> "አንድ (ሰው እንደ ተራራ የሚገዝፉ ወንጀሎችን ተሸክሞ የውመል ቂያማ ይመጣል፤ ነገር ግን ምላሱ አላህን በማውሳት (በመዘከሩ) የተነሳ ወንጀሎቹን ሲያፈራርሳቸው (ሲዘርዛቸው) ያገኘዋል።" (ኢብኑ ተይሚያህ)
> ይህን ዚክር ደጋግመው ይበሉ፦
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
⤴️ ለሚወዱት ሰው በማጋራት የዚክሩ ተቋዳሽ ያድርጓቸው።
ጥቆማ፦ የአላህን ዚክር ማብዛትና ኢስቲግፋር ማድረግ (ምሕረት መለመን) ምን ያህል ታላላቅ ወንጀሎችን እንኳ ሳይቀር እንደሚያብስ የታላቁ ዓሊም ኢብኑ ተይሚያህ ምክር ነው። በተለይም በዚህ ዘመን ልብ በጭንቀትና በወንጀል በከበደበት ጊዜ ይህን ማዘውተር ትልቅ እረፍት ይሰጣል።
> ይህን ዚክር ደጋግመው ይበሉ፦
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
✨ አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
⤴️ ለሚወዱት ሰው በማጋራት የዚክሩ ተቋዳሽ ያድርጓቸው።
ጥቆማ፦ የአላህን ዚክር ማብዛትና ኢስቲግፋር ማድረግ (ምሕረት መለመን) ምን ያህል ታላላቅ ወንጀሎችን እንኳ ሳይቀር እንደሚያብስ የታላቁ ዓሊም ኢብኑ ተይሚያህ ምክር ነው። በተለይም በዚህ ዘመን ልብ በጭንቀትና በወንጀል በከበደበት ጊዜ ይህን ማዘውተር ትልቅ እረፍት ይሰጣል።
❤22👍9
በኢማሙ አሕመድ እና በተማሪያቸው አል-መርሩዚ መካከል በትዳር ዙሪያ የተደረገ ድንቅ ውይይት!
● [መርሩዚ] እንዲህ አለ፦ አቡ አብደላህ (ኢማም አሕመድን) እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፦ "ነቢዩ ﷺ ሳይጋቡ መቆየትን (ምንኩስናን) ከልክለዋል። የነቢዩን ﷺ ፈለግ የጠላ ሰው እውነት ላይ አይደለም። የነቢዩን ባልደረቦች፣ የሙሃጅሮችንና የአንሷሮችን መንገድ የጠላ ሰው ደግሞ ከዲኑ ውስጥ ምንም ቦታ የለውም።"
* ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «እኔ በሌሎች ሕዝቦች ፊት በእናንተ ብዛት እፊካከራለሁና(እኩራለሁ።) በብዛት ውለዱ።»
* "ነቢዩ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) በዚያ ሁሉ ሀዘናቸው ውስጥ እንኳ አግብተዋል፣ ልጅም ተወልዶላቸዋል።"
* ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ሴቶች(ሚስቶች) ለእኔ (እንዲወደዱ) ተደርገዋል።»
* የነቢዩ ﷺ ባልደረቦችም ያገቡ ነበር።
● እኔም አልኩ፦ ሰዎች ግን "ገቢያቸንን በሐላል መንገድ የማግኛ መንገዱ ጠቧል።" ይላሉ።
* እሳቸውም ፦ "ነቢዩ ﷺ ምንም ለሌለው ሰው እንኳ በብረት በቀለበት (መህርነት) ድረዋል።"
* እኔም፦ በቁርኣን ሱራም ቢሆን (ይቻላል አይደል)? አልኩኝ።
እሳቸውም፦ "ይህንን ተወው" አሉ። "ትክክል (ሶሒሕ) አይደለም እንዴ?" አልኳቸው።
* እሳቸው፦ "ተወው አልኩህ! ከአንድ ነገር ስከለክልህ ተከለከል፤ አንድ ወንድ ሊያገባ ይገባል፤ ካለው (ይቀልባታል)፣ ከሌለው ደግሞ ይታገሳል።"አሉኝ።
● እኔም አልኩ፦ "እርስዎ፦ "የምቀልባት ካጣሁ እፈታታለሁ" ይሉኛል። እኔ ግን ስራ አግኝቼ መህሯ አንድ ሺህ ድርሀም ቢሆንብኝስ? እኔ ደግሞ አሁን ላይ ምንም የለኝም።
* ሳቁና እንዲህ አሉ፦ "በአምስት ድርሀም አግባ! ኢብኑ አል-ሙሰየብ (ታላቁ ታቢዒይ) ልጃቸውን በሁለት ድርሀም ድረዋል።"
● እኔም፦ ቤተሰቦቼ በአምስት ድርሀም እንዳገባ አይፈቅዱልኝም አልኳቸው።
* አሉ፦ "አሃ! አሁን የዱንያን ነገር አመጣህብኝ፤ ይህ ሌላ ጉዳይ ነው።"
● እኔም፦ ኢብራሂም ኢብኑ አድሀም (ታላቁ ዛሂድ) "የቤተሰብ ሐላፊ መሆን እንዴት ያስፈራል?!..." ማለታቸው ይወራል ስላቸው፤
* ንግግሬን ሳልጨርስ ጮኹብኝና እንዲህ አሉ፦ "በጎንዮሽ መንገዶች (ጠቃሚ ባልሆኑ ወሬዎች) ውስጥ ወደቅን። አላህ ዓፊያውን ይስጥህና—ሙሐመድ ﷺ እና ባልደረቦቻቸው ምን ላይ እንደነበሩ ተመልከት!"
● ቀጠልኩና ለአቡ አብደላህ እንዲህ አልኳቸው፦ -ፉደይል ኢብኑ ዒያድ "አንድ ሰው በልባችን ውስጥ (ትልቅ ቦታ) ይኖራል፤ ነገር ግን በማዕዱ ዙሪያ ሰዎች ሲሰበሰቡ (ቤተሰብ ሲያፈራ) ከልባችን ይወጣል።" ማለታቸው ይወራል?
* አሉ፦ "ከእነዚህ የጎንዮሽ ወሬዎች ተወኝ!አላልኩህም? እውቀት እንዲህ አይቀሰምም! አላህ አውፍ ይበልህና! —ሙሐመድ ﷺ እና ባልደረቦቻቸው ምን ላይ እንደነበሩ ተመልከት!"( እነሱን ተዋቸው!)
* ከዚያም ቀጠሉና፦ "እነሆ በዘመንህ ያሉ ደጋግ ሰዎች (ሷሊሖች) አግብተው እንጂ አታገኛቸውም።"
📚 ምንጭ፦ አል-ጃሚዕ ሊዑሉሚ አል-ኢማም አሕመድ (10/ 484 - 485)
● [መርሩዚ] እንዲህ አለ፦ አቡ አብደላህ (ኢማም አሕመድን) እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፦ "ነቢዩ ﷺ ሳይጋቡ መቆየትን (ምንኩስናን) ከልክለዋል። የነቢዩን ﷺ ፈለግ የጠላ ሰው እውነት ላይ አይደለም። የነቢዩን ባልደረቦች፣ የሙሃጅሮችንና የአንሷሮችን መንገድ የጠላ ሰው ደግሞ ከዲኑ ውስጥ ምንም ቦታ የለውም።"
* ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «እኔ በሌሎች ሕዝቦች ፊት በእናንተ ብዛት እፊካከራለሁና(እኩራለሁ።) በብዛት ውለዱ።»
* "ነቢዩ ያዕቆብ (ዐለይሂ ሰላም) በዚያ ሁሉ ሀዘናቸው ውስጥ እንኳ አግብተዋል፣ ልጅም ተወልዶላቸዋል።"
* ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ሴቶች(ሚስቶች) ለእኔ (እንዲወደዱ) ተደርገዋል።»
* የነቢዩ ﷺ ባልደረቦችም ያገቡ ነበር።
● እኔም አልኩ፦ ሰዎች ግን "ገቢያቸንን በሐላል መንገድ የማግኛ መንገዱ ጠቧል።" ይላሉ።
* እሳቸውም ፦ "ነቢዩ ﷺ ምንም ለሌለው ሰው እንኳ በብረት በቀለበት (መህርነት) ድረዋል።"
* እኔም፦ በቁርኣን ሱራም ቢሆን (ይቻላል አይደል)? አልኩኝ።
እሳቸውም፦ "ይህንን ተወው" አሉ። "ትክክል (ሶሒሕ) አይደለም እንዴ?" አልኳቸው።
* እሳቸው፦ "ተወው አልኩህ! ከአንድ ነገር ስከለክልህ ተከለከል፤ አንድ ወንድ ሊያገባ ይገባል፤ ካለው (ይቀልባታል)፣ ከሌለው ደግሞ ይታገሳል።"አሉኝ።
● እኔም አልኩ፦ "እርስዎ፦ "የምቀልባት ካጣሁ እፈታታለሁ" ይሉኛል። እኔ ግን ስራ አግኝቼ መህሯ አንድ ሺህ ድርሀም ቢሆንብኝስ? እኔ ደግሞ አሁን ላይ ምንም የለኝም።
* ሳቁና እንዲህ አሉ፦ "በአምስት ድርሀም አግባ! ኢብኑ አል-ሙሰየብ (ታላቁ ታቢዒይ) ልጃቸውን በሁለት ድርሀም ድረዋል።"
● እኔም፦ ቤተሰቦቼ በአምስት ድርሀም እንዳገባ አይፈቅዱልኝም አልኳቸው።
* አሉ፦ "አሃ! አሁን የዱንያን ነገር አመጣህብኝ፤ ይህ ሌላ ጉዳይ ነው።"
● እኔም፦ ኢብራሂም ኢብኑ አድሀም (ታላቁ ዛሂድ) "የቤተሰብ ሐላፊ መሆን እንዴት ያስፈራል?!..." ማለታቸው ይወራል ስላቸው፤
* ንግግሬን ሳልጨርስ ጮኹብኝና እንዲህ አሉ፦ "በጎንዮሽ መንገዶች (ጠቃሚ ባልሆኑ ወሬዎች) ውስጥ ወደቅን። አላህ ዓፊያውን ይስጥህና—ሙሐመድ ﷺ እና ባልደረቦቻቸው ምን ላይ እንደነበሩ ተመልከት!"
● ቀጠልኩና ለአቡ አብደላህ እንዲህ አልኳቸው፦ -ፉደይል ኢብኑ ዒያድ "አንድ ሰው በልባችን ውስጥ (ትልቅ ቦታ) ይኖራል፤ ነገር ግን በማዕዱ ዙሪያ ሰዎች ሲሰበሰቡ (ቤተሰብ ሲያፈራ) ከልባችን ይወጣል።" ማለታቸው ይወራል?
* አሉ፦ "ከእነዚህ የጎንዮሽ ወሬዎች ተወኝ!አላልኩህም? እውቀት እንዲህ አይቀሰምም! አላህ አውፍ ይበልህና! —ሙሐመድ ﷺ እና ባልደረቦቻቸው ምን ላይ እንደነበሩ ተመልከት!"( እነሱን ተዋቸው!)
* ከዚያም ቀጠሉና፦ "እነሆ በዘመንህ ያሉ ደጋግ ሰዎች (ሷሊሖች) አግብተው እንጂ አታገኛቸውም።"
📚 ምንጭ፦ አል-ጃሚዕ ሊዑሉሚ አል-ኢማም አሕመድ (10/ 484 - 485)
❤22👍7
ፈውስ ለሚፈልግ ሰው
ኢብን አል-ቀዪም አል-ጀውዚያ (አላህ ይዘንላቸውና) "መዳሪጁ ሳሊኪን" በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
> "እኔ በዚህ ረገድ (በሩቃ) በራሴም ሆነ በሌሎች ላይ አስደናቂ ነገሮችን ሞክሬያለሁ፤ በተለይም መካ (አላህ ያክብራትና) በነበርኩበት ጊዜ። እንቅስቃሴዬን ሊገቱ የሚቃረቡ በጣም አስቸጋሪ ህመሞች ያጋጥሙኝ ነበር፤ በተለይ በጦዋፍ ወቅትና በሌሎችም ጊዜያት። በዚያን ጊዜ ወደ ፋቲሃ ለመቅራት እፈጥንና ህመሙ ባለበት ቦታ ላይ እደባብሰዋለሁ፤ ያኔ ህመሙ ልክ እንደ ጠጠር ተንከባሎ እንደሚወድቅ (ወዲያው እንደሚጠፋ) ሆኖ ይሰማኝ ነበር። ይህንንም ደጋግሜ ሞክሬዋለሁ።
> እንዲሁም ከዘምዘም ውሃ በአንድ (ብርጭቆ) እወስድና ፋቲሃን ደጋግሜ እቀራበት ነበር፤ ከዚያም እጠጣዋለሁ። በዚህም ውስጥ በመድኃኒት የማላገኘውን ዓይነት ጥቅም እና ጥንካሬ አገኝ ነበር። ነገሩ ከዚያም በላይ ታላቅ ነው፤ ሆኖም (ውጤቱ) እንደ እምነት ጥንካሬና እንደ እርግጠኝነት (የቂን) ጥራት ይለያያል። አላህም ረዳታችን ነው።"
>
ኢብን አል-ቀዪም አል-ጀውዚያ (አላህ ይዘንላቸውና) "መዳሪጁ ሳሊኪን" በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
> "እኔ በዚህ ረገድ (በሩቃ) በራሴም ሆነ በሌሎች ላይ አስደናቂ ነገሮችን ሞክሬያለሁ፤ በተለይም መካ (አላህ ያክብራትና) በነበርኩበት ጊዜ። እንቅስቃሴዬን ሊገቱ የሚቃረቡ በጣም አስቸጋሪ ህመሞች ያጋጥሙኝ ነበር፤ በተለይ በጦዋፍ ወቅትና በሌሎችም ጊዜያት። በዚያን ጊዜ ወደ ፋቲሃ ለመቅራት እፈጥንና ህመሙ ባለበት ቦታ ላይ እደባብሰዋለሁ፤ ያኔ ህመሙ ልክ እንደ ጠጠር ተንከባሎ እንደሚወድቅ (ወዲያው እንደሚጠፋ) ሆኖ ይሰማኝ ነበር። ይህንንም ደጋግሜ ሞክሬዋለሁ።
> እንዲሁም ከዘምዘም ውሃ በአንድ (ብርጭቆ) እወስድና ፋቲሃን ደጋግሜ እቀራበት ነበር፤ ከዚያም እጠጣዋለሁ። በዚህም ውስጥ በመድኃኒት የማላገኘውን ዓይነት ጥቅም እና ጥንካሬ አገኝ ነበር። ነገሩ ከዚያም በላይ ታላቅ ነው፤ ሆኖም (ውጤቱ) እንደ እምነት ጥንካሬና እንደ እርግጠኝነት (የቂን) ጥራት ይለያያል። አላህም ረዳታችን ነው።"
>
👍18❤8
ኒካሕ(ጋብቻ )የሸይጣንን ተንኮል ለመመከት ይረዳል።
ኢብን ተይሚያ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦
○ "ላጤ መሆን የሸይጣንን ተንኮል ለመመከት፣ ዒልምን ለመቅሰም እና አላህን ለመገዛት የበለጠ ያግዛል ተብሎ የሚታሰበው፦
ይልቁንም ላጤ አለመሆን (ማግባት) የሸይጣንን ተንኮል ለመመከት የበለጠ ያግዛል።"
📚መጅሙዕ አል-ፈታዋ (31/ 63)
ኢብን ተይሚያ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦
○ "ላጤ መሆን የሸይጣንን ተንኮል ለመመከት፣ ዒልምን ለመቅሰም እና አላህን ለመገዛት የበለጠ ያግዛል ተብሎ የሚታሰበው፦
የሸሪዓን ድንጋጌና ተጨባጭ ሁኔታን የሚቃረን ስህተት ነው።
ይልቁንም ላጤ አለመሆን (ማግባት) የሸይጣንን ተንኮል ለመመከት የበለጠ ያግዛል።"
📚መጅሙዕ አል-ፈታዋ (31/ 63)
❤14
ዩኑስ (ዐለይሂ ሰላም) ከዓሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ እንዲወጡ ምክንያት የሆነው ዚክር የትኛው ነው?
Anonymous Poll
3%
ሱብሃነላህ ወቢሃምዲሂ
3%
አስተግፊሩላህ አል-ዐዚም ወአቱቡ ኢለይህ
94%
ላ ኢላሀ ኢላ አንተ ሱብሃነከ ኢኒ ኩንቱ ሚነዝ-ዟሊሚን
❤10
ታላቅ የዚክር ስጦታ !
"ወደ መኝታህ በምትሄድበት ጊዜ (ከመተኛትሀ በፊት)፦
«
>
ያለ ሰው፤ ወንጀሎቹ የባሕር አረፋ ያህል ቢሆኑ እንኳ ይማሩለታል።"
>
የሐዲሡ ደረጃ
📚፦ ሐዲሡ ሶሒሕ (ትክክለኛ) ነው።
>
"ወደ መኝታህ በምትሄድበት ጊዜ (ከመተኛትሀ በፊት)፦
«
ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ፣ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር። ላ ሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላሂል ዓሊዪል ዓዚም፤ ሱብሐነላህ፣ ወልሐምዱሊላህ፣ ወላ ኢላሀ ኢለላህ፣ ወላሁ አክበር።"
>
ያለ ሰው፤ ወንጀሎቹ የባሕር አረፋ ያህል ቢሆኑ እንኳ ይማሩለታል።"
>
የሐዲሡ ደረጃ
📚፦ ሐዲሡ ሶሒሕ (ትክክለኛ) ነው።
>
❤19👍16
አሰላሙ አለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ፤
🌷ሰባሑል ኸይር!
የዕለቱ መልእክት
ከዓብደላህ ኢብኑ አል-ሐሪስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተወራው እንዲህ ብለዋል፦ "
ዛሬ በዕለት ተዕለት ውሎህ በተለይም ሰዎች ዘንድ መጀመሪያ ስትገናኝ ፈገግታን በተግባር ለመፈፀም ሞክር።
ፈገግታና የፊትህ ብሩህነት በሰዎች መካከል ባለው ግንኙነት ላይ የሚያመጣውን ለውጥና ተፅዕኖ ተመልከት።
በሥነ-ምግባር ከሰው ሁሉ በላጭ የሆኑትን ውድ ነቢይህን (ﷺ) ለመምሰል ጥረት አድርግ።
🌷ሰባሑል ኸይር!
የዕለቱ መልእክት
ከዓብደላህ ኢብኑ አል-ሐሪስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተወራው እንዲህ ብለዋል፦ "
ከአላህ መልክተኛ (ﷺ) በላይ ፈገግታ የሚያበዛ አንድም ሰው አይቼ አላውቅም።"
ዛሬ በዕለት ተዕለት ውሎህ በተለይም ሰዎች ዘንድ መጀመሪያ ስትገናኝ ፈገግታን በተግባር ለመፈፀም ሞክር።
ፈገግታና የፊትህ ብሩህነት በሰዎች መካከል ባለው ግንኙነት ላይ የሚያመጣውን ለውጥና ተፅዕኖ ተመልከት።
በሥነ-ምግባር ከሰው ሁሉ በላጭ የሆኑትን ውድ ነቢይህን (ﷺ) ለመምሰል ጥረት አድርግ።
❤14👍14
📢 የደርስ መቀጠል ማስታወቂያ!
በተባረከው የረመዳን ወር ምክንያት ተቋርጠው የነበሩትና በየመሳጂዱ ሲሰጡ የነበሩት ዱሮሶች፤ አላህ ፈቃዱ ከሆነ ከነገ (ረቡዕ) ጀምሮ በነበራቸው ፕሮግራም መሠረት የሚቀጥሉ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን።
የዒልም ጉዟችንን በንቃት እንድንቀጥል አላህ ይርዳን።
>
ትምህርቱን ለሌሎችም በማጋራት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
🌐 t.me/sultan_54
በተባረከው የረመዳን ወር ምክንያት ተቋርጠው የነበሩትና በየመሳጂዱ ሲሰጡ የነበሩት ዱሮሶች፤ አላህ ፈቃዱ ከሆነ ከነገ (ረቡዕ) ጀምሮ በነበራቸው ፕሮግራም መሠረት የሚቀጥሉ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን።
የዒልም ጉዟችንን በንቃት እንድንቀጥል አላህ ይርዳን።
>
ትምህርቱን ለሌሎችም በማጋራት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
🌐 t.me/sultan_54
Telegram
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
👍10❤5
* ተስፋ የተሰጠው ማን ነው?
> "ከእናንተም መካከል (ያልተጋቡትን)፣ ከወንዶች ባሮቻችሁና ከሴቶች ባሮቻችሁም ሳሊሆች የሆኑትን አጋቡ፤ ድሆች ቢሆኑ አላህ ከችሮታው ያበለጽጋቸዋል፤ አላህም ችሮታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።" (አን-ኑር: 32)
>
በጥልቅ ዕውቀታቸው የሚታወቁት ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሺንቂጢ (ረሒመሁላህ)
በታዋቂው የተፍሲር መጽሐፋቸው "አድዋኡል በያን" ላይ እንዲህ ይላሉ፦
"አላህ ሀብታም እንደሚያደርገው ቃል የገባለት ፣ በትዳሩ የአላህን ታዛዥነት የሚፈልግ (ዓላማው አላህን መታዘዝ የሆነ) ነው። ይህም አይኑን በመስበር (ከሐራም በመጠበቅ) እና ብልቱን በመጠበቅ በኩል አላህን ለመገዛት እገዛን የፈለገ ሰው ነው።"
"ይህም ነቢዩ (ﷺ) በትክክለኛው ሐዲሥ እንዲህ ብለው እንደገለጹት ነው፦ 'እናንተ ወጣቶች ሆይ! ከእናንተ መካከል የትዳርን ጣጣ የሚችል ያግባ፤ እርሱ(ማግባት) ለዓይን ይበልጥ ሰባሪ (ከሐራም ጠባቂ)፣ ለብልትም ይበልጥ ጠባቂ ነውና...'"
የጋብቻው ዓላማ አይንን በመስበርና ብልትን በመጠበቅ አላህን መታዘዝ ከሆነ፣ የመበልጸግ (የሀብታምነት) ቃል ኪዳኑ የተመሰረተው በዚህ ተግባር አላህን በመታዘዝ ላይ ነው።"
📚 ምንጭ፦ አድዋኡል በያን (6/243)
> "ከእናንተም መካከል (ያልተጋቡትን)፣ ከወንዶች ባሮቻችሁና ከሴቶች ባሮቻችሁም ሳሊሆች የሆኑትን አጋቡ፤ ድሆች ቢሆኑ አላህ ከችሮታው ያበለጽጋቸዋል፤ አላህም ችሮታው ሰፊ ዐዋቂ ነው።" (አን-ኑር: 32)
>
በጥልቅ ዕውቀታቸው የሚታወቁት ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሺንቂጢ (ረሒመሁላህ)
በታዋቂው የተፍሲር መጽሐፋቸው "አድዋኡል በያን" ላይ እንዲህ ይላሉ፦
"አላህ ሀብታም እንደሚያደርገው ቃል የገባለት ፣ በትዳሩ የአላህን ታዛዥነት የሚፈልግ (ዓላማው አላህን መታዘዝ የሆነ) ነው። ይህም አይኑን በመስበር (ከሐራም በመጠበቅ) እና ብልቱን በመጠበቅ በኩል አላህን ለመገዛት እገዛን የፈለገ ሰው ነው።"
"ይህም ነቢዩ (ﷺ) በትክክለኛው ሐዲሥ እንዲህ ብለው እንደገለጹት ነው፦ 'እናንተ ወጣቶች ሆይ! ከእናንተ መካከል የትዳርን ጣጣ የሚችል ያግባ፤ እርሱ(ማግባት) ለዓይን ይበልጥ ሰባሪ (ከሐራም ጠባቂ)፣ ለብልትም ይበልጥ ጠባቂ ነውና...'"
የጋብቻው ዓላማ አይንን በመስበርና ብልትን በመጠበቅ አላህን መታዘዝ ከሆነ፣ የመበልጸግ (የሀብታምነት) ቃል ኪዳኑ የተመሰረተው በዚህ ተግባር አላህን በመታዘዝ ላይ ነው።"
📚 ምንጭ፦ አድዋኡል በያን (6/243)
❤17
*أسأل الله أن يحفظكم من كل حاسد،*
*وأن يكفيكم شرّ كل حاقد،*
*وأن يُبعد عنكم كل منافق،*
*وأن يصرف عنكم من يتربّص بكم*
💕🤲🏼💕
*وأن يكفيكم شرّ كل حاقد،*
*وأن يُبعد عنكم كل منافق،*
*وأن يصرف عنكم من يتربّص بكم*
💕🤲🏼💕
❤15🥰10👌2
«ዲኑንና ሥነ-ምግባሩን የምትወዱት (የምትመርጡት) ሰው ለጋብቻ ከጠየቃችሁ ዳሩት፤ ይህን ካላደረጋችሁ በምድር ላይ ፈተናና ሰፊ ጥፋት ይሆናል» የሚለውን ሐዲሥ አስመልክቶ፦
መዝሀር አድ’ዲን አዝ’ዘይዳኒ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦
● “ከእናንተ መካከል አንዱ ከልጆቻችሁ ወይም ከቅርብ ዘመዶቻችሁ አንዷን እንዲያገባ ቢጠይቃችሁ፤ ተመልከቱ፡- ሳሊህ ሙስሊምና መልካም ሥነ-ምግባር ያለው ከሆነ ዳሩት።
⏎ ምክንያቱም እናንተ ለቅርብ ዘመዶቻችሁ ሴቶች፣ የዱንያ ሰዎች እንደሚፈልጉት ዓይነት የታወቀ የሀብትና የሥልጣን ባለቤት ካልሆነ በቀር አንድርም ካላችሁ፤ አብዛኞቹ ሴቶቻችሁ ያለ ባል፣ አብዛኞቹ ወንዶችም ያለ ሚስት ይቀራሉ።
⏎ በዚህ ጊዜ ወንዶች ወደ ሴቶች፣ ሴቶችም ወደ ወንዶች ያዘነብላሉ፤ ዝሙትም ይበዛል። በሴቶቻቸው ላይ በሚሰማው የዝሙት ወሬ ምክንያትም ለወላጆችና ለፍተው ላሳደጉ ውርደት ይከተላቸዋል።
⏎ ምናልባትም በሴቶቻቸው ላይ ስለተወራው የዝሙት ወሬ በሰሙት ነገር ቅናት አሸንፏቸው ሴቶቻቸውን ሊገድሉ ይችላሉ፤ እንዲሁም እነዚያን ለዝሙት የፈለጓቸውን ወንዶችም ይገድላሉ። ይህ ሁሉ ሰፊ ጥፋትና ትልቅ ፈተና ነው።
📚ምንጭ፦ አል-መፋቲሕ ፊ ሸርሒል መሳቢሕ (4/13)
መዝሀር አድ’ዲን አዝ’ዘይዳኒ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦
● “ከእናንተ መካከል አንዱ ከልጆቻችሁ ወይም ከቅርብ ዘመዶቻችሁ አንዷን እንዲያገባ ቢጠይቃችሁ፤ ተመልከቱ፡- ሳሊህ ሙስሊምና መልካም ሥነ-ምግባር ያለው ከሆነ ዳሩት።
⏎ ምክንያቱም እናንተ ለቅርብ ዘመዶቻችሁ ሴቶች፣ የዱንያ ሰዎች እንደሚፈልጉት ዓይነት የታወቀ የሀብትና የሥልጣን ባለቤት ካልሆነ በቀር አንድርም ካላችሁ፤ አብዛኞቹ ሴቶቻችሁ ያለ ባል፣ አብዛኞቹ ወንዶችም ያለ ሚስት ይቀራሉ።
⏎ በዚህ ጊዜ ወንዶች ወደ ሴቶች፣ ሴቶችም ወደ ወንዶች ያዘነብላሉ፤ ዝሙትም ይበዛል። በሴቶቻቸው ላይ በሚሰማው የዝሙት ወሬ ምክንያትም ለወላጆችና ለፍተው ላሳደጉ ውርደት ይከተላቸዋል።
⏎ ምናልባትም በሴቶቻቸው ላይ ስለተወራው የዝሙት ወሬ በሰሙት ነገር ቅናት አሸንፏቸው ሴቶቻቸውን ሊገድሉ ይችላሉ፤ እንዲሁም እነዚያን ለዝሙት የፈለጓቸውን ወንዶችም ይገድላሉ። ይህ ሁሉ ሰፊ ጥፋትና ትልቅ ፈተና ነው።
📚ምንጭ፦ አል-መፋቲሕ ፊ ሸርሒል መሳቢሕ (4/13)
👍9❤2🥰1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከኢብኑል ቀይም አልጀውዚያ "አዳእ ወአድ-ደዋእ" ከተሰኘው መጽሐፍ የተወሰደ
● አቡ ደርዳእ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ይሉ ነበር፦
"በቂያማ ቀን 'አቡ ደርዳእ ሆይ! አውቀህ ነበር፤ ታዲያ ባወከው ነገር ላይ ምን ሠራህበት?' ተብሎ መጠየቅን ያህል በራሴ ላይ የምፈራው ከባድ ነገር የለም።"
● ኢብኑ አቢ ሙለይካ እንዲህ ብለዋል፦
"ከነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦች መካከል ሰላሳዎቹን አግኝቻለሁ፤ ሁሉም በራሳቸው ላይ ንፍቅናን ይፈሩ ነበር። ከእነርሱ መካከል 'ኢማኔ እንደ ጅብሪልና ሚካኤል ኢማን ነው' የሚል አንድም ሰው የለም።"
● ቡኻሪ በሶሒሃቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
"ባብ”
« አማኝ (ሙእሚን) ሳያውቀው ሥራው እንዳይበላሽ (እንዳይጠፋ) ስለመፍራቱ።»
● አቡ ደርዳእ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ይሉ ነበር፦
"በቂያማ ቀን 'አቡ ደርዳእ ሆይ! አውቀህ ነበር፤ ታዲያ ባወከው ነገር ላይ ምን ሠራህበት?' ተብሎ መጠየቅን ያህል በራሴ ላይ የምፈራው ከባድ ነገር የለም።"
● ኢብኑ አቢ ሙለይካ እንዲህ ብለዋል፦
"ከነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦች መካከል ሰላሳዎቹን አግኝቻለሁ፤ ሁሉም በራሳቸው ላይ ንፍቅናን ይፈሩ ነበር። ከእነርሱ መካከል 'ኢማኔ እንደ ጅብሪልና ሚካኤል ኢማን ነው' የሚል አንድም ሰው የለም።"
● ቡኻሪ በሶሒሃቸው ላይ እንዲህ ብለዋል፦
"ባብ”
« አማኝ (ሙእሚን) ሳያውቀው ሥራው እንዳይበላሽ (እንዳይጠፋ) ስለመፍራቱ።»
❤17
ሸኽ አልባኒ - አላህ ይዘንላቸውና - ስለ ራሳቸው እንዲህ ይላሉ፦
> "ገና በወጣትነቴ የሰዓት ጥገና ሙያን እንድማር መመራቴ ከአላህ ስኬትና ችሮታ ነው። ይህም የሆነው ሙያው ነጻ በመሆኑና በዒልመ አል–ሐዲስ ትምህርት ላይ ለማያደርገው ጥረት እንቅፋት ስለማይሆንብኝ ነው። ከማክሰኞና ከጁምዓ በስተቀር በየቀኑ ለሥራው የምመድበው ሦስት ሰዓታትን ብቻ ነበር። ይህ የጊዜ መጠን ለእኔ፣ ለቤተሰቦቼና ለልጆቼ የሚያስፈልገንን መሠረታዊ ፍላጎት በበቂ ሁኔታ እንድናገኝ ያስችለኛል - ይህም ወሳኝ ነጥብ ነው። ቀሪውን ጊዜዬን ደግሞ ሸሪዓዊ እውቀትን በመፈለግ፣ ኪታቦችን በማዘጋጀትና የሐዲስ መጻሕፍትን በማጥናት፣ በተለይም በዛሂሪያ መጻሕፍት ቤት የሚገኙ በእጅ የተፃፉ(መኽጡጣት) የጥንት ጽሑፎችን በመመርመር አሳልፈዋለሁ።"
>
> "ገና በወጣትነቴ የሰዓት ጥገና ሙያን እንድማር መመራቴ ከአላህ ስኬትና ችሮታ ነው። ይህም የሆነው ሙያው ነጻ በመሆኑና በዒልመ አል–ሐዲስ ትምህርት ላይ ለማያደርገው ጥረት እንቅፋት ስለማይሆንብኝ ነው። ከማክሰኞና ከጁምዓ በስተቀር በየቀኑ ለሥራው የምመድበው ሦስት ሰዓታትን ብቻ ነበር። ይህ የጊዜ መጠን ለእኔ፣ ለቤተሰቦቼና ለልጆቼ የሚያስፈልገንን መሠረታዊ ፍላጎት በበቂ ሁኔታ እንድናገኝ ያስችለኛል - ይህም ወሳኝ ነጥብ ነው። ቀሪውን ጊዜዬን ደግሞ ሸሪዓዊ እውቀትን በመፈለግ፣ ኪታቦችን በማዘጋጀትና የሐዲስ መጻሕፍትን በማጥናት፣ በተለይም በዛሂሪያ መጻሕፍት ቤት የሚገኙ በእጅ የተፃፉ(መኽጡጣት) የጥንት ጽሑፎችን በመመርመር አሳልፈዋለሁ።"
>
❤39👍15👌6
ከትዳር ጋር በተያያዘ ከሰለፎች የተገኙ ዘገባዎች
1. ከአቡ ኢስሐቅ የተገኘ ዘገባ፡
ወደ እሳቸው (ወደ አንድ ታላቅ ዓሊም) ገባሁ፤ እርሳቸውም እንዲህ አሉኝ፦
* «ቁርአንን በሙሉ (ሐፍዘሃል)?» እኔም፦ «አዎ፣ ለአላህ ምስጋና ይሁንና» አልኩ።
* «ሐጅ አድርገሃል?» አሉኝ። እኔም፦ «አዎ» አልኩ።
* «አግብተሃል?» አሉኝ። እኔም፦ «አይ» አልኩ።
* እሳቸውም እንዲህ አሉ፦ «ታዲያ ምን ይከለክልሃል? ዓብዱላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦ **‹
ጣዉስ እንዲህ አሉኝ፦
«ወይ ታገባለህ፣ አሊያም ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ለአቢ ዘዋኢድ ያሉትን እልሃለሁ፦ **‹
3. ከሙንዚር የተገኘ ዘገባ፡
ወህብ ቢን ሙነቢህ እንዲህ ሲሉ ሰማሁ፦
«**
የላጤ (ያላገባ ሰው) ምሳሌ፤ በበረሃ ውስጥ እንዳለች ዛፍ ነው፤ ነፋስ ወደዚህና ወደዚያ ያወዛውዛታል።**»
4. ከአምር ኢቢኑ ዲናር የተገኘ ዘገባ፡
ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከነቢዩ ﷺ ሞት በኋላ ላለማግባት አስበው ነበር። በዚህ ጊዜ (እህታቸው) ሐፍሳ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለቻቸው፦
«**
📚*ምንጭ፡ ሙሰነፍ ኢብን አቢ ሸይባ (10382 - 10388)*
1. ከአቡ ኢስሐቅ የተገኘ ዘገባ፡
ወደ እሳቸው (ወደ አንድ ታላቅ ዓሊም) ገባሁ፤ እርሳቸውም እንዲህ አሉኝ፦
* «ቁርአንን በሙሉ (ሐፍዘሃል)?» እኔም፦ «አዎ፣ ለአላህ ምስጋና ይሁንና» አልኩ።
* «ሐጅ አድርገሃል?» አሉኝ። እኔም፦ «አዎ» አልኩ።
* «አግብተሃል?» አሉኝ። እኔም፦ «አይ» አልኩ።
* እሳቸውም እንዲህ አሉ፦ «ታዲያ ምን ይከለክልሃል? ዓብዱላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦ **‹
ከዚህች ዓለም የቀረው አንድ ቀን ብቻ ቢሆን እንኳ፣ እዚያች ቀን ላይ ሚስት እንዲኖረኝ እወዳለሁ።›**»2. ከኢብራሂም ቢን መይሰራ የተገኘ ዘገባ፡
ጣዉስ እንዲህ አሉኝ፦
«ወይ ታገባለህ፣ አሊያም ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ለአቢ ዘዋኢድ ያሉትን እልሃለሁ፦ **‹
ከጋብቻ የሚከለክልህ ወይ ደካማነት (አቅም ማጣት) ነው፣ አሊያም አመጸኝነት (ፋጅር መሆን) ነው።›**»
3. ከሙንዚር የተገኘ ዘገባ፡
ወህብ ቢን ሙነቢህ እንዲህ ሲሉ ሰማሁ፦
«**
የላጤ (ያላገባ ሰው) ምሳሌ፤ በበረሃ ውስጥ እንዳለች ዛፍ ነው፤ ነፋስ ወደዚህና ወደዚያ ያወዛውዛታል።**»
4. ከአምር ኢቢኑ ዲናር የተገኘ ዘገባ፡
ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከነቢዩ ﷺ ሞት በኋላ ላለማግባት አስበው ነበር። በዚህ ጊዜ (እህታቸው) ሐፍሳ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለቻቸው፦
«**
ወንድሜ ሆይ! አግባ፤ ልጅ ተወልዶልህ (በሕፃንነቱ) ቢሞት (ለአኺራ ስንቅ) ሸፋዓ ይሆንሃል፤ በሕይወት ቢቆይ ደግሞ ዱዓ ያደርግልሃል።**»
📚*ምንጭ፡ ሙሰነፍ ኢብን አቢ ሸይባ (10382 - 10388)*
❤10👍5
የኪታብ ጥቆማ!
### ስለ አህሉሱናህ ወልጀመዓ ዓቂዳ በዝርዝር የሚያብራሩ ምርጥ መጽሐፍት
አሽ–ሸይኽ ዶ/ር ሷሊህ ኢቢኑ ዐብዱልዐዚዝ አስ–ሲንዲ በዘመናችን ካሉ ታላላቅ የዐቂዳ ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው።
የአህሉሱናህ ወልጀመዓን ዓቂዳ በሚገባ ለመረዳት የሚረዱ ሁለት ታላላቅ መጽሐፍትን እንዲህ ሲሉ ይጠቁማሉ፡-
1. ሸርህ ኡሱል ኢዕቲቃድ አህሊሱናህ ወልጀመዓ (በአል-ላለካኢ የተዘጋጀ)፦ ይህ ኪታብ የአህሉሱናን ዓቂዳ ለማብራራት ከተፃፉ ኪታቦች ሁሉ እጅግ ላቅ ያለ፣ ምርጥና ሁሉንም አጠቃላይ የሆነ ኪታብ ነው ነው። ማንኛውም ስለ አህሉሱናህ ዓቂዳ ጥልቀት ያለው እውቀት መያዝ የሚፈልግ ሰው ከዚህ ኪታብ አይጠገብም። ኪታቡ የአህሉሱናን ትምህርት ከማብራራት ባለፈ፣ የተሳሳቱ አመለካከቶችን (ቢድዓዎችን) ውድቅ በማድረግ ረገድም የሚደነቅ ስራ ተሰርቶበታል።
2. አል-ኢባናህ (በኢብኑ በጣህ የተዘጋጀ)፦
ከላይ የተጠቀሰውን ኪታብ ከዚህኛው ከኢብኑ በጣህ "አል-ኢባናህ" ኪታብ ጋር አጣምሮ ያነበበ ሰው፣ እጅግ በጣም ሰፊና ጠቃሚ የሆነ እውቀትን ያገኛል። ይህ ኪታብም ልክ እንደ መጀመሪያው ለአህሉሱናህ ሊቃውንትና ተማሪዎች እጅግ ውድና በምንም የማይተካ ኪታብ ነው።
ባጠቃላይ፡ እነዚህ መጽሐፍት የአህሉሱናን (ዓቂዳ) በዝርዝርና በማስረጃ ለማወቅ ለሚፈልግ ለማንኛውም ሰው መሰረታዊ ምንጮች መሆናቸውን ገልጸዋል።
### ስለ አህሉሱናህ ወልጀመዓ ዓቂዳ በዝርዝር የሚያብራሩ ምርጥ መጽሐፍት
አሽ–ሸይኽ ዶ/ር ሷሊህ ኢቢኑ ዐብዱልዐዚዝ አስ–ሲንዲ በዘመናችን ካሉ ታላላቅ የዐቂዳ ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው።
የአህሉሱናህ ወልጀመዓን ዓቂዳ በሚገባ ለመረዳት የሚረዱ ሁለት ታላላቅ መጽሐፍትን እንዲህ ሲሉ ይጠቁማሉ፡-
1. ሸርህ ኡሱል ኢዕቲቃድ አህሊሱናህ ወልጀመዓ (በአል-ላለካኢ የተዘጋጀ)፦ ይህ ኪታብ የአህሉሱናን ዓቂዳ ለማብራራት ከተፃፉ ኪታቦች ሁሉ እጅግ ላቅ ያለ፣ ምርጥና ሁሉንም አጠቃላይ የሆነ ኪታብ ነው ነው። ማንኛውም ስለ አህሉሱናህ ዓቂዳ ጥልቀት ያለው እውቀት መያዝ የሚፈልግ ሰው ከዚህ ኪታብ አይጠገብም። ኪታቡ የአህሉሱናን ትምህርት ከማብራራት ባለፈ፣ የተሳሳቱ አመለካከቶችን (ቢድዓዎችን) ውድቅ በማድረግ ረገድም የሚደነቅ ስራ ተሰርቶበታል።
2. አል-ኢባናህ (በኢብኑ በጣህ የተዘጋጀ)፦
ከላይ የተጠቀሰውን ኪታብ ከዚህኛው ከኢብኑ በጣህ "አል-ኢባናህ" ኪታብ ጋር አጣምሮ ያነበበ ሰው፣ እጅግ በጣም ሰፊና ጠቃሚ የሆነ እውቀትን ያገኛል። ይህ ኪታብም ልክ እንደ መጀመሪያው ለአህሉሱናህ ሊቃውንትና ተማሪዎች እጅግ ውድና በምንም የማይተካ ኪታብ ነው።
ባጠቃላይ፡ እነዚህ መጽሐፍት የአህሉሱናን (ዓቂዳ) በዝርዝርና በማስረጃ ለማወቅ ለሚፈልግ ለማንኛውም ሰው መሰረታዊ ምንጮች መሆናቸውን ገልጸዋል።
👍6❤3
ሰዎችን መሰለል ማህበረሰቡ ውስጥ ጥላቻና በቀል ያነግሳል። 7122 SMS | ለወዳጆ ያስተዋውቁ
👍5
ለፈገግታ!
አንዱ ሰው እንዲህ ይላል፦
"ሁልጊዜ ለፈጅር ሰላት ቀድሜው በመገኘቴ የሚቀናብኝ አንድ ጓደኛ ነበረኝ። አንድ ቀን ምስጢሩ ምንድን ነው? እንዴት ሁልጊዜ በፈጅር ሰላት ትቀድመኛለህ? ብሎ ጠየቀኝ።
እኔም፦ 'ለአላህ ምስጋና ይሁን! ሁለት ሚስቶች አሉኝ፤ እነሱ እኔን ለማገልገልና ለሰላት እንድነቃ በመርዳት እርስ በእርስ ይፎካከራሉ፣” አልኩት።
ጓደኛዬም በዚህ ተነቃቅቶ ሁለተኛ ሚስት አገባ። አሁን ግን ለአላህ ምስጋና ይሁንና መስጂድ ውስጥ አብሮኝ ማደር ጀምሯል!"
** (التخطيط في علم التوريط)
ገጽ፦ 567
😂 😂 😂 😂 😂
አንዱ ሰው እንዲህ ይላል፦
"ሁልጊዜ ለፈጅር ሰላት ቀድሜው በመገኘቴ የሚቀናብኝ አንድ ጓደኛ ነበረኝ። አንድ ቀን ምስጢሩ ምንድን ነው? እንዴት ሁልጊዜ በፈጅር ሰላት ትቀድመኛለህ? ብሎ ጠየቀኝ።
እኔም፦ 'ለአላህ ምስጋና ይሁን! ሁለት ሚስቶች አሉኝ፤ እነሱ እኔን ለማገልገልና ለሰላት እንድነቃ በመርዳት እርስ በእርስ ይፎካከራሉ፣” አልኩት።
ጓደኛዬም በዚህ ተነቃቅቶ ሁለተኛ ሚስት አገባ። አሁን ግን ለአላህ ምስጋና ይሁንና መስጂድ ውስጥ አብሮኝ ማደር ጀምሯል!"
** (التخطيط في علم التوريط)
ገጽ፦ 567
😂 😂 😂 😂 😂
👌23🥰5😱4👍3❤2