አቡ ሩሐማ - Abu Ruhama
972 subscribers
784 photos
137 videos
22 files
911 links
➧«ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ»፡፡ (ማኢዳ፥3)
Download Telegram
የመጽሐፍ 'ቅዱስ' ግጭቶች
ክፍል 11
• ════•════•
11. ይሁዳ እየሱስን አሳልፎ ሲሰጠው ለምልክትነት ስሞት ነበርን?
📌 ስሞታል
➢‹‹አሳልፎ የሚሰጠውም፦የምስመውእርሱነው ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቷቸው ነበር።ወዲያውም ወደ ኢየሱስ ቀረበና፦መምህር ሆይ፥ሰላም ለአንተ ይሁን ብሎ ሳመው።"
❨ማቴዎስ 26፡48-49❩
• ════•════•
📌አልሳመውም(እየሱስ ራሱ ማንነቱን ገልጾላቸዋል)
➢‹‹ኢየሱስም፥የሚመጣበትን ሁሉ ዐውቆ ወጣና፦ማንን ትፈልጋላችኹ አላቸው።
የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ፦እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከነርሱ ጋራ ቆሞ ነበር።›› ❨ዮሐንስ 18፥4-5❩

۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍2🤣1
ሁለተኛ ኮርስ
፩:3 የጠፉ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሉምን?


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ
እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

قُلْ مَنْ أَنزَلَ الْكِتَابَ الَّذِي جَاءَ بِهِ مُوسَاٰ نُورًا وَهُدًى لِّلنَّاسِ ۖ تَجْعَلُونَهُ قَرَاطِيسَ تُبْدُونَهَا وَتُخْفُونَ كَثِيرًا ۖ وَعُلِّمْتُم مَّا لَمْ تَعْلَمُوا أَنتُمْ وَلَا آبَاؤُكُمْ ۖ قُلِ اللَّهُ ۖ ثُمَّ ذَرْهُمْ فِي خَوْضِهِمْ يَلْعَبُونَ

6፥61 እንዲህ በላቸው፡- «ያንን ብርሃን እና ለሰዎች መሪ ኾኖ *ሙሳ ያመጣውን መጽሐፍ ክፍልፍሎች የምታደርጉት ስትኾኑ ማን አወረደው? የወደዳችኋትን ትገልጿታላችሁ ብዙውንም ትደብቃላችሁ፤ እናንተም አባቶቻችሁም ያላወቃችሁትን ተስተማራችሁ

وَتُخْفُونَ كَثِيرًا
ብዙውንም ትደብቃላችሁ በሚለው ይሰመርበት ለሙሴ በተሰጠው መፅሐፍ እንዴት እንደደበቁትና የኢየሱስ መፅሐፍ እንዴት እንደደበቁት
እናያለን።

Dr. Stevan Davies: ዴቪስ ስለ ጠፉት የኢየሱስ አባባሎች በሰፊው የጻፈ የአዲስ ኪዳን ምሁር ነው። “የኢየሱስ የጠፉ አባባሎች” በተሰኘው መጽሐፋቸው በአዲስ ኪዳን ውስጥ ያልተካተቱ ነገር ግን በሌሎች ምንጮች ሊገኙ የሚችሉ ብዙ የኢየሱስ ንግግሮች እንዳሉ ተከራክሯል።

ለምሳሌ

ክርስቲያኖች በ 387 ድህረ-ልደት”AD” በካርቴጅ ጉባኤ ከወንጌላት የቶማስ፣ የይሁዳ፣ የጴጥሮስ፣ የያዕቆብ፣ የበርናባስ፣ የፊሊጶስ፣ የበርተሎሞዎስ፣ የመቅደላዊት ማርያም የተባሉትን ወንጌላትን ቀንሰዋል።

እነኚህ መፅሐፍቶች የት ይገኙ ይሁን?

“For I have not spoken of myself; but the Father which sent me, he gave me a commandment, what I should say, and what I should speak.”
  — John 12፥49 (KJV)

he gave me a commandment, በሚለው ይሰመርበት ትዕዛዝ የተሰጠው ከአባቱ መሆኑን "but the Father which sent me" ሲለን ለኢየሱስ የተሰጠው መፅሐፍ አሁን በእጅ የተፃፈ ሰይሆን አምላክ የሰጠው ነው።ለዚህም “የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ።”
  — ዮሐንስ 17፥8

“የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና" በሚለው ይሰመርበት የተሰጠው ቃል የሰው እጅ የልገባበት ስሆን ያንን ቃል ለሀዋሪያቶች ስሰጣቸው እነርሱም ተቀበሉት፥።

ኢየሱስ እየሰበከ የነበረው የተሰጠውን ወንጌል እንጂ ቧሃላ ማቴዎስ, ማርቆስ, ዩሀንስ, ሉቃስ የፀሐፉት ወንጌል አይደለም ምክንያቱም እነኚ ወንጌሎች ከኢየሱስ እርገት ቦሃላ ነው
በአዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉት አራቱ ወንጌላት የተጻፉት በተለያየ ጊዜ ሲሆን በሊቃውንት ዘንድ ግምታቸው ይለያያል። 

የማርቆስ ወንጌል፡-  በ65-70 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል፡-  በ80-90 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል፡-   በ80-85 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል፡-  በ90-100 ዓ.ም
በአንዳንድ ሙሁራኖች መሰረት እንዲህ ተብለው ይታመናል።

እኛም ይሄንን ተንተርሰን እየሱስ እያስተማረበት የነበረው ወንጌል ማርቆስ 1፥14-15 ላይ የተጠቀሰው
አሁን ያለውን የነ የማርቆስ የማቴዎስ የሉቃስ የዮሐንስ ሰይሆን የራሱ ከእግዚአብሔር የተቀበለውን ነው።
ለዚህም ነው እንዲህ የሚለው
"-- ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።”
  — ማርቆስ 1፥14-15
የኛ ጥያቄ የኢየሱስ ወንጌል ይት ይኑር ይሁን?

የጴጥሮስ ወንጌል
- የቶማስ ወንጌል
ወንጌል ማርያም
- ሚስጥራዊ የማርቆስ ወንጌል
- የእውነት ወንጌል
- የባርናባስ ወንጌል
እነኚህ ወንጌላት ይት ይኑሩ ይሁን?

የሙሴ መፅሐፍ
አይሁዳውያን ለሙሳ የተሰጠውን መጽሐፍ በመከፋፈል ኦሪት ዘፍጥረት፣ ኦሪት ዘጸአት፣ ኦሪት ዘኁልቁ፣ ኦሪት ዘሌዋውያን፣ ኦሪት ዘዳግም በማለት ከፋፍለውታል፤ እነርሱም የማይመቻቸውን አፓክራፋ ማለት ድብቅ በማለት በመቀነስ ደብቀውታል፤

የሙሴ መፅሐፍ ግን በአራት ተከፋፍለው አነበረም።
ምክንያቱም ለሙሴ እግዚአብሔር ፅፎ እንደሰጣው ዘጸአት 24፥12 ላይ ተፅፎላቸዋል

“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ወደ እኔ ወደ ተራራው ውጣ፥ በዚያም ሁን፤ እነርሱን ታስተምር ዘንድ እኔ የጻፍሁትን ሕግና ትእዛዝ የድንጋይም ጽላት እሰጥሃለሁ አለው።”
  — ዘጸአት 24፥12

ስማቸው በባይብል ውስጥ ተጠቅሰው አሁን የማይገኙ የጠፉ የባይብል ክፍሎች

ምሳሌ 1 የእግዚአብሔር የጦርነት መፅሐፍ

“ስለዚህ በእግዚአብሔር የጦርነት መጽሐፍ እንዲህ ተባለ፦ ዋሄብ በሱፋ፥ የአርኖንም ሸለቆች፥”
  — ዘኍልቁ 21፥14

ምሳሌ 2 የእስራኤል የነገሥታት የታሪክ መፅሐፍ

“የቀረውም የኢዮርብዓም ነገር፥ እንዴት እንደ ተዋጋ፥ እንዴትም እንደ ነገሠ፥ እነሆ፥ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎአል።”
  — 1ኛ ነገሥት 14፥19

ምሳሌ 3 የያሻር መፅሐፍ

“ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን እስኪበቀሉ ድረስ ፀሐይ ቆመ፥ ጨረቃም ዘገየ። ይህስ በያሻር መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ፥ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኰለም።”
  — ኢያሱ 10፥13

ምሳሌ 4 የአይሁዳ ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ

“የቀረውም የአብያም ነገር፥ ያደርገውም ሁሉ፥ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? በአብያምና በኢዮርብዓምም መካከል ሰልፍ ነበረ።”
  — 1ኛ ነገሥት 15፥7

ምሳሌ 5 የሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ

“የቀረውም የሰሎሞን ነገር፥ ያደረገውም ሁሉ፥ ጥበቡም፥ እነሆ፥ በሰሎሞን ታሪክ መጽሐፍ ተጽፎአል።”
  — 1ኛ ነገሥት 11፥41

ምሳሌ 6 በአዶ ራእይ የተጻፈ መፅሐፍ

“የቀረውም ፊተኛውና ኋለኛው የሰሎሞን ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ፥ በሴሎናዊውም በኦሒያ ትንቢት፥ ስለ ናባጥም ልጅ ስለ ኢዮርብዓም ባየው በባለ ራእዩ በአዶ ራእይ የተጻፈ አይደለምን?”
  — 2 ዜና 9፥29

ምሳሌ 7 በፋርስ ነገሥታት ታሪክ የተፃፈው መጽሐፍ

“የኃይሉና የብርታቱም ሥራ ሁሉ ንጉሡም እስከ ምን ድረስ እንዳከበረው የመርዶክዮስ ክብር ታላቅነት፥ በሜዶንና በፋርስ ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን?”
  — አስቴር 10፥2

ምሳሌ 8 ኢሳይያስ የፃፈው መፅሀፍ


“የቀረውንም የፊተኛውንና የኋለኛውን የዖዝያንን ነገር ነቢዩ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ጽፎታል።”
  — 2 ዜና 26፥22

ምሳሌ 9 የሳሙኤል መፅሐፍ

“ሳሙኤልም የመንግሥቱን ወግ ነገረ፥ በመጽሐፍም ጻፈው፤ በእግዚአብሔርም ፊት አኖረው። ሳሙኤልም ሕዝቡን ሁሉ ወደ እየቤታቸው አሰናበታቸው።”
  — 1ኛ ሳሙኤል 10፥25

ዶ/ር ባርት ዲ ኤርማን፡ ኤርማን የአዲስ ኪዳን ምሁር እና የጽሑፍ ሃያሲ ሲሆን ስለጠፉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በሰፊው ጽፏል። በ"Lost Christianities" በተሰኘው መጽሃፉ ውስጥ በእምነት መጀመሪያዎቹ መቶ ዘመናት ውስጥ ብዙ የተለያዩ የክርስትና ስሪቶች እንደነበሩ እና በመጨረሻም አዲስ ኪዳን የሆኑት ጽሑፎች ከትልቅ ታሪክ ውስጥ ትንሽ ክፍል ብቻ እንደሆኑ ይከራከራሉ.

ጥብቅ ማሳሰቢያ
እዚህ የምንለቃቸው ፁሁፎች
edit አድርጎ መጨመርም ሆነ መቀነስ የተከለከተ ነው።


📕 ወንድም አምዳላ ናሲር
የተኛውም አይነት  ሀሳብ ካለዎት
  👉ሀሳብ መስጫ👈
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
👇👇
https://t.me/comparativeRelgion/517
👍2
የመጽሐፍ 'ቅዱስ' አስተምህሮት
ለምጻም እርኩስ ነው።
• ════•════•
★ ለምጻም ሰው ነው ርኩስ ነው ካህኑ፦በርግጥ ርኩስ ነው ይለዋል ደዌው በራሱ ነው።የለምጽ ደዌ ያለበት ሰው ልብሱ የተቀደደ ይሁን፥ራሱም የተገለጠ ይሁን፥ከንፈሩንም ይሸፍን ርኩስ ርኩስ ነኝ ይበል። ደዌው ባለበት ዘመን ሁሉ ርኩስ ይሆናል እርሱ ርኩስ ነው ብቻውን ይቀመጣል መኖሪያውም ከሰፈር በውጭ ይሆናል።
📓ዘሌዋውያን 13፥44-46❩

۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍1👎1
ሑዘይፋህ ኢብኑል የማን ለአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አልኳቸው ይላሉ፦"እኛ በክፋት ውስጥ ነበርን። አላህ ይህንን ኸይር (ኢስላምን) አመጣልን። ከዚህ ኸይር በኋላ ክፋት ይኖራልን?" "አዎ" አሉ። "ከዚያስ ክፋት በኋላ መልካም ነገር ይኖራልን?" ስላቸው "አዎ" አሉ። "እንዴት ?" ስላቸው "ከኔ በኋላ በመመሪያዬ የማይመሩ፣ በሱናየም የማይጓዙ መሪዎች ይመጣሉ። በነሱም ላይ ልቦቻቸው የሸይጧን አካላቸው ደግሞ የሰው የሆኑ ሰዎች ይነሱባቸዋል" አሉ። ሑዘይፋ ረዐ "እንዲህ አይነት ሁኔታ ላይ ከደረስኩኝ ምን ላድርግ ?" ሲላቸው "አሚሩን ትሰማለህ፣ ለሱም ትታዘዛለህ፣ ጀርባህ ቢመታህም ገንዘብህን ቢነጥቅህም እንኳ" አሉ። (ሙስሊም ዘግበውታል:4891)
የመጽሐፍ ቅዱስ ግጭቶች
     ክፍል 12
• ════•════•➵
📌️ይሁዳ ኢየሱስን በመክዳቱ ያገኘውን ገንዘብ ምን አደረገው?
●*●*●*●*●*️●*️●
    በብሩ መሬት ገዛበት
➤‹‹ ይህም፡ሰው፡በዐመፅ፡ዋጋ፡መሬት፡ገዛ፥በግንባሩም፡ተደፍቶ፡ከመካከሉ፡ተሰነጠቀ፥አንዠቱም ዅሉ
ተዘረገፈ›› ❨የሀዋርያት ስራ 1፥18❩
.*.*.*.*.*.*.*.
  በቤተ መቅደስ ጣለው
➤ ‹‹ብሩንም፡በቤተ፡መቅደስ፡ጥሎ፡ኼደና፡ታንቆ፡ሞተ።›› ❨📓ማቴዎስ 27፡5❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍1
የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዋሰዋዊ ስህተቶች
  • ════•════•
   ️🔘 ሰው ወይም ሴት ️🔘
⓵.እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፦
ለእስራኤል ልጆች ንገራቸው፦ሰው ወይም ሴት ለእግዚአብሔር ራሱን የተለየ ያደርግ ዘንድ የናዝራዊነት ስእለት ቢሳል፦...(📓ዘኁልቁ 6፥2)
      ●*●*●*●*●*️●*️●
⓶.ሰው ወይም ሴት መናፍስትን ቢጠሩ ወይም ጠንቋዮች ቢሆኑ ፈጽመው ይገደሉ በድንጋይ ይውገሯቸው ደማቸው በላያቸው ነው።
(📓ዘሌዋውያን 20፥27)
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
1
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡
• ════•════•
️ሸይጣን በመጽሐፍ"ቅዱስ"እና ቁርዓን አስተምህሮት
📌️ የመጽሐፍ"ቅዱስ" አስተምህሮት
ሰይጣን እንደ የፈጣሪ ስልጣን ተፎካካሪ
➵ አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ!
አንተን በልብህ፦ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ።ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።
(📓ትንቢተ ኢሳያስ 14፡12-14)
●*●*●*●*●*️●*️●
️ የቁርዓን አስተምህሮት
📌️ ሸይጣን ተፎካካሪ ያልሆነ አመፀኛ ፍጥረት

قَالَ رَبِّ فَأَنظِرْنِي إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
➵«ጌታዬ ሆይ! እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝም» አለ፡፡ (📓ሷድ፥79)
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍1
▣ የነብያት ሃይማኖት ▣
•════•════•
ኢስላም
📌️ ኢስላም የነብያት ሁሉ ሃይማኖት ነው።
⓵. ለእናንተ ከሃይማኖት ያንን በእርሱ ኑሕን ያዘዘበትን ደነገገላችሁ፡፡ ያንንም ወዳንተ ያወረድነውን ያንንም በእርሱ ኢብራሂምን ሙሳንና ዒሳንም ያዘዝንበትን ሃይማኖትን በትክክል አቋቁሙ በእርሱም አትለያዩ ማለትን (ደነገግን)፡፡ በአጋሪዎቹ ላይ ያ ወደርሱ የምትጠራቸው ነገር ከበዳቸው፡፡ አላህ የሚሻውን ሰው ወደእርሱ (እምነት) ይመርጣል፡፡ የሚመለስንም ሰው ወደርሱ ይመራል፡፡ ❨ሹራ፥13❩

⓶. ነብዩ ሙሐመድ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦”ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ለዒሣ(ኢየሱስ) የማርያም ልጅ በዚህ ዓለም በመጨረሻይቱ ዓለም ቅርብ ነኝ።
ነቢያት ወንድማማቾች ናቸው እናቶቻቸው ይለያያሉ፤ ነገር ግን ሃይማኖታቸው ኢስላም አንድ ነው። ❨📙ቡኻሪ 60፥113❩
●*●*●*●*●*️●*️●
ክርስትና
ነብያት ክርስቲያን አልነበሩም። ክርስትና የተጀመረው ከኢየሱስ እርገት በኋላ ነውና።
በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ። ❨📗የሐዋርያት ስራ 11፥26❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
👍1
Forwarded from ሙሐመድ የንፅፅር ማህደር (𝑚𝑎𝑚¹)
ክፍል 9
የቁርኣንና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ሲተነተኑ…

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

      በዚህ ርዕስ የኢየሱስን የስቅለት ታሪክ ለየት ባለ መንገድ እናየዋለን። ቀደም ብለን ከምዕራፉ መግቢያ ጀምሮ ግልፅ ለማድረግ እንደሞከርነው የኢየሱስ የስቅለት ታሪክ ባልተረጋገጠ መረጃ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ከራሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ አንቀፆችን ጠቅሰን በዝርዝር አይተናል። እናም መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስን መሰቀል እንጅ መሞቱን አያረጋግጥም። የመሰቀሉም ታሪክ ቢሆን ሐዋርያቶች በዓይናቸው ያላዩትና ያልተጣራ ጭምጭምታ እንጅ እውነታ የለውም።

      በአንፃሩ ኢየሱስ መዳን ከመሰቀል ሳይሆን ህገ-ነቢያትን በመፈፀም እንደሚገኝ መናገሩን፣ አይሁዶች ሊሰቅሉት ባሰቡ ጊዜ አምላኩ ከሞት ያድነው ዘንድ አጥብቆ መለመኑ፣ ከሞት ተነሳ ከተባለ በኋላም መንፈሳዊ ሳይሆን ያልሞተ ፍጥረታዊ አካል መሆኑን ለሐዋርያቱ ማሳየቱ እና ሌሎቹም ክስተቶች ኢየሱስ ተሰቅሎ እንዳልሞተ እንደሚመሰክሩ ማስረጃዎችን አስደግፈን አይተናል።

      የእነዚህ ነገሮች ሁሉ ድምር ውጤት የሚያሳየን ታዲያ በምዕራፉ መግቢያ የጠቀስነውን የቁርኣን አንቀፅ ነው።

      ‹‹አልገደሉትም፥ አልሰቀሉትም፥ ግን ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ።››
      (ኒሳዕ 157)

      በእርግጥም መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስን ሞቶ መነሳት ማረጋገጥ ካልቻለ እውነታው በቁርኣን እንደተገለፀው ኢየሱስ ቀድሞም ‹‹አልተሰቀለም፤ አልሞተም›› ነበር ማለት ነው። ለዚህም ነው ቁርኣን ‹‹ጥርጣሬን ከመከተል በቀር በእርሱ ነገር (በመሰቀሉ) ምንም እውቀት የላቸውም›› በማለት እስካሁን ያየናቸውን ነጥቦች ሁሉ በአንድ ዓረፍ ነገር የገለፀው።

      እናም ቁርኣን የኢየሱስን አለመሰቀል ብሎም አለመገደል አስረግጦ ከተናገረና መጽሐፍ ቅዱስም ኢየሱስ ተሰቅሏል ይበል እንጅ በግልባጩ እንዳልሞተ ካረጋገጠ ሁለቱ መጽሐፎች አንድ አይነት ይዘት አላቸው ማለት ነው። ይህን የምለውም ኢየሱስ በመጽሐፍ ቅዱስ መሰቀሉ እንጅ ሞቶ መነሳቱ አለመረጋገጡ የትንሳኤ ሙታን ስብከትን ከንቱ ስለሚያርገው ከቁርአኑ ገለፃ ጋር አንድ ያደርጋቸዋል በማለት ነው።

      ይህንን መነሻ ሃሳብ ይዘን የመጽሐፍ ቅዱስን ተጨባጭ መረጃዎች ከቁርአኑ አንቀፆች ጋር ብናቀናጃቸው ምን ዓይነት ታሪክ ይሰጡን ይሆን? የሚለውን ቀጥለን ለማየት እንሞክር። ነገርግን ይህ የግል ዕይታዬ እንጅ የኢስልምና አቋም እንዳልሆነ ይታወቅልኝና ንድፈ ሃሳቡን እንስራው።

      ኢየሱስ ወንጌልን ማስተማር ከጀመረ ከጥቂት ዓመታት በኋላ እነሱ እንደፈለጉት ያልሆነላቸው አይሁዳውያን፡-

      ‹‹ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ።››
      (ማቴ 26፡4)

      ሲል ማቴዎስ ዘግቦታል። ይህንኑ ሃሳብ ቁርኣንም፡-

      ‹‹ሊገድሉህ ሲያስቡህ ጊዜ…›› (ማዒዳህ 119)

      በማለት አይሁዳውያን ኢየሱስን ሊገድሉት እንደተማከሩበት ይገልፃል። ከዚያም ኢየሱስም አምላኩ ከአይሁዳውያን ሴራ እንዲያድነው አጥብቆ ፀለዬ።

      ‹‹አባ አባት ሆይ፥ ሁሉ ይቻልሃል፤ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን አንተ የምትወደው እንጂ እኔ የምወደው አይሁን አለ።››
      (ማር 14፡36)

      ይህ በእንባና በለቅሶ የታጀበ ልመናውም ከአምላኩ ዘንድ ተሰማ። ፈጣሪም እንዲህ ሲል መለሰለት፡-

      ‹‹ዒሳ ሆይ! እኔ ወሳጅህ ወደ እኔም አንሽህ ነኝ። ከእነዚያ ከካዱት ሰዎች አጥሪህ ነኝ።››
      (ኢምራን 55)

      ወደ ዕብራውያን የተላከው መልዕክትም የኢየሱስ ፀሎት ተቀባይነት ማግኘቱን እንዲህ ሲል ገለፀ፡-

      ‹‹እርሱም በሥጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት።››
      (ዕብ 5፡7)

      ከዚያም አይሁዶች ሌሊት በጨለማ ሊይዙት መጡ። የሚደንቀው ነገር ሊይዙት የመጡት ሰዎች ኢየሱስን በአካል ለይተው አያውቁትም ነበርና አስቆርቱ ይሁዳ፡-

      ‹‹የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር።››
      (ማቴ 26፡48)

      ነገር ግን የፈጣሪ እቅድ በለጠና እቅዳቸው ሳይሳካላቸው ቀረ። በውድቅት ሌሊት የማያውቁትን ኢየሱስን አስረው ለመሄድ የመጡት ሰዎች የተሳሳተ ሰው ይዘው ሄዱ። እርሱንም በፍጥነት አዋክበው ሰቀሉት። ቁርኣን ይህንን ሲተርከው፡-

      ‹‹ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ።››
      (ኒሳዕ 157)

      በማለት ኢየሱስ መስሏቸው ሌላ ሰው በስህተት እንደሰቀሉ ማረጋገጫ ሰጠ።ኢየሱስም ሊይዙት ከመጡት አይሁዳውያን ከተሰወረ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ‹‹ተሰቀለ›› በተባለው ያልተጣራ ወሬ እንዳይወዛገቡና እንዳይጠራጠሩ ሊያረጋግጥላቸው አንድ ላይ በተሰበሰቡበት ሰዓት ተገልጦ፡-

      ‹‹እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።››
      (ሉቃ 24፡39)

      ሐዋርያቱም የኢየሱስን አካል ዳስሰው ሞቶ የተነሳ መንፈስ እንዳልሆነ አረጋገጡ። ከዚያ በኋላ ወደ አምላኩ አረገ። በዚህም ተዓምራዊ ስራ ኢየሱስ ከአይሁዶች ተንኮል ዳነ።

      ፈጣሪም በቁርአኑ እንዲህ ሲል የክስተቱን ድምዳሜ ገለፀልን፡-

      ‹‹አይሁዶች አደሙ፥ አላህም አድማቸውን መለሰባቸው፥ አላህም ከአድመኞች ሁሉ በላጭ ነው።››
      (ኢምራን 54)

      እንግዲህ ይህንን ይመስላል የሁለቱ መጽሐፎች ትርክት የጋራ ውጤት። እናም የጥናታችን መቋጫ ከላይ ከሰፈረው የቁርኣን አንቀፅ የዘለለ አይሆንም። አይሁዶች ኢየሱስን አልሰቀሉትምም፥ አልገደሉትምም። በክብር ወደ አምላኩ አረገ እንጂ። እናም መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስን ተሰቅሎ መሞት የማያረጋግጥ ከሆነ ትንሳኤ ሙታን የለም ማለት ነው። ትንሳኤ ሙታን ከሌለ ደግሞ ክርስትና የለም። ‹‹ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሳማ፤ ክርስቶስም ካልተነሳ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት።››
      ያለው ጳውሎስ በእርግጥም እውነት ነው።
---------------------------------------------------------------------------------------------
https://t.me/muhammed6964

ወሠላሙ ዐለይኩም
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
• ════•════•
ጅምላ ጭፍጨፋ
መጽሐፍ "ቅዱስ"
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦እስራኤል ከግብጽ በወጣ ጊዜ ዐማሌቅ በመንገድ እየተቃወመ ያደረገበትን እበቀላለሁ።
አሁንም ሄደህ ዐማሌቅን ምታ፥ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፥አትማራቸውም ወንዱንና ሴቱን ብላቴናውንና ሕፃኑን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን ግደል።
❨1ኛ ሳሙኤል 15፥2-3❩
●*●*●*●*●*️●*️●
ቁርዓን
مِنْ أَجْلِ ذَٰلِكَ كَتَبْنَا عَلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنَّهُ مَن قَتَلَ نَفْسًا بِغَيْرِ نَفْسٍ أَوْ فَسَادٍ فِي الْأَرْضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ النَّاسَ جَمِيعًا وَمَنْ أَحْيَاهَا فَكَأَنَّمَا أَحْيَا النَّاسَ جَمِيعًا
በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን፡፡
❨ማዒዳ:32❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
የእግዚአብሔር ጫማ­­︎
•════•════•
➾ መንፈሱም፡አነሣኝ፡ወደ፡ውስጠኛውም፡አደባባይ፡አገባኝ፤እንሆም፥የእግዚአብሔር፡ክብር፡መቅደሱን፡ ሞልቶት፡ነበር።በመቅደሱም፡ ኾኖ፡የሚናገረኝን፡ሰማኹ፥በአጠገቤም፡ሰው፡ቆሞ፡ነበር። እንዲህም፡አለኝ፦የሰው፡ልጅ፡ሆይ፥በእስራኤል፡ልጆች፡መካከል፡ለዘለዓለም፡የምቀመጥበት፡የዙፋኔ፡
ስፍራና፡የእግሬ፡ጫማ፡መረገጫ፡ይህ፡ነው።ዳግመኛም፡የእስራኤል፡ቤትና፡ነገሥታታቸው፡
በግልሙትናቸውና፡በከፍታዎቻቸው፡ባለው፡በነገሥታታቸው፡ሬሳ፡ቅዱስ፡ስሜን፡አያረክሱም፤
📓ዩሐንስ ራዕይ 43፥5-7❫
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
▣ ከዚህ ምን እንጠቀማለን? ▣
• ════•════•
ክፍል 1
❶.በእስጢፋኖስና በፈርዶናጥስ በአካይቆስም መምጣት ደስ ይለኛል፥እናንተ ስለሌላችኹ የጐደለኝን ፈጽመዋልና መንፈሴንና መንፈሳችኹን አሳርፈዋልና። እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን ዕወቋቸው። የእስያ አብያተ ክርስቲያናት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። አቂላና ጵርስቅላ በቤታቸው ካለች ቤተ ክርስቲያን ጋራ በጌታ እጅግ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። ወንድሞች ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። በተቀደሰ አሳሳም ርስ በርሳችኹ ሰላምታ ተሰጣጡ። እኔ ጳውሎስ ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ ጽፌያለኹ። (📙1ኛ ቆሮንቶስ 16፥17-21)

❷.በመቄዶንያም ሳልፍ ወደ እናንተ እመጣለኹ በመቄዶንያ አድርጌ ዐልፋለኹና
እናንተም ወደምኼድበት ወደ ማናቸውም ስፍራ በጕዞዬ እንድትረዱኝ ምናልባት በእናንተ ዘንድ እቈይ ወይም እከርም ይሆናል።
አሁን እግረ መንገዴን ሳልፍ ልጐበኛችኹ አልወድምና ጌታ ቢፈቅደው የሆነውን ዘመን በእናንተ ዘንድ ልሰነብት ተስፋ አደርጋለሁና።
በኤፌሶን ግን እስከ በዓለ ኀምሳ ድረስ እሰነብታለኹ። ሥራ የሞላበት ትልቅ በር ተከፍቶልኛልና፥ተቃዋሚዎችም ብዙ ናቸው።
ጢሞቴዎስም የመጣ እንደ ሆነ በእናንተ ዘንድ ያለፍርሀት እንዲኖር ተጠንቀቁ እንደ እኔ ደግሞ የጌታን ሥራ ይሠራልና እንግዲህ ማንም አይናቀው። ነገር ግን፥ከወንድሞቹ ጋራ እጠብቀዋለኹና፥ወደ እኔ ይመጣ ዘንድ በሰላም በጕዞው ርዱት።
ስለ ወንድማችን ስለ አጵሎስ ግን ከወንድሞቹ ጋራ ወደ እናንተ ሊኼድ እጅግ አድርጌ ለምኜው ነበር ዛሬም ለመምጣት ከቶ ፈቃድ አልነበረውም፥ሲመቸው ግን ይመጣል።
(📙1ኛ ቆሮንቶስ 16 ፥5-12)

❸.በቶሎ ወደ እኔ እንድትመጣ ትጋ፤ ዴማስ የአሁኑን ዓለም ወዶ ትቶኛልና፥ ወደ ተሰሎንቄም ሄዶአል፤ ቄርቂስም ወደ ገላትያ ቲቶም ወደ ድልማጥያ ሄደዋል፤ ሉቃስ ብቻ ከእኔ ጋር አለ። ማርቆስ ለአገልግሎት ብዙ ይጠቅመኛልና ይዘኸው ከአንተ ጋር አምጣው። ቲኪቆስን ግን ወደ ኤፌሶን ላክሁት። ስትመጣ በጢሮአዳ ከአክርጳ ዘንድ የተውሁትን በርኖሱንና መጻሕፍቱን ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ። ❨📙2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥9-13❩
Edit የሆነ ፅሁፍ ነው።
ጥያቄ ለክርስቲያኖች
▣ ከዚህ ምን እንጠቀማለን? ▣
•════•════•
ክፍል 2
️❶.ለጵርስቅላና ለአቂላ ለሄኔሲፎሩም ቤተ ሰዎች ሰላምታ አቅርብልኝ።
ኤርስጦስ በቆሮንቶስ ቀረ፥ጥሮፊሞስን ግን ታሞ በሚሊጢን ተውኹት። ከክረምት በፊት እንድትመጣ ትጋ።ኤውግሎስና ጱዴስ፥ሊኖስም ቅላውዲያም፥ወንድሞችም ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡልሃል።
(📙2ኛ ጢሞቴዎስ 4 ፥19-21)

️❷.ሌትና ቀን በልመናዬ ሳላቋርጥ ስለማስብኽ እንደ አባቶቼ አድርጌ በንጹሕ ኅሊና የማመልከውን እግዚአብሔርን አመሰግናለኹ
እንባኽን እያሰብኹ በደስታ እሞላ ዘንድ ላይኽ እናፍቃለኹ።
(📙2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥3-4)

❸.ነገር ግን፥ወንድሜንና ከእኔ ጋራ ዐብሮ ሠራተኛ ወታደርም የሚሆነውን፥የእናንተ ግን መልእክተኛ የሆነውና የሚያስፈልገኝን የሚያገለግለውን አፍሮዲጡን እንድልክላችኹ በግድ ዐስባለኹ
ዅላችኹን ይናፍቃልና፥እንደ ታመመም ስለ ሰማችኹ ይተክዛል።
በእውነት ታሞ ለሞት እንኳ ቀርቦ ነበርና ነገር ግን፥እግዚአብሔር ማረው፥ሐዘን በሐዘን ላይ እንዳይጨመርብኝ ለእኔ ደግሞ እንጂ ለርሱ ብቻ አይደለም።እንግዲህ እንደ ገና ስታዩት ደስ እንዲላችኹ ለኔም ሐዘኔ እንዲቃለል በብዙ ፍጥነት እልከዋለኹ።
(📙ፊልጵስዩስ 2 ፥25-28)
ኢየሱስና ‹‹ስድብ››
ደንቆሮ ብሎ የሚሳደብ የገሀነም ፍርድ ይገባዋል ይላል ኢየሱስ
۞‹‹እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥በወንድሙ፡ላይ፡የሚቈጣ፡ዅሉ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ወንድሙንም፡ጨርቃም፡
የሚለው፡ዅሉ፡የሸንጎ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ደንቈሮ፡የሚለውም፡ዅሉ፡የገሃነመ፡እሳት፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል።›› (ማቴዎስ 5፥22)
ነገርግን ኢየሱስ እራሱ ይህንን ስድብ ሲጠቀም እንመለከታለን፡፡
⓵.‹‹እናንተ፡ደንቈሮዎችና፡ዕውሮች፥ማናቸው፡ይበልጣል፧ወርቁ፡ነውን፧ወይስ፡ወርቁን፡የቀደሰው፡ቤተ፡ መቅደስ።›› (ማቴዎስ 23፥17)
⓶.‹‹እናንት ደንቆሮዎች፥ የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን?›› (ሉቃስ 11፥ 40)
ታዲያ አላህ ይጠብቀንና በኢየሱስ አገላለጽ መሰረት ኢየሱስ የገሀነም ፍርድ ይገባዋል ልንል ነውን?
(ምንጭ:-ከ100 በላይ የመጽሐፍ ቅዱስ ግጭቶች ፥ያህያ ኢብኑ ኑህ)
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡
• ════•════•
️ሸይጣን በመጽሐፍ"ቅዱስ"እና ቁርዓን አስተምህሮት
📌️ የመጽሐፍ"ቅዱስ" አስተምህሮት
ሰይጣን እንደ የፈጣሪ ስልጣን ተፎካካሪ
➵ "ሁሉን የሚገዛ ሰይጣን መጥቶ በአምላክ ፊት ቆሞ እንዲህ አለ እነሆ አብርሃም ልጁ ይስሐቅን ይወደዋል ከሁሉም ይልቅ እርሱ ደስ ያሰኘዋል በመሠዊያው ላይ መሥዋዕት አድርጎ ያቀርበው ዘንድ ንገረው።" (መጽሐፈ ኩፋሌ 14፥2)
➵"አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ!
አንተን በልብህ፦ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ።ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።"
(📓ትንቢተ ኢሳያስ 14፡12-14)
●*●*●*●*●*️●*️●
️ የቁርዓን አስተምህሮት
📌️ ሸይጣን የአላህ ተፎካካሪ ሳይሆን አመፀኛ ፍጥረት

قَالَ رَبِّ فَأَنظِرْنِي إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
➵«ጌታዬ ሆይ! እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝም» አለ፡፡ (📓ሷድ፥79)
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
⭕️ኃጢያት በክርስትና እና ኢስላም አስተምህሮ
▣ በክርስትና አስተምህሮ ▣
⓵.“በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።” ❨📘ሮሜ 5፥19❩
●*●*●*●*●*️●*️●

▣ በኢስላም አስተምህሮ ▣

وَأَن لَّيْسَ لِلْإِنسَانِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
⓵.ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡( 📙 ነጅም:39)
⓶. የተመራ ሰው የሚመራው ለራሱ ብቻ ነው፡፡ የተሳሳተም ሰው የሚሳሳተው (ጉዳቱ) በእርሷ ላይ ነው፡፡ ተሸካሚም (ነፍስ) የሌላይቱን ኃጢኣት አትሸከምም፡፡ መልዕክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም፡፡ ❨📓ኢስራ:15❩
۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞ ۞
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13
ጥያቄ ለክርስቲያኖች

በቁርኣን ውስጥ ዒሳ(ኢየሱስ) ከሰራቸው ተኣምራት መካከል አንዱ በህፃንነቱ  መናገሩ ነው።(ቁርኣን 19:27—34 ይመልከቱ)ነገር ግን በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ የምናገኘው የመጀመሪያው ተዓምር ውሃውን ወደ ወይን ጠጅ መቀየሩ ነው። (ዮሐ 2:1—11 ይመልከቱ )
በኦሪት ህግ መሰረት ዝሙት የሰራ ሰው ቅጣቱ  በድንጋይ ተወግሮ መገደል ነው። ይህ ከሆነ ማርያም (መርየም) አርግዛ ልጅ ስትወልድ ህዝቡ እንዴት ዝም አላት? ምን ብላ አስረድታ ነው  በመንፈስ ቅዱስ  አማካኝነት ማርገዟን ለአይሁዳውያን ያስረዳችው?  
በቁርኣን የተገለፀው የልጇ በተኣምር መናገር  ከዚህ ወንጀል እንዴት ነፃ እንዳደረጋት ትርጉም ይሰጣል።
Edit የተደረገ ፅሁፍ
👍1
ውዱዕ(ለአምልኮ የሚደረግ ትጥበት)
•════•════•
✺يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِذَا قُمْتُمْ إِلَى الصَّلَاةِ فَاغْسِلُوا وُجُوهَكُمْ وَأَيْدِيَكُمْ إِلَى الْمَرَافِقِ وَامْسَحُوا بِرُءُوسِكُمْ وَأَرْجُلَكُمْ إِلَى الْكَعْبَيْنِ ۚ

➵ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ወደ ሶላት በቆማችሁ (ለመቆም ባሰባችሁ) ጊዜ ፊቶቻችሁን፣ እጆቻችሁንም እስከ ክርኖች እጠቡ፡፡ ራሶቻችሁንም (በውሃ) አብሱ፡፡ እግሮቻችሁንም እስከ ቁርጭምጭሚቶች (እጠቡ)፡፡ (ማኢዳ፥6)
.*.*.*.*.*.*.*.
➵ እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አኖረ፥ለመታጠቢያም ውሃን ጨመረበት። በርሱም ሙሴና አሮን ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ታጠቡ። ወደመገናኛው ድንኳን በገቡ ጊዜ፥ወደ መሠዊያውም በቀረቡ ጊዜ ይታጠቡ ነበር።
❨ዘጸአት 40፥30-32❩

●የነብዩ ሙሴና ነብዩ አሮን ፈለግ (ለስግደት ትጥበትን የሚፈፅሙት) የሚከተሉት ሙስሊሞች ናቸውን ወይስ ክርስቲያኖች?
👌2
📌️ የመጽሐፍ ቅዱስ ህግጋት
• ════•════•
በክትን ለመጻተኛ(ምጽዋትን ለሚለምን) ስጥ ወይም ለእንግዶች ሽጡ

✺ አንተ፡ለአምላክኽ፡ለእግዚአብሔር፡የተቀደሰ፡ሕዝብ፡ነኽና፥የበከተውን፡ዅሉ፡አትብላ፤ይበላው፡ዘንድ፡ በአገርኽ፡ደጅ፡ለተቀመጠ፡መጻተኛ፡ትሰጠዋለኽ፥ወይም፡ለእንግዳ፡ትሸጠዋለኽ።የፍየሉን፡ጠቦት፡በእናቱ፡
ወተት፡አትቀቅል።❨📙️ኦሪት ዘዳግም 14፥21❩
●*●*●*●*●*️●*️●*️●
📌️ ቁርዓን
መልካምን እንጂ ከመጥፎ አትለግሱ

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِن طَيِّبَاتِ مَا كَسَبْتُمْ وَمِمَّا أَخْرَجْنَا لَكُم مِّنَ الْأَرْضِ ۖ وَلَا تَيَمَّمُوا الْخَبِيثَ مِنْهُ تُنفِقُونَ وَلَسْتُم بِآخِذِيهِ إِلَّا أَن تُغْمِضُوا فِيهِ ۚ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ حَمِيدٌ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ካፈራችሁትና ከዚያም ለእናንተ ከምድር ካወጣንላችሁ ከመልካሙ ለግሱ፡፡ መጥፎውንም (ለመስጠት) አታስቡ፡፡ በእርሱ ዓይኖቻችሁን ጨፍናችሁ እንጂ የማትወስዱት ስትኾኑ ከእርሱ (ከመጥፎው) ትሰጣላችሁን? አላህም ተብቃቂ ምስጉን መኾኑን ዕወቁ፡፡ ❨በቀራ፥267❩
●*●*●*●*●*️●*️●*️●
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/sunah13