደል ነው።

📖 قال الله تعلى:- ﴿ واتبعوا ما تتلو الشياطين على ملك سليمان وما كفر سليمان ولكن الشياطين كفروا يعلمون الناس السحر وما أنزل على الملكين ببابل هاروت وماروت وما يعلمان من أحد حتى يقولا إنما نحن فتنة فلا تكفر فيتعلمون منهما ما يفرقون به بين المرء وزوجه وما هم بضارين به من أحد إلا بإذن الله ويتعلمون ما يضرهم ولا ينفعهم ولقد علموا لمن اشتراه ما له في الآخرة من خلاق ولبئس ما شروا به أنفسهم لو كانوا يعلمون ﴾ .
سورة البقرة [2:96]

📖 አላህም እንዲህ አለ:- በነብዩ ሱለይማን (ዐለይሂሰላም) ዘመነ-መንግስት ሸይጧኖች የሚያነቡትንም ድግምት ተከተሉ ሱለይማን ግን አልካደም ድግምተኛ አልነበረምና ግን ሸይጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ.....

📖 قال الله تعلى:- ﴿ قال فإنا قد فتنا قومك من بعدك وأضلهم السامري ﴾
سورة طه [20:69]

📖 አላህም እንዲህ አለ:- ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም አልን  ይላል። ሱረቱ ጧሀ [20፥69]

📌 እንቁጣጣሽን ማክበር አቆጣጠሩ አገራዊ ሳይሆን እምነታዊና ባህላዊ መሰረት ያለው ሲሆን ከእርሱ ጋር የተያያዙት ባእድ አምልኮ አስበን ከዚህ ሰው ሰራሽ በአል እራሳችንን እንጠብቅ።
✍️ሰለምቴው ወድማቹ ሙስጠፋ ነኝ

@Alfurqan12b
@Alfurqan12b     
ወሰላሙ አለይኩም
የአላህ መልዕክት
• ════•════•
۞ وَلَا تُجَادِلُوا أَهْلَ الْكِتَابِ إِلَّا بِالَّتِي هِيَ أَحْسَنُ .
➳‹‹የመጽሐፉን ባለቤቶችም በዚያች እርሷ መልካም በኾነችው ክርክር እንጂ አትከራከሩ፡፡»
❨አንከቡት፥46❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/sunah13
እጅግ ብዙ ተንታኞች፤ የታሪክ ተመራማሪዎችና ፊላስፎች ይህንን አለምአቀፍ፣ ሁለንተናዊና ስኬታማ የሆነውን የነቢዩን ተልዕኮ እውነታ አፅድቀዋል።

ድንቅ ኢንጊሊዛዊ ፀሀፊ ጆርጅ በርናንድ ሾው እንዲህ ይላሉ:-

“ሁሌም የሙሀመድን እምነት የምሰጠው ቦታ እጅግ የላቀ ነው፤ ይኸውም ከምርጥ መገለጫዎቹ የመነጨ ነው። ይህ እምነት ከየትኛውም የአለም ተለዋዋጭ መልክ ጋር በየትኛው ቦታና ጊዜ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ብቸኛው እምነት ነው። ስለዚህ ድንቅ ሰው (ሙሀመድ) በጥልቀት አጥንቻለሁ በኔ አመለካከት ‘የክርስቶስ ጠላት’ ከመባል እጅግ የራቀና ይልቁንም ‘የሰው ልጅ አዳኝ’ ሊባል ይገባዋል።” (ዘ ጄኒዩን ኢስላም ጥራዝ 1፣ ቁ.8፤ 1936)

አሜረከዊው የታሪክ ሰው ማይክል ሀርት በታሪክ የታዩና ተፅዕኖ ያሳደሩ የአለምን ምርጥ ሰዎች ከደረጃ ባስቀመጡበት “ዘ 100፡ ኤ ራንኪንግ ኦፍ ዘ ሞስት ኢንፉሌንሺያል ፐርሰን” በተሰኘው መፅሀፍ ለምን ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመጀመሪያው ደረጃ እንደሰጣቸው ሲናገር እንዲህ ይላል:-

“በእርግጥ በታሪክ የአለማችን ምርጥና ታላቅ ተፅዕኖ ያሳደሩ ሰዎች ተርታ ለሙሀመድ አንደኛ ደረጃ መስጠቴ አንዳንድ አንባቢዎችን ሊያስገርምና ሌሎችን ሊያጠያይቅ ይችል ይሆናል። ሆኖም ግን በአለማዊው ሆነ በሀይማኖታዊው ዘርፍ ሙሉ በሙሉ የተሳካላት ብቸኛ ሰው ሙሀመድ ነው።” (ዘ 100፡ ኤ ራንኪንግ ኦፍ ዘ ሞስት ኢንፉሌንሺያል ፐርሰን፤ ኒዮርክ፤1978፣ ገፅ 33)
.......
ከ Invitation to Islam ፅሁፍ ላይ ኤዲት የተደረገ
ነብያዊ ሐዲስ
• ════•════•
۞ عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ فِي خُطْبَتِهِ يَحْمَدُ اللَّهَ وَيُثْنِي عَلَيْهِ بِمَا هُوَ أَهْلُهُ ثُمَّ يَقُولُ مَنْ يَهْدِهِ اللَّهُ فَلَا مُضِلَّ لَهُ وَمَنْ يُضْلِلْهُ فَلَا هَادِيَ لَهُ إِنَّ أَصْدَقَ الْحَدِيثِ كِتَابُ اللَّهِ وَأَحْسَنَ الْهَدْيِ هَدْيُ مُحَمَّدٍ وَشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا وَكُلُّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ .

➳ጃቢር ኢብኑ ዐብደላህ እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ሑጥባቸው ላይ እንደተናገሩት፦ "አላህ የመራውን ማንም አያጠመውም፤ አላህ ያጠመመውን ማንም አያቀናውም። ከንግግር ሁሉ በላጩ የአላህ መጽሐፍ ነው፤ ከመመሪያ ሁሉ በላጩ የሙሐመድ መመሪያ ነው። ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓ ነው፤ ቢድዓ ሁሉ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ የእሳት ነው። ❨ሡነን ነሣኢ : መጽሐፍ 19፥ ሐዲስ 23❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍2
ስራ መስራት አትወድም?በማለዳ ተነስተህ መጣርና መድከሙ አስመርሮሀል?እንግዲያውስ ለአንተ እግዚአብሔር መፍትሄ አለው፦

“የዕለት ጒርስ ለማግኘት በመጣር፣ ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣ አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤ እርሱ ለሚወዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።”
— መዝሙር 127፥2 (አዲሱ መ.ት)

እንደ መጽሀፍ ቅዱስ መሠረት ለምድራዊ ኑሮ መድከምህ "ከንቱ" ነው። እግዚአብሔር ቢወድህ ኑሮ እንቅልፍ ጥሎ ያስተኛህ ነበር።

If it is said that it will be a response

"እግዚአብሔር ለሚወዳቸው ያለ ድካም አስተኝቶ ሲሳይ ይሰጣቸዋል ለማለት ነው" የሚል መልስ እንኳን ከተሰጠ የሚከተሉት እንቆቅሎሾች መብራራት አለባቸው፦

1/ መጽሀፍ ቅዱስ እራሱ መተኛትን ነቅፎ ስራን ደግሞ አበረታቶ ከገለጻቸው ሌሎች ምንባቦች ጋር መልዕክቱ ይጣረሳል። ለአብነት መጽሀፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦

“ሰብሉን በበጋ የሚሰበስብ ጠቢብ ልጅ ነው፤ በመከር ጊዜ የሚተኛ ግን ውርደት ይከተለዋል።”
— ምሳሌ 10፥5 (አዲሱ መ.ት)

በተመሳሳይ

“ሰነፍ እጆች ሰውን ያደኸያሉ፤ ትጉ እጆች ግን ብልጽግናን ያመጣሉ።”
— ምሳሌ 10፥4 (አዲሱ መ.ት)

2/ ለኑሮ መድከምና ንጹህ የልፋትን ዋጋ መመገብ በዚህ ደረጃ ከእግዚአብሔር ውዴታ ጋር በተቃርኖ የሚቀርብ ነው?ከንቱ ተደርጎ በፈጣሪ የሚናናቅስ ነው?

2/ እግዚአብሔርስ ቢሆን (በዘፍጥረት 3፥19) የሰው ልጅ በላቡ እንዲበላ ትዕዛዝ ማውረዱን ረስቶት ነው?ሰው በደነገገው መመሪያ መሠረት የሚያደርገውን ድካም እንደ ከንቱ የሚያየው?

(የሕያ ኢብኑ ኑህ)
ታቦት እና ጣዖት
እኛ ሙስሊሞች፦ "ታቦት ጣዖት ነው" አላልንም። ምክንያቱም ታቦት የጽላት ማስቀመጫ ሳጥን ነው።
ባይሆን የአገራችን የተዋሕዶ ክርስቲያኖች ናቸው፦ "ጣዖቱን ታቦት ነው" የሚሉን። ምክንያቱም አንድ ድንጋይ፣ ወርቅ፣ ብረት፣ እንጨት የጸጋ ይሁን የአምልኮ ስግደት ከተሰገደለት ያ ነገር ጣዖት ነው። ያንን ቅርጻ ቅርጽ ለምን የጸጋ ስግደት ትሰግዱለታላችሁ? ስንላቸው "ታቦት ነው" ይሉናል። ለታቦት የሰገደ ሰው በባይብል የለም። ለታቦት ስገዱ የሚል የለም። ሙሴ የሰራው ታቦት አንድ ሲሆን ጠፍቷል።
ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://t.me/Wahidcom
ጥያቄያችን
ክፍል 5
መስቀል መሳለም ሆነ በመስቀል ማሳለም የትኛው ነብይና ሃዋርያ አደረገ አድርጉስ አለ?
ከወሒድ ፅሁፍ ላይ Edit የተደረገ
ነብያዊ ሐዲስ
• ════•════•
۞ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم
قَالَ ” لَيَرِدَنَّ عَلَىَّ نَاسٌ مِنْ أَصْحَابِي الْحَوْضَ، حَتَّى عَرَفْتُهُمُ اخْتُلِجُوا دُونِي، فَأَقُولُ أَصْحَابِي. فَيَقُولُ لاَ تَدْرِي مَا أَحْدَثُوا بَعْدَكَ.
✴️ ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ ከባልደረቦቼ ጥቂት ወደ ሐውድ ፏፏቴዬ ይመጣሉ፤ ከዚያም እኔ አውቃቸዋለው፤ ከዚያም ከእኔ ይወገዳሉ፤ እኔም እንዲህ እላለው፦ “ባልደረቦቼ”፤ እርሱም እንዲህ ይላል፦ ከአንተ በኃላ በሃይማኖቱ አዲስ ነገር እንደሚጨምሩ አታውቅም።” ❨ቡኻሪ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 170)
ስለ ባይብል መበረዝ
●*●*●*●*●*️●*️●
۞ عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ يَا مَعْشَرَ الْمُسْلِمِينَ، كَيْفَ تَسْأَلُونَ أَهْلَ الْكِتَابِ، وَكِتَابُكُمُ الَّذِي أُنْزِلَ عَلَى نَبِيِّهِ صلى الله عليه وسلم أَحْدَثُ الأَخْبَارِ بِاللَّهِ، تَقْرَءُونَهُ لَمْ يُشَبْ، وَقَدْ حَدَّثَكُمُ اللَّهُ أَنَّ أَهْلَ الْكِتَابِ بَدَّلُوا مَا كَتَبَ اللَّهُ وَغَيَّرُوا بِأَيْدِيهِمُ الْكِتَابَ، فَقَالُوا هُوَ مِنْ عِنْدِ اللَّهِ، لِيَشْتَرُوا بِهِ ثَمَنًا قَلِيلاً أَفَلاَ يَنْهَاكُمْ مَا جَاءَكُمْ مِنَ الْعِلْمِ عَنْ مُسَاءَلَتِهِمْ، وَلاَ وَاللَّهِ مَا رَأَيْنَا مِنْهُمْ رَجُلاً قَطُّ يَسْأَلُكُمْ عَنِ الَّذِي أُنْزِلَ عَلَيْكُمْ.

➵ ኢብኑ አባስ ሲናገር፦ ሙስሊሞች ሆይ ለምን የመጽሐፉ ሰዎችን ትጠይቃላችሁ? በተመሳሳይ መጽሐፋችሁ ከአላህ ዘንድ ለነቢዩ የተወረደው ወቅታቂ ንግግርና የምትቀሩት እያለ? መጽሐፋ አልተበረዘምን? አላህ ለእናንተ የመጽሐፉ ሰዎች በእጆቻቸው በርዘው «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» እንደሚሉ አውርዷል። ❨ቡኻሪ መጽሐፍ 52, ሐዲስ 46
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13