ONLY ARSENAL
445 subscribers
116 photos
14 videos
12 links
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

💥የዝዉዉር ዜና
💥የአሰልጣኞች አስተያየት
💥ጎሎች እና አዝናኝ ቪዲዮዎች
💥የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
💥ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
√ዛሬ ነው፣ ቀኑ እንዴት አደራችሁ? እስቲ መቼም የማይረሳ Andrey Arshavin ሊቨርፑልን ላይ ያገባው 4 ምርጥ ጎሎች ይመልከቱ!

@onlyarse
#አርሰናል እና ሊቨርፑል በሁሉም ውድድሮች #192 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን #አርሰናል 68 ጊዜ ሲያሸንፍ #ሊቨርፑል 71 ጊዜ አሸንፏል #53 ጊዜ አቻ ወተዋል፣ #በዚህ ግንኙነታቸው በከፍተኛ ጎል በማሸነፍ ቀዳሚውን ድርሻ የሚወስደው!

አርሰናል ሲሆን 8-1 ሊቨርፑልን ያሸነፈበት ውጤት ትልቁ ነው፣ #ሊቨርፑል ትልቁ ያሸነፈበት ውጤት 5-0 ነው።

#በዚሁ ግንኙነታቸው 546 ጎል የተቆጠረ ሲሆን አርሰናል 265 ሊቬ 281 ጎል አስቆጥረዋል! #ያለፉትን ስደስት ጨዋታ ግንኙነት የኛው አርሰናል መጥፎ ሪከርድ ነው፣ ያለው ምንም ጨዋታ ሊቨርፑልን አላሸነፈም!

#4 ጊዜ ሊቨርፑል ሲያሸንፍ
#2 ጊዜ ደግሞ አቻ ወቷል

ዛሬ ከምሽቱ 1:30 ግን ሌላ ታሪክ ነው፣ መድፈኛችን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በከፍተኛ ተነሳሽነት ለብቀላ ተዘጋጅተዋል፣ አስፈሪው የፊት መስመራችን ጎል ለማምረት ተዘጋጅቷል፣ ፔፔ ቋሚ ሆኖ እንደሚጀምር ተነግሯል ይህ ደግሞ ምርታማነታችንን ይጨምረዋል።

ጥሩ ተስፋ ያሳየን #በካዞርላ ጅማሮ አይተን በደንብ ሳንጠቀምበት፣ሳንጠግበው በጉዳት ያመለጠን ልጃችንን #በዳኒ ሴባዮስ ውስጥ አይተነዋል ይህም የሊቨርፑልን ሳጥን በተደጋጋሚ እንድንገባ ያደርገናል።

ከምንም በላይ የሚያሳስበን የነበረው ተከላካይ ክፍላችን በስህተት የታጀበውን ሙስጣፊን ቁጭ ማድረጋችን በራሱ አንድ እፎይታ ነው! በልምድ የታጀበውን #ሉዊዝን የመሀል ደጀናችን ማድረጋችን ክላሳችንን እንደሚጨምርልን ግልፅ ነው፣

#ሜትላንድ ናይልስ ከወትሮው ተሻሽሎል ወደ ማጥቃቱ ላይ ቢያዘነብልም ኳስ መቀማት ላይ መሻሻልን እያሳየ ነው፣
#ሌላው በግራ በኩል ከኮላሲናች ይልቅ ሞንሪያል ይጠቅመናል ባይ ነኝ ኮላሲናች ለማጥቃት ሲሄድ የሚከፍተውን ቦታ ተመልሶ ለመዝጋት ይቸገራል መከላከሉ ላይም እምብዛም ነው፣ እንደ አርኖልድ ደግሞ ፈጣን ፓሰር ክፍተት ካገኘ ወደ ሳጥን ወዲያው ወዲያው ኳስ በመጣል ያስቸግረናል ስለዚህ እንደ #ሞንሪያል አይነት ብዙም ቀጠናውን ለቆ የማይሄድ እና ኳስ መቀማት ላይ የተካነ ሰው፣ ያስፈልገናል ስለዚህ ኤምሬ ምርጫው እሱን ማድረግ አለበት።

#ሌላው ቶሬራን እና ጉንዶዚንን ከሴባዮስ ጋር ቢያጣምራቸው ሀሪፍ ነው ዣካ ባይገባ መልካም ነው።

መልካም የድል ቀን! ድል ለመድፈኛችን!

"SHARE" @onlyarse
#እውነታ

ሊቨርፑል በታሪኩ ከአርሰናል ጋር በሁሉም ውድድር ባደረጋቸው 226 ጫወታው በአንድ ጫወታ 6 ጎል አስቆጥሮ የማያውቅ ሲሆን አርሰናል ግን ይህን ለ4 ግዜ ማድረግ ችሏል።

√አርሰናል ሊቨርፑልን በሰፊ ጎል ያሸነፈባቸው ጫወታዎች፣

•1931.....አርሰናል 6-0 ሊቨርፑል
•1928.....አርሰናል 6-3 ሊቨርፑል
•1934.....አርሰናል 8-1 ሊቨርፑል
•2007.....ሊቨርፑል 3-6 አርሰናል

√ሊቨርፑል አርሰናልን በሰፊ ጎል ያሸነፈባቸው ጫወታዎች!

•1893.....አርሰናል 0-5 ሊቨርፑል
•1964.....ሊቨርፑል 5-0 አርሰናል
•2014.....ሊቨርፑል 5-1 አርሰናል
•2018.....ሊቨርፑል 5-1 አርሰናል

ለመጨረሻ ግዜ አርሰናል ሊቨርፑል ላይ 5+ ጎል ያስቆጠረው ከ12 አመት በፊት ሲሆን ሊቨርፑል ደግሞ ባለፉት 5 አመታት ይህን 2 ግዜ ማድረግ ችሏል።

•••••የዛሬው ጫወታስ ስንት ለስንት ይጠናቀቃል? እሱን አብረን የምናየው ይሆናል! "ድል ለመድፈኛችን"

"SHARE" @onlyarse
🇬🇧በ 3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ።

🕗የመጀምሪያው አጋማሽ ተጠናቆል

🛑 ሊቨርፑል 1⃣ 0⃣አርሴናል🔴

#ማቲፕ⚽️ 41'
ጎልል ሳህላ⚽️
🇬🇧በ 3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ።

🕗49'

🛑 ሊቨርፑል 2⃣ 0⃣አርሴናል🔴

#ማቲፕ⚽️ 41'
#ሳህላ⚽️(P) 49'
ሳህላ
🇬🇧በ 3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ።

🕗70'

🛑 ሊቨርፑል 3⃣0⃣አርሴናል🔴

#ማቲፕ⚽️ 41'
#ሳህላ⚽️(P) 49' 58'
73'

አርሴናል አሁን ሊቨርፑል ጎል አካባቢ እየተጫወቱ ነው
🇬🇧በ 3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ።

🕗ጨዋታው ተጠናቀቀ

🛑 ሊቨርፑል 3⃣1⃣አርሴናል🔴

#ማቲፕ⚽️ 41'
#ሳህላ⚽️(P) 49' 58' #ቶሬራ⚽️85'
በትላንት ምሽት ጨዋታ ላይ ኮትዲቯራዊዉ አጥቂ Nicolas Pepe ከ 50 የፕሪሜርሊግ ጨዋታ ቦሀላ ሆላንዳዊዉን አይበገሬ ተከላካይ ቨርጅል ቫንዳይክን በድሪብል ያለፈ የመጀመሪያዉ ተጨዋች ሆኗል። @onlyarse
Unai Emery ከጨዋታው በኃላ ናቾ ሞነሪያል በዚ ሳምንት ከክለባችን ሊለቅ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል።

"SHARE" @onlyarse
√ህይወት ከባድ ናት እግር ኳስም አንዳንዴ ከባድ ነው፣ግን አንድ ነገር አቃለው መቼም ተስፋ አልቆርጥም እዚህ የመጣሁት ከትልቅ አላማ ጋር ነው እናም ለዛ እስከመጨረሻው እፋለማለሁ።

ደጋፊዎችን ለድጋፋችሁ እጅግ አመሰግናለሁ መቼም አልደበቅም ማሸነፍ ወይም መሸነፍ !!!

@onlyarse
Gary Nevile በሊቨርፑልና አርሰናል ጨዋታ ዙሪያ በሰጠው አስተያየት አርሰናል 3-1 ቢሸነፍም ከሽንፈቱ ባሻገር ግን ከዚህ ቀደም አርሰናል ላይ ያላየናየው ብዙ Posetive የሆኑ ነገሮች አይተናል።
አርሰናል በዚ አመት የተሻሻለ ይመስላል ሌላው ቀርቶ ደጋፊዎቹ ሌላ ጊዜ 3ጎል ከገባ በኃላ እስቴዲየሙን ለቀው ሲወጡ እንመለከት ነበር አሁን ግን እስከመጨረሻው ጨዋታው ሲከታተሉ ነበር ይህ የሚያሳየን እስከመጨረሻው ቡድኑ ላይ የተመለከቱት የሆነ ተስፋ ሰጪ ነገር ስለነበር ነው፡፡

አርሰናል ዛሬ ያሳዩት ብቃት ብዙ ከሜዳ ውጪ ጨዋታዎችን ሊያሸንፉበት የሚያስችላቸው ነው፡፡ ግን መርሳት የሌለብን በአሁኑ ሰአት የአውሮፓ ምርጡን ቡድን ሊቨርፑል ነው ብሎ ሀሳቡን አጠናቋል።

የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች Gary Nevile ትናንት በአንፊልዱ ጨዋታ ላይ የሰጠው ትንታኔ ነው።

"SHARE" @onlyarse
​​አርሰናል 1 3 ሊቨርፑል
ሊቬዎች ኮንግራ ውጤቱ ይገባቹሃል
ጫወታውን ስናየው ገና ከአስላለፉ ነበር የተሸነፍነው የዚህን ጫወታ ውጤት ሙሉ በሙሉ የአሰልጣኙ ነው ሃላፍትናውን የሚወስደው
ምክንያቱም ለሊቨርፑል አይነት ከባድ ቡድን የሚያሰልፈውን ተጫዋች እንኳን ለይቶ የማያውቅ የወረደ አሰልጣኝ ነው በዚህ ሰው እሰከዛሬዋ ቀን ድረስ ተስፋዬ ጫፍ ድረስ ነበር ግን ከንግዲህ ቡሃላ ዋንጫውን ቢያነሳ የማለተማመንበት አይነት ሰው ሆኖ አግንቼዋለው
ወደዋናው ነጥብ ስመጣ የሊቬን አይነት ቡድን ስትገጥም አይደለም አሰላለፍ የምትቀይረው ቢያንስ አሰላለፍ የመቀየር እቅድ ካለው ቀለል ባሉ ክለቦች ላይ ነበር ሞክሮ ተጫዋቾቹ ይህን አሰላለፍ እንዲለምዱት ማድረግ ይጠይቃል
በርግጥ እስካሁን የገጠምናቸው ቡድኖች ቀለውን ነበር እያልኩ አይደለም ግን በለመዱት አሰላለፍ 4 2 3 1 ን ነበር መጠቀም የነበረበት የዛሬው 4 3 3 አሰላለፍ በለፉት ጫወታዎች ምርጥ የነበረውን ሴባሎስን እንኳን ከጫወታውያደረገው ውጪ አድርጎታል
ለምሳሌ የተሰለፈበት ቦታ ምቾት አልሰጠውም ስለነበር ወደሇላ እና ወደማሃል እየተመለስ ለመጫወት ሲሞክር ነብር ሌላው ደግሞ ይህ አሰላለፍ ነው ላካዜቴን ጫወታውን ከመጀመሪያው እንዳይጀምር
ሌላው ደግሞ በቴክኒኩ ብቻ ሳይሆን በአካል ብቃቱ የዳበሩ ተጫዋቾችን መጠቀሙን ትቶ ዊሎክን ያለ አግባብ ከመጀመሪያው ማስጀመሩ ሌላኛው ትልቁ ስትቱ ነው ዊሎክ ምርጥ ማደግ የሚችል ተስፈኛችን ነው ይህን ልጅ በእንደዚህ አይነት ጫወታ ላይ አይደለም ሪስክ ወስደህ የምታጫውተው
ሌላኛው ደግሞ ከሚገባው በላይ ጎንዶዚ ላይ ያለው እምነት ነው ይህን ጎንዶዚ ላይ ያለውን እምነት ቀንሶ ማሃል መዳው ላይ ቶሬራንና ዣካን አጣምሮ ፊት አጥቂውን በላካና በኦባ ፔፔን አድርጎ ሴባሎስን 10 ቁጥር ላይ ማድረግ ይችል ነበር
ኦዚል ቢኖር ኦዚልን 10 ቁጥር ላይ አድርጎ ሴባሎስን ከቶሬራ አጣምሮ ቢሆንም የተሻለ ነገር ልናይ እንችል ነበር ይህን ሁሉ ማድረግ እየቻለ አጉል ልፈላሰፍ ባይ ለመፈላሰፍ እንኳን ጫወታዎችን መመርጥ የማይችል አሰልጣኝ ሆኖ አግንቼዋለው
ሌላው የተከላካይ ክፍሉ ላይ ምንም ተቃውሞ የለኝም አማራጭም የለም የሚጠበቀው ነው እና የተከላካይ ክፍላችን ግን ከበፊቱ የተሻለውን የተከላካይ ክፍል ማየት ችያለው ምንም እንኳን በቡድኑ ድክመት 3 ጎሎችን ብናስተናግድም የተረጋጋ ሆኖ አግንቼዋለው ዴቪድ ልዊዝ ስተቱ እንዳለ ቢሆንም የተከላካይ ችግራችንን ቀርፎልናል ለማለት ነው
እኔ ግን የሚያሳዝነኝ ይህ ቡድንና አሰልጣኝ አንድም ቀን ምርጥ 11 ዳቸውን ሳይመርጡ ግዜው እየሄደ መሆኑ ነው ለማየት ያብቃቹህ ኤምሬ መቼም ምርጥ 11 መስራት አይችልም
ምክንያቱም የዛሬውን ጨምሮ ያለፉትን ሶስት ጫወታዎች መርጦ ማዘጋጀት ይችል ነበር አንዴ ፊትነሱ ሙሉ አልሆነም አንዴ ከተጫዋችች ጋር ሰጣ ገባ ውስጥ ይገባና በህምም ምክንያት እያለ ቡድኑን እየጎዳው እንደሆነ ይሰማኛል
ኦዚል መመለስ አለበት ቡድኑን በአግባቡ እየመራ ምርጥ 11 ዱን መምረጥ ግድ ይለዋል የራሱን ክብር በተጫዋቾች ላይመሸነፍ ከፍ ለማድረግ ከመሞከሩ ይልቅ ለቡድኑ ውጤት የሚጠቅመውን ማድረግ አለበት ባይ ነኝ
በተረፈ ማንኛውም ቡድን ላይ በኳስ አለም መሸነፍና ማሸነፍ ያለ ቢሆንም በአሰልጣኝህ እንዝላልነት ያበሳጫል ሊቬዎች በተለይ በመጀመሪያው 45 እና በሁለተኛው 45 እሰከ 70ኛው ደቂቃ መሰለኝ ባልሳሳት በጣም ቀለል ያለ ልምምዳቸውን ነበር የሰሩት አሁንም በድጋሚ ሊቬዎች እንኳን ደስ አላቹህ
@onlyarse
ቀጣይ ሳምንት እሁድ
Arsenal vs Tottenham
የዛሬው የቶትንሃም ሽንፈት ለመድፈኞቹ ጥሩ ነገር አለው ምክንያቱ ሁለቱም የለንደን ክለቦች መሸነፋቸው ለአርሴናል ለቀጣይ ጨዋታ በሞራል እንዲጫዎት ያደርጋል ግን ኡናይ ኤምሬ የአሰላለፍ ስተት ከፈፀም ቶትንሃም ቀላል አይፈትነንም
@onlyarse
▪️እውነቱን ለመናገር አርሰናል ድንቅ ተጫዋች አስፈርሞዋል።በጫወታው ከማንም በላይ ጎልቶ ወቶዋል በመጀመሪያ የቋሚነት አሰላለፍ ላይ እንዲ አይነት ድንቅ ብቃት በማሳየቱ ሊደነቅ ይገባል።እውነት አርሰናል ሁነኛ የመስመር ተጫዋች አግኝቶዋል።

በአውኑ ወቅት የአለማችን አይደፈሬው ተከላካይ የሚባለውን ቨርጂል ቫንዳይክን ሲፈትነው አምሽቶዋል።ከፈረሳይ ሊግ መቶ ቶሎ አይላመድም ሚሉ ወሬዎች ሲናፈሱ ቢቆዩም ፔፔ ግን ድንቅ ብቃቱን አስመልክቶዋል።

የአርሰናል መሸነፍ እንደ ምክንያት ሚታየው የአሰልጣኙ የቴክኒክ ችግር ነው እየተባለ ነው።ለጨዋታው ማይመጥኑ ተጫዋቾችን በማሰለፍ።"ለኒኮላ ፔፔ ከ ኦባምያንግ ይልቅ ላካዜት ይሻለዋል"

በባለፈው ጨዋታ 82' ደቂቃ ላይ ወደ ሜዳ የገባው ላካዜት ሙሉ ጨዋታውን ቢሰለፍ ኖሮ ማጥቃቱ ላይ አርሰናል በጣም የተሻለ ይሆን ነበር። ከኦባምያንግ የተሻለ የአጨራረስ ብቃቱን እናይ ነበር አርሰናል ፕረስ አርጎ እንዲጫወት ትልቁን ስራ ሚሰራው ደግሞ ቶሬራ ነው ይህ ኡራጋዊ አማካኝ በአንድም ጨዋታ ላይ ቋሚ ሆኖ አልጀመረም በሱ ምትክ ብዙ ልምድ የሌለውን ማትዮ ጎንዶዚ የኤምሬ ተቀዳሚ ምርጫ ሆኖዋል። ኤምሬ ግን ምን አስበው ነው......🤔በቀጣይስ የሰሜን ለንደን ደርቢ አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ ምን አይነት ፎርሜሽን ያሳዩን ይሆን። በአሁኑ ሳምንት ትችት ስለደረሰባቸው ጥሩ ፎርሜሽን ያሳዩናል ብዬ እገምታለው።

"SHARE" @onlyarse
▪️ትችት ሁሌ ከአፉ የማይጠፈው የSky Sport ተንታች ቶምሰን ቫርድ እንዲ ሲል ተደምጦዋል።አርሰናል እንዲሸነፍ ዋናውን ሚና የተጫወቱት ሁለቱ ፀጉራሞች ናቸው።ዴቪድ ሊውዝ እና ማትዮ ጎንዶዚ በቶተንሀሙ ጫወታ ላይ እነዚን ተጫዋቾች ሚሰለፉ ከሆነ እመኑኝ አርሰናል የአሁኑን ሳምንት ጫወታ ይደግመዋል።ግን እንደኔ እይታ ሁለቱንም ተጫዋቾች ቁጭ ማድረግ መፍትሄው ነው።ሲል ተደምጦዋል። እኔ ግን የምለው ስተት በእግር ኳስ አለም ያለ ነገር ነው ከስተታቸው ተምረው በቀጣዩ ጨዋታ ጥሩ ነገር ያሳዩናል ብዬ እገምታለው።

"SHARE" @onlyarse