Space Science and Geospatial Institute
1.46K subscribers
5.05K photos
138 videos
21 files
412 links
Download Telegram
ሐምሌ 5 ቀን 2014 ዓ.ም
-------------------------------
የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የቢሾፍቱ ከተማን የዲጅታል አድራሻ ስርአት ለመገንባት ከከተማው አስተዳደሩ ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ
----------------------------------
የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ በእለቱ ባደረጉት ንግግር ይህ በዛሬው እለት የተካሄደው የውል ስምምነት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቢሾፍቱ ከተማን የዲጂታል የአድራሻ ስርዓት በማልማት ደረጃውን የጠበቀ የአድራሻ ስርዓት መዘርጋት ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የቢሾፍቱ ከተማ የዲጅታል አድራሻ ስርአት ፕሮጅክት በዛሬው እለት በይፋ ስራውን የጀመረ ሲሆን በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ስራው ተጠናቆ አገልግሎት ላይ የሚውል ይሆናል፡፡

የውል ስምምነቱን በስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በኩል የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ የፈረሙ ሲሆን በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በኩል የከተማዋ ም/ከንቲባ አቶ አብዱሰላም መሐመድ ፊርማቸውን በማኖር የፕሮጀክቱን ስራ በይፋ አስጀምረዋል፡፡

የጂኦስፓሽያል መረጃ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ከሚያስፈልጉ ወሳኝ ግብዓቶች መካከል አንዱና ዋነኛ ነዉ፡፡የጂኦስፓሻል መረጃ ለመንገድ፤ለባቡር መስመር፤ለግድቦች፤ለኢንዱስሪዎች እና ለአዉሮፕላን ማረፍያዎች ግንባታ ፤ለጤና ፤ለገጠርና ከተማ መሬት ይዞታ /ካዲስተር/ካርታ፤ለቱሪዝም፤ለግብርና፤ለአካባቢ ጥበቃና ተፈጥሮ ሐብት ልማት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነዉ፡፡በተጨማሪም ዉሳኔ ሰጪ የመንግስት አካላት በነዚህና ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህራዊ ልማት እቅድና ትግበራ ዉስጥ መረጃ ላይ የተመሰረተ ትክክለኛና ወቅታዊ ዉሳኔ እንዲሰጡ ለማስቻል የጂኦስፓሽያል መረጃዎች የማይተካ ሚና አለው፡፡

በሀገራችንም በአሁኑ ጊዜ እየተካሄደ ካለዉ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጋር ተያይዞ የጂኦስፓሻል መረጃ ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል፡፡የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ይህን አገራዊ የመረጃ ፍላጎት ለማሟላት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
___________________________________________
PhD_Msc_Announcement_2022_2023.pdf
161.5 KB
Announcement 🛎🛎🛎
Call for Applications into PhD And MSc Programmes 2022/2023 Academic Year at Space Science and Geospatial Institute
Space Science and Geospatial Institute (SSGI) is seeking applications from national and international applicants into PhD and MSc programmes for the 2021/2022 academic year.
Space Science and Geospatial Institute
PhD_Msc_Announcement_2022_2023.pdf
ቀን 29 ሐምሌ /2014 ዓ.ም
ለ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
ጉዳዩ፡ የምዝገባ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ ይሆናል
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለድህረ-ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች ማስታወቂያ በማውጣት በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ለመማር ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች ሲመዘግብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ የምዝገባ ጊዜውም ሐምሌ 30 2014 ዓ.ም የሚጠናቀቅ መሆኑን አስመልክቶ ከተለያዩ አካላት የምዝገባ ጊዜ ይራዘምልን ጥያቄ እየቀረበ ይገኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲውም ይህንን ፍላጎት በማጤን በሁሉም የድህረ-ምረቃ ትምህርት ዘርፎች የሚደረገውን ምዝገባ እስከ ነሐሴ 07/2014 ዓ.ም ድረስ ያራዘመ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ዳይሬክቶሬት
በመሰረተ ልማት መረጃ ስርአት ማዘመን ዙሪያ ለአንድ ወር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ
( ነሐሴ 2 ቀን 2014 ዓ.ም ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩቱ )
በአዲስ አበባ ከተማ እየተተገበረ ያለውን የትላልቅ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ሂደት፣ በሪሞት ሴንሲንግ ሳተላይት መረጃዎች እና በጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን ለማስቻል የሚረዳ ስልጠና፣ ከሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ ቆይቷል።

በተለይ ለመዲናችን አዲስ አበባ አስፈላጊና አጅግ ጠቃሚ የሆነው ይህ ስልጠና ዛሬ ነሐሴ 2 ቀን 2014 ዓ.ም የምስጋና፣ ለሰልጣኞች የሥራ መመሪያ እና የምስክር ወረቀት የመስጠት መርሃ ግብር በማካሄድ ተጠናቋል ።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ደቦ ቱንካ (ኢንጂነር) እንደገለፁት፤ በከተማዋ በርካታ ግዙፍ የልማት ሥራዎች እንደሚሰሩና ነገር ግን ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ መሰረተ ልማቶችን መንከባከብ፣ ከጥፋት መጠበቅና በቀጣይነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ማድረግ ብሎም አንዳቸው ከሌላይኛው ጋር ተጋግዞ በመስራት፤ በከተማዋ የመሰረተ ልማት ስርዓት ላይ አመርቂ ውጤት ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ ተደርጎባቸው በመሬት ውስጥ ለውስጥና ከመሬት በላይ የሚሰሩ መሰረተ ልማቶች በአግባቡ እንዲያገለግሉ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ ስርዓት መዘርጋት ተገቢ በመሆኑ፤ በስልጠና ለማጠናከር ታስቦ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለውም ስልጠናውን የወሰዳችሁ አካላትም በከተማው በሚሰሩ የመሰረተ ልማት ሥራዎች ላይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ በወሰዳችሁት መሰረታዊ ስልጠና እውቀት ልክ፣ እንደ አንቂ ደውል ሆናችሁ በመንቀሳቀስና ውጤታማ ሥራ በመስራት፤ በከተማው አስተዳደር መሰረተ ልማት ሥራዎች ላይ በጋራ ውጤታማ ተግባር ማከናወን ይጠበቅባችኋል በማለት አሳስበዋል፡፡

በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ግርማ ወርቄ በበኩላቸው፣ ግባችን በአዲስ አበባ ያሉ መሰረተ ልማቶች የት ተመዝግበው እንዳሉ መለየትና አንዱ ተቋም የሰራውን ሌላው ተቋም እንዳያፈርሰው የምንሰራበት የመሰረተ ልማት አስተዳደር ስርኣት እንደ መሆኑ፤ ቀጣይ ይበልጥ ትኩረት ሰጥተን በጋራ የምንሰራበት ይሆናል ብለዋል፡፡

በመድረኩም ለአንድ ወር ስልጠናውን ሲሰጥ የቆየው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደተናገሩት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የከተማው አስተዳደር ጋር በቀጣይ በትብብር መስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ እና አስፈላጊውን የሙያ ድጋፍ በማድረግ በዘርፉ የሚታዩትን ተግዳሮቶች ለፍታት በትብብር ኢንስቲትዩታቸው እንደሚስራ በመግለፅ ስልጠናው የተሳካ እንዲሆን አስተዋጽኦ ያደረጉትን የልማት አጋር አካላትን አመስግነዋል፡፡

ስልጠናው የተሰጠው በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት፣ የስዊድን ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት (SIDA) እና የአዲስ አበባ ሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት በትብብር ሲሆን ፤ለከተማዋ ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ስርአት መሰረታዊ በሆኑ አራት ሙያዊ መጠሪያ ባላቸው ማለትም የጂ.አይ.ኤስ (GIS) ፣ ሪሞት ሴንሲንግ (RS) ግራውንድ ፔኔትሬቲንግ ራዳር (GPR) እና ጂ.ኤን .ኤን .ኤስ (GNNS) በተባሉ ርዕሰ ጉዳዮች ከንድፈ ሀሳብ እስከ የተግባር ላይ ስልጠናን ያካተተ የስልጠና መርሃ ግብር ተካሂዷል።
👍1