Scripture union addis ababa
103 subscribers
607 photos
13 videos
29 files
14 links
Download Telegram
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ህይወትና እንቆቅልሽ
ህይወት ከእንቆቅልሽ ተለይታ አታውቅም በየአንዳንዱ ቀን ከተለያዩ የህይወት እንቆቅልሾች ጋር መጋጠምህ አይቀርም፤ በቀላሉ መፍትሄ የማታገኝለት፣ ነገሩን ዝም ብለህ ስትመለከተው ምንም ትርጉም የሌለው፣ ልትረዳው የማትችለው በየእለቱ የሚያሳስብህ፣ የሚያስጨንቅህ፤ ተጨንቀህም አስበህም መፍትሄ የማታገኝለት የህይወት እንቆቅልሽ፤ በየእያንዳንዱ የመንገድህ ፌርማታ ላይ ሊጠብቅህ ይችል ይሆናል።

ዙሪያህን መመልከት ትተህ ወደ ላይ ብትመለከት የእንቆቅልሾችን ሁሉ መፍትሄ የሆነውን ጌታ በዙፋኑ ትመለከታለህ፣ እርሱ ያንተን የተተበተበ የህይወት ጥያቄና ግራም የሚያጋባህን ነገሮች ሁሉ ሊፈታ መፍትሄንም ሊሰጥህ ከባድ የሚባል ነገርን ለማያውቀው ጌታ፣ ለእርሱ ይህ ቀላል ነው።

አንተ ብቻ ጩህ ነገርህንም ይዘህ በፊቱ ቁም።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ምንድን ነው ምትሰራው?

አሁን በዚህ ወቅት ምን እየሰራህ ነው?
የምትሮጠው ሩጫ ምን ላይ ነው? ለምትወደው፣ ህልም፣ ራእይህ፣ ለሆነው ወይስ በተቃራኒው?

በውስጥህ የመኖርን ምክንያት ለሚሰጥህ፣ ባይከፈልህም በደስታ ለምታረገው ነገር፣ ስራህን ስታስብ የበለጠ መሰጠት፣ ጠንክሮ መስራትን በውስጥ መነቃቃትንና ግለትን ለሚሰጥህ ነገር ካልሆነ እንዲሁ በዝለት መቼ ጨርሼው በተገላገልኩ፤ እያልክ ህይወትህ ደስታን ሳያገኝ እንዲሁ ትኖራለህ

ጉልበትህንም ሀልህንም ለአንተ የውስጥ ፍላጎትህ ላለበት ነገር አውለው ያኔ ትበረታለህ፣ ያኔ እንዲሁ ምንም ሳታበረከት በከንቱ አታልፍም

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
🙏🙏ሰላም ሰላም የ አባቴ ልጆች እንዴት አላችሁልን🙌🙌🖐

ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር ፡ በጣም በጉጉት የሚጠበቀው የ ENTOTO AMBA JIDIDIAH FELLOWSHIP የ ተራራ ፀሎት ፕሮግራማችን ከ final exam በኋላ ሚያዚያ 2 ቅዳሜ ቀን ይሆናል ጌታም በክብር ይገናኘናል🙌🙌 መቅረት አይቻልም

ተባረኩ!!!!
@entotoambafellowship
@entotoambafellowship
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ትኩረት
ህይወት በብዙ ሀላፊነቶችና ግዴታዎች የተሞላች ነች እነዚህንም ስራዎች ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመወጣት በአንድ ነገር ላይ አተኩሮ የመስራት ስልትን ማዳበር ይጠይቅሀል። እጅህ ላይ ያለውን ሁሉ ለማከናውን የምትሮጥ ከሆነ ጊዜህን፣ ጉልበትህን፣ ሀይልህን እንዲሁ በከንቱ ትጨርሰዋለህ።

ብዙ ስራ ቢኖርም በቅደም ተከተል፣ አንድ በአንድ በነገሮች ላይ የመስራት ስልትን መጠቀም ይኖርብሀል፤ አለበለዚያ ሁሉን ለማድረግ ስትሞክር አንዱንም ሳትተገብር ምንም ውጤት ሳታስመዘግብ እንዲሁ ታልፋለህ።

የተበታተነ ህይወት ምን ጊዜም ውጤቱ ከንቱ ልፋት ብቻ ነው። የጎላ ፍሬ ማየት ከፈለግክ ዋና የምትለውን የህይወትህን ተግባር መርጠህ በዛ ላይ አድምተህ ስራ ያኔ የሚያጎመራ ውጤትን ታገኛለህ።

ብዙ የሮጠ ምንም አያገኝም ይልቅስ የሚፈልገውን ለይቶ አውቆና መርጦ በጥበብ የሚሮጥ ስኬትን ያጣጥማል።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ጸሎት

ህይወት በብዙ ፈተናዎችና ትግሎች የተሞላች ነች አንዱን ታግለህ ሳትጨርስ ሌላው ይከተላል፣ እሱንም ሳታገባድድ ደግሞ ሌላው ይመጣብሀል እጅግ አታካችና አስቸጋሪ መንገድ ነች ህይወት። ታዲያ እነዚህን ውጣ ውረዶች በሙሉ በራስህም ሆነ ይረዱኛል በምትላቸው ሰዎች በኩል በመታገል፣ የበላይ ሆነ መጨረስ የማይታሰብ ነው። ሁለም ሰው የራሱ ችግር ስላለበት ላንተ ሊደርስልህ አይችልም

ነገር ግን ወደ ሰማዩ አባትህ አይንህን ብታነሳ፤ እርዳኝ ብለህ ብትጮህ፣ በጸሎት ብቻ አሸናፊ ትሆናለህ። በፊቱ በመንበርከክ ሀይልን ትቀበላለህ የገጠመህን ተራራም የመሻገሪያ አቅም ይጨመርልሀል።

በጸሎት ልብህን ትጠብቃለህ፣ ከአባትህም ጋር ህብረትን ታደርጋለህ፣ ህይወትህ ከወንዝ ዳር እንዳለ ተክል ያብባል ድርቅ ቢመጣም እንኳ አይጠወልግም። ከራስህም አልፈህ ለብዙዎች መፍትሄ ትሆናለህ፣ መዝሙረኛው ዳዎት እንዳለው" በጠዋትም በቀትርም በማታም" ፊቱን በጸሎት አብዝተክ መፈለግ ይሁንልህ።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ስብራትህን ይዘህ

ህይወት ትእይንት ናት ብዙ ገጠመኝ የተሞላች ትእይንት መኖር ስትቀጥል የምትታዘበው ነገር ይህንኑ እውነታ ነው።

ብዙ ህመም፣ ብዙ ግራ መጋባት፣ ብዙ ትግል በዚህ መሀል የህይወት ስብራቶችም ይገጥሙሀል ለማገገም ለመፈወስም ጊዜ የሚፈልጉ፣ ቶሎ የማይሽሩ ህመሞች ሲያልፋም ጠባሳ ጥለው የሚያልፋ የህይወት ስብከቶች አሉ በእነዚህ ስብራቶች ውስጥ ሆኖ ወደፊት መሄድን ማሰብ ይከብዳል ተስፋ ይመነምናል ህይወት ትርጉም ያጣል።

ወደፊት መሄድ ለወጣት የማይቻል ተራራ ይሆናል ወደፊት ካልሄድን ወደሗላ እየሄድ ነውና ያገኘሀቸው ለውጦችን በሙሉ ማጣትህ ነው።

ስለዚህም ያለህ አማራጭ ህመምህን፣ ግራ መጋባትህንም፣ ስብራትህን ይዘህ በፊቱ በጸሎት ሁን እርሱን እሻው እየወጋ፣ እየጠዘጠዝህ ካለው ህመምህ ጋር በፊቱ ሁን እርሱ ፈዋሽህ፣ መድሀኒትህ እግዚአብሄር ነውና።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
የእግር ኳስ ነገር
በአለማችን ላይ የሰውን ልብ እጅግ ከገዙ፣ ህይወቱንም እንኳ እስከመስጠት እንዲደርስ ምክንያት ከሆኑ የስፓርት ውድድሮች ሁሉ እግር ኳስ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።

በኳስ ምክንያት የተጣሉ፣ የተገዳደሉ፣ የተታረቁ፣ ድንበር ሳይበግራቸው አንድነትን ያሳዩ፣ ብዙ ሰዎች አሉ። እኔ ከሚገርመኝ የእግር ኳስ ስልቶች ውስጥ የ12ቱ ተጫዋቾች ነገር ነው። የሁሉም ድል የሚወሰነው እያንዳንዳቸው በሚያደርጉት ጥረትና ትጋት ላይ ነው ሁሉም ለቡድኑ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ቀላል የሚባል አይደለም፣ የአንዱ ተጫዋች ድካም በሙሉ ቡድኑ ላይ የሚያስከትለው ጉዳት ቀላል አይደለም።

"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንደሚባለው የእያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋም ህይወት እንደ እግር ኳሱ ሁሉ ነው።
የእያንዳንዱ ሰው ሀላፊነቱን እንደሚገባ መወጣት ወይም ቸልተኛ መሆን በድምሩ በሀገር ላይ የሚያስከትለው የድል ወይም የኪሳራ ውጤት ቀላል አይደለም።

የአንዱ ጥንካሬ፣ ትጋት ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለሀገሩ ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጾ አለው።
ስለዚህም በተሰማራህበት ስፍራ በር ትተህ ስራ የአንተ ብርታ ለመላ ሀገሪቱ አስተዋጾ ቀላል ስላልሆነ።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ጠንክረህ ስራ

ህልምህን፣ ራእይህን፣ እውን ማድረግ የምትሻ፣ የምትመኝ ከሆነ ምኞትህንና ፍላጎትህን በጠንካራ የስራ ባህል ልትደግፈው ይገባሀል።

ህይወት ያለ ስራ ትርጉም የላትም። በህይወት ደስ እየተሰኘህ እንድትኖር ከሚያደርጉህ ነገሮች መሀል በላብህ፣ በድካምህ፣ ለፍተህ የምታገኘው ፍሬ ነው።

ከስራ የሚገኝ ውስጣዌ እርካታ አለ፣
ጠንክሮ መስራት በውስጥህ ልዮ የውጤታማነትን ስሜት ይፉጥርልሀል፣ ብዙ እንድታፈራም በር ይከፍትልሀል

ስራ ፈት መሆን ራስህ፣ አእምሮህን፣ ቤተሰብህን፣ ሀገርህንም በብድርና በችግር ውስጥ በማስማቀቅ ለከፋ ድህነት ከማጋረጥ ያለፈ ነገር በውስጡ አያስገኝህም።

ለብዙዎች መትረፋን የምታስብ ከሆነ ራስህን በጠንካራ የስራ ባህል አስታጥቅ። ያኔ በብዙ ፍሬ ትባረካለህ።
በምን ላይ ነው የተሰማራሕው በትምህርት? በስራ? ጠንክረህ ስራ፣ አትድከም፣ አትሰልች በመጨረሻ ሙልካሙን የድካምህን ፍሬ ታጭዳለህ።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ተስፋ አለ
ምን እየተሰማህ ነው? ውስጥህ ምን እየጎዳህ ነው? ተስፋ አርገህ አጣህ? እንዳሰብከው ሳይሆን ቀረ? አይዞህ አሁንም ተስፋ አለ ተስፋን የሚሰጥ ስላለ እርሱ አሁንም በዙፋኑ ላይ ጸንቶ ስለሚኖር አሁንም ተስፋ።

ቀን ሲጨልምብህ፣ ግራ ሲገባ በእርሱ ታምነህ፣ ነገ ብርሀን ይሆናል ብለህ ጉዞህን ቀጥል።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
አስረክበው
በህይወትህ እጅግ ልታገኘው የምትፈልገው ነገር ይኖራል። ብዙም ታግለህ፣ ሮጠህም ይሆናል ነገር ግን ምንም ለውጥ አላየህበትም።

ብዙ ብትለፋም የተቀየረ ነገር የለውም በእንደዚህ አይነት ጊዜ ልታረግ የምትችለው ነገርህን በሙሉ ለእግዚአብሄር ማስረከብ፣ ለጌታ አደራ አሳልፈህ ስጠው በቃ ልብህንም በእርሱ ላይ ጣለው እርሱ መንገድህን ቀያሽ ህይዉትህንም በእጁ የያዘ ጌታ ነው።

እርሱን ታምነኽው ተጓዝ የሚያሳስብህን ግር የሚልህን ሁሉ ለእርሱ ሰጥተኽው መንገድህን ቀጥል።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ሰልፍ ዲሲፕሊን
ሰው በህይወት ዘመኑ ሁሉ ውጤታማና ስኬታማ የሆነን ህይወት ለመምራት የሚሻ ከሆነ ራሱን የመምራት ጥበብ ማዳበር ይኖርበታል።

ሰልፍ ዲሲፕሊን ማለት አንድን ተግባር ከግብ ለማድረስ ራሳችንን በመቆጣጠር፣ ስርአት በማስያዝ፣ መከፈል ያለበትን ዋጋ ሁሉ በመክፈል የምንኖርበት ስልት ነው።

ወደ አላማህ እንዳትደርስ፣ ከግብህ ጋር እንዳትገናኝ መሰናክል ከሚሆንብህ ነገር ትልቁና ዋናው ያው ራስህ ነህ ፤ ያማለት ስንፍና፣ እንቅልፍ ማብዛት፣ ወሬ፣ ሀሜት፣ ስራን አለመውደድ እነዚህ ሀሉ ከራስህ የሚመነጭ ተግዳሮት፣ መሰናክል ናቸው።

ማሸነፊያ መንገዱ አንድ ነው ራስን የማስተዳደር ( የመግዛት፣ የመምራት) ጥበብ ማዳበር፤ ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ መስጠይ፣ ዋና መሆን ላለበት ጉዳይ ዋና ማድረግ፣ የጊዜ አጠቃቀምን ማስተካከል፣ ወዘተ....... ራሳችንን የማስተዳደሪያ መንገዶች ናቸው።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
በምትሰራቸው ስራዎች አለመሳካት እየገጠመክ እየወደክ እየተነሳህ ህይወት ትቀጥላለች። ለማደግ ለመለወጥ ብለህ ብዙ ነገር ሞክረክ ሳይሳካ ይቀራል። ግን ፍላጎትህ እውነት ካለው ካንተ የሚጠበቀው ተስፍ ሳትቆርጥ ደጋግሞ መሞከር ነው። አይሳካም አይሆንም ወይም አሁንም ይበላሻል ብለህ ሙከራህን አታቁም።ሁሉም ያደገው ከአንድ እንጂ ከመቶ አይደለም አንተም ከስኬትህ ሳይሆን ከውድቀትህ ጀምር።

መልካም ቀን
ራሄል ካሳሁን
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
በአመት አንዴ!!

ፋሲካ በአመት አንዴ አክብረን የምናልፈው በዓል አይደለም። ፋሲካ ምግብና መጠጥም አይደለም። ፍሲካችን ኢየሱስ ነው።
“እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።”
— ኢሳይያስ 53፥5

እለት እለት ኢየሱስን በማወቅ ማደግ ይሁንልን!
ኢየሱስ ህይወት፣ ህይወትም ኢየሱስ ነው።
ከፍርዕዖን ግዛት ሳይሆን ከሰይጣን ሀሳብ ( ከዘላለም ሞት) ነብሳችን ያዳናት ጌታ ኢየሱስ ይባረክልን።
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ፈጣሪህን እና በዙሪያህ የሚገኙ ሰዎችን ለማመስገን የግድ ትልቅ ነገርን እስኪያደርጉልህ አትጠብቅ አምላክህን ለማመስገን ግዴታ ከትልቅ አደጋ እስኪያስመልጥህ አትጠብቅ ምክንያቱም በሰላም ወጥተህ መግባትህ ውስጥ አንተ ያላስተዋልካቸው እርሱ ግን አስቀድሞ የተከላከለልህ እጅጉን ከብዙ አደጋዎች አድኖሃል ሰዎችም ቢሆኑ የሚታይ ነገር ስላደረጉልህ ሳይሆን ምንም ባያደርጉ እንኳን ስሜትህን መጋራታቸውን አስተውል ።

መልካም ቀን
ራሄል ካሳሁን
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
በገጠመህ ትልቅ በሚመስል ትንሽ ችግር ምክንያት በችኮላ ተስፋ አትቁረጥ ውሳኔዎችህ ካለፉ በኋላ የማትቀይራቸው ሊሆኑ ይችላሉ ያንተ በህይወትህ ላይ ተስፋ ማጣት ብዙዎች መኖራቸውን ተርጉም እንዲያጣ እስከዛሬ ላንተ የከፈሉትን ሁሉ ዋጋቢስ ታደርገዋለህ አንዳንዶች አልወደዱኝም እያልክ የሚወዱህን አታስከፋ ህይወት መረረኝ ስትል የሚያጣፈጡልህንም እንዳታጣ ተጠንቀቅ።

መልካም ቀን
ራሄል ካሳሁን
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
መዘናጋት
ከዋናው የህይወትህ አላማ፣ ካየህበት ስፍራ እንዳትደርስ መሰናክል የሚሆንብህ ትልቁ ተግዳሮትህ መዘናጋት ይባላል። ለጥቂት ጊዜ ፈታ ልበል ትንሽ ዘና ልበል በማለት ፋት ልትሰጠው ከማይገባህ የህይወት አላማህ እንድትዘናጋ ትኩረትህን ፈቅ እንድታደርግ ያደርግሀል።

ከመዘናጋት ህይወት ለማምለጥ አላማህን አጥብቀህ መያዝን ፈጽመህ አትርሳ። ዝም ብሎ ያለማቋሩጥ የሚፈሰው ውሀ ድንጋዮን አብዝቶ እንደሚሸረሽረው እንዲሁ ደግሞ አንተም በትኩረት ስትሰራ ስራህ እንዲሁ ብርቱ ውጤትን ያስገኝሀል።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ
@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
እጅህን ለነገ ስጠው
በህይወት መንገድ ስትጓዝ በሚገጥምህ ከባድ ገጠመኞች ምክንያት የህይወት ግራጫ መልክ የያዝከው ተስፋ መንምኖ ነገን ማየት፣ በመንገድህ ስትጓዝም ሌላ እድል እንዳለም ማስተዋል እስካትችል ሊያጨልምብህ ይችላል የትላንት የልብ ላይ ህመም እድል እንደሌለህ፣ ምንም ብታረግ ህይወትህ ትርጉም እንደሌለው አርጎ ሊያሳይህ ይችላል።

ትላንት በሆነው ነገር ከፊት ያለው ዘመንህ ሊታሰርብህ፣ ልትዋጀው፣ ልትሰራበት፣ ልትጠቀምበት ሲገባህ የእርሻ ማሳላይ አረም ሊበቅልበት፣ ጓተራህም በድርቅ ሊመታብህ፣ ቤትህም ጾሙን ሊያድር ይችላል።

በትላንትና እስራት ስር መሆን ዘመንህን በአንበጣ ማስበላት ነው። ወደፊት ከመሄድ ተገትተህ በቆምክበት ጊዜ ልክ ኪሳራህም እየበዛ ይሄዳል ለዚህም ነው ሐዋሪያው ጳውሎስ "የሗላዬን እየተውኩ የፊቴን ለመያዝ እዘረጋለሁ" ብሎ ያስተማረው።

በተቻለህ አቅምና ፍጥነት የትላንት ህመምን፣ ጉዳትን፣ ችግርን፣ ከአእምሮህ ውስጥ አውጣው። አለበለዚያ በአደጉኛው ወይንቤቱ ከርችሞ ሊያስቀርህ ይችላል።

ከዚህ እስር ቤት ለመውጣት ከፈለግክህ እጅህን ለነገ ስጠው። በሙሉ ሀይልህ ነገን ብቻ ተመልከት ያኔ ከትላንት እስራት ነጻ ትወጣለህ።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ራስህን እርዳ

አሁን በዚህ ሰአት ካለህበት ስፍራ ሊያወጣህ፣ ወደስኬት ጎዳናም ሊያሻግር ችግሮችህ በሙሉ አሸንፎ ውጤታማ ሊያደርግህ የሚችል ማን ይሆን?

አንተን የተሻለ ሰው ሊያደርግ የሚችል፣ ህልምህን፣ ራእይህን፣ የተፈጠርክለትን አላማ አከናውነህ እንድታልፍ ትልቁን ሚና የሚጫወተው ማን ይመስልሀ?

በህይወትህ የምትናፍቀውን ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ማን እንደሆን ታውቃለህ?

አንተ ራስህ ነህ!!!

ሌላ ማንም የለም ለአንተ ህይወት ለውጥ ዋናው ድርሻ የሚይዘው አንተ ራስህ ነው።

አንተ ወስነህ ካልተንቀሳቀስክ ማንም አይንቀሳቀስልህም፣ ማንም በህይወትህ የሚመጣውን ለውጥ አያስቀጥልልህም።

ስለዚህም ራስህን እርዳ ቆርጠህ ተነሳና ወደፊት ተራመድ።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
አደራ

ሰው ሰውን ሲያምነው፣ እንደራሱ ሲቆጥረው፣ ሲወደው፣ የሚወደውን ነገር በአደራነት በዚያ ሰው ዘንድ ሊያስቀምጥ ይችላል።

በማህበራዊ ህይወታችንም ይህንን ነገር ብዙውን ጊዜ እንታዘባለን። በአደራነት የተሰጠ ልጅ፣ ቤት፣ መኪና፣ ገንዘብ፣ ወዘተ አደራን ከሌላ ነገር የሚለየው ሰጪ አንድ ቀን ከእኛ ስለሚቀበል ነው። ማለትም ለጊዜው የተሰጠ እንጂ የእኛ ንብረት አይለመሆኑ ነው።

አንተ የአምላክህንና የብዙ ሰዎችንአደራ ተቀብለሀል ታዲያ ይህን አደራ ምን እያረከው፤ እንዴትስ እየተወጣከው ነው።

በቤተክርስቲያን የተሰጠህን አደራ እንዴት እያረክ ነው ባለህበት የአገልግሎት አቅጣጫ ሀላፊነትህን እንደሚገባ እየተወጣክ ነው? ወይስ?

በቤት የተሰጠህን አደራ እናት አናትህን ወንድም እህትህን ፣ ባለቤትህን፣ ልጆችህን እንዴት እየተንከባከብ ነው?

በማህበረሰብ ውስጥ የተሰጠህን አደራስ እንዴት እየተወጣክ ነው?

አደራ ሲሰጥህ ምን ያህል ታማኝ ተደርገህ እንደተቆጠርክ፣ ምን ያህል ትጋትና መሰጠት እንደሚጠበቅብህ ልታስብ ይገባሀል።

ተግተህም የተሰጠህን አደራ እንደ ራስ ልትይዝ፣ ልትንከባከብ ይገባል።


መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus
Forwarded from Youth focus (Sam Kb)
ጽዳትና ጸሎት
በህይወት ስንኖር የእለት ተግባራችን ከሚሆኑ ነገሮች ውስጥ ትልቁን ስፍራ የሚይዘው ጽዳት ነው። ራሳችንን፣ አካባቢያችንን፣ ስራ ቦታችንን... እናጸዳለን ቆሻሻ ሲከማች ያንን ቦታ የማበላሸትና በሽታ የማምጣት አቅሙ ትልቅ ስለሆነ ህይወትና ጽዳት የተለያዮ ጉዳዮች አይደሉም።

የጥርስ ቆሻሻ ቶሎ ካልጽዳ ጥርስን ከጥቅም ውጪ እንደሚያደርገው፣ አካባቢ ካልጸዳ፣ ልብስ፣ ሰውነት ካልታጠበ ጀርምና በሽታ አምጪ ተዋሲያን እንደሚከማቹት ሁሉ ሰውም በጽሎት ማስወገድ ያለበትን ማንነት ካላስወገደ እንዲሁ ባልተወገደው አላስፈላጊ ማንነት ህይወታችን ስለሚበላሽ በጽሎት የሚደረገውን ጽዳት አጠናክሮ መቀጠል ቸል የማይባል ጉዳይ ነው።

መልካም ቀን
ሳሙኤል ከበደ

@youthfocus
@youthfocus
@youthfocus