Nigat Media
132 subscribers
520 photos
22 videos
277 links
Nigat Media ያልተዛባ መረጃን በተለየ አቀራረብ!
👉 https://www.nigatmedia.com
👉 https://www.am.nigatmedia.com
👉 https://www.facebook.com/nigatmedia1
👉 https://www.youtube.com/nigatmedia
Download Telegram
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ መሸሻቸው ተሰምቷል። ርዕሰ መስተዳድሩ ከባህር ዳር ከተማ ሸሽተው ወደ አዲስ አበባ ከገቡ አንድ ወር እንዳለፋቸው የተገለፀ ሲሆን፣ ከሌሎች የክልሉ አመራሮች ጋር እንዳይገናኙ ሆነው ከጥቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የሚሰጣቸውን መመሪያ እና መግለጫ እንዲያስተላልፉ ተደርገዋል ነው የተባለው።

በትላንትናው እለት በዶ/ር ይልቃል ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤም ከአዲስ አበባ ርዕሰ ምስተደሰድር ቢሮ ተዘጋጅቶ የወጣ መሆኑም ነው የተነገረው።
የሲዳማ ኤጄቶ ለአማራ ፋኖ የላከው መልዕክት‼️

አንባገነኑ የብልፅግና መንግስት ከኦሮሞ ውጭ ያሉ ማንነቶችን ከምድር ገፅ ለማጥፋት የወጠነውን ውጥን እኛ የሲዳማ ኤጄቶ አጥብቀን በመቃዎም ከጀግናው አማራ ፋኖ ጎን በመቆም አገራችንን ከብተና ለመታደግ እንደሚንሰራ ለወንድም ፋኖ ማሳወቅ እንፈልጋለን ።

የተከበረው የአማራ ህዝብም የውስጥ ልዩነቶችን ወደጎን በመተው የጋራ ጠላቱ የሆነውን ብልጽግና አሽቀንጥረው ለመጣል በተባረሩ ክንዶች ትግል እንዲያደርግ እናሳስባለን።

እኛም የሲዳማ ህዝብና ኤጄቶ ባለማወቅ የተሸከምነውን የኢትዮጵያ ጠላና ተገንጣይ ብልጽግናን ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ለመቅበር ከየትኛውም ግዜ በላይ ተዘጋጅተናል ትግልም ጀምረናል ።
ሰበር ዜና‼️

አርቲስት ዳኘ ዋለ አሁን በአዲስ አበባ ከተማ ኡራኤል አካባቢ መኪናውን እያሽከረከረ ሲጓዝ በመንግስት ደህንነቶች ታፍኖ ተወስዷል።
ሰበር መረጃ‼️
👉 የህዝብ እንደራሴው ታሰሩ‼️

ዛሬ ምሽት ፌደራል ፖሊስ ያለመከሰስ መብት ያላቸውን የፓርላማ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለን  እየደበደበ ከቤታቸው መውሰዱ ተሰምቷል።
ሰበርርርርር . . .‼️

ከወራት በፊት ከ500 በላይ ሰዎች የተገደሉበት ደብረ ኤልያስ ወረዳ በፋኖ ቁጥጥር ስር መግባቱን ሰምተናል።
# መረጃ
በትላንትናው እለት ከወልዲያ ዩኒቨርሲቲ 12ኛ መልቀቂያ ፈተና ጨርሠው ሲመለሡ በመንግስት ፀጥታ ሀይሎች የታገቱ አበበ መኮንን፣ ጀግናው አስቻለው፣ ደሴው ብርሀኑ እና ለጊዜው ስማቸው ያልታወቁ አንዱ ከብልባል አንድ ከወደብዬ ቀበለ የመጡ ተማሪዎች ተለቀዋል ቢባልም እስካሁን ከቤተሰቦቻቸው አልተገናኙም።

ፈጣንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
👇👇👇
t.me/nigat_media1
ባህር ዳር ክተት አውጃለች🔥🔥

ከሳተላይት ዋይ ፋይ በቀር ባህር ዳር ኢንተርኔት ስለተቋረጠ ማህበራዊ ሚዲያ አይሰራም። ሆኖም በአሁኑ ሰአት የባህር ዳር ህዝብ ድባንቄ ተራራን ለመቆጣጣር ትንቅንቅ እያደረገ ይገኛል።

አቅም ያለው ሁሉ ወደቦታው በመሄድ እንዲያግዝ ለምታውቁት ሰው ሁሉ እየደወላችሁ ወደ ድባንቄ ተራራ በመሄድ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አድርጉ ብላለች!!

ለበለጠ መረጃ👇👇
http://t.me/nigat_media1
ከሸዋ ህዝባዊ ጥምር ጦር ደብረብርሀን የተሠጠ መግለጫ!!

በበርካታ አቅጣጭ የመጣውን የአብይን ቡድን በሚያስደምም ጀግ ንነት ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቀን ከፊት የመጣውን ኃይል ደምስሰን ከተ ማችን መቆጣጠራችንን ይታወቃል::

በመሆንም ቡድን የደረሰበትን ውርደትና ኪሳራ ለማካካስ በማሰብ
በርካ ሀይል ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢወች በመሰብሰብ የሀገር  መከላከያ ዩኒፎርም በማልበስ በበርካታ ከባድ መሳሪያ ታጅቦ
ወደ ከተማው መግቢያ በሮች በማስጠጋት እንቅስቃሴዎች መጀ መሩ እውን ነዉ።

ይህ ኃይል አማራ ጠልና ለአማራ ህዝብና ከተሞች ምንም ርህራሄ የሌለው ፈሪ ግን ጨካኝ ቡድን:ለንፁሃን ለሴትና ለህፃናት በአጠቃ ላይ ሲቪሊያን ላይ በብዙ እጥፍ የሚከፋ ኃይል በመሆኑ ምክንያ ት እጅግ ብስለት ስክነትና ለህዝባችን እውነተኛ አሌኝታነታችንን ለማሳየት በማሰብ ያለምንም ቶክስ ልውውጥ በኃይል በቀላሉ የተቆጣጠርነውን ከተማችንን በሰላም ለቀን ወሳኝ ስትራቴጅካዊ
ቦታን ይዘን እንገኛለን።

ህዝባችን እንዲያውቅልን የምንፈልገው እውነት ተቆጣጥረን የለቀ ቅነውን ከተማ አይደለም የትኛውንም ከተሞች በፈለግን ሰዓት የመ ቆጣጠር አቅሙ እንዳለንና የትኛውም ቡድን ሊከለክለን እንደ ማይ ችል ማወቅ ግን ይኖርበታል።

ነሐሴ 2/2015
ሸዋ ደብረብርሀን
በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ያለው የኦህዴድ ጉዳይ ፈጻሚ ጦር ተነቅሎ ወደአማራ ክልል ገብቷል። የሶማሊያን ድንበር የሚጠብቅ ሠራዊትም ተነቅሎ መጥቷል። የሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና የኬንያ ድንበር ጠባቂዎች ሁሉ አሁን ድንበሩን ክፍት አርገው ወደአማራ ክልል ገብተዋል ወይም እየገቡ ነው። ሌላው ቀርቶ የታላቁን ህዳሴ ግድብ እንኳ ያለጠባቂ ቀርቷል።  ይሄንን ሁሉ ማዝመት ያስፈለገው አማራጭ ስለሌለ ነው። ሌላው ሠራዊት አልቋል። ተበትኗል፣ ተማርኳል ወይም ተገድሏል። የአማራ ክልሉ ለየት የሚያደርገው ፋኖ በክብር ስርዓተ ቀብር ይፈጽማል።  ሠራዊት በማስጨረስ የታወቀው አብይ በትግራይ ጦርነት በተከተለው የተሳሳተ ስትራቴጂ ሰራዊቱ ሲያልቅ ሠራዊቴ አለቀ ሳይል የክልል ልዩ ሀይሎችን ነበር ያዘመተው። ፋኖ ፕሮፓጋንዳው ላይ ስለሌለበት አልተናገረውም እንጂ አሁን በመከላከያ የደረሰው እልቂት ትግራይ ላይ ደርሶ ከነበረውም የከፋ ነው።  ይሄንን መራር እውነት ወደፊት ሁሉም ይረዳዋል።

#ሙሉቀን ተስፋው
የጠላህን ህዝብ በግድ ካልገዛሁት ብለህ የንጹሃንን ደም እንደማፍሰስ ያለ ወንጀል በምድርም በሰማይም የለም። ይህ ደም እጃቸው ላይ ያለባቸው ሁሉ እንደ ቃየን ሲቅዘበዘቡና የሚሆኑትን ሲያሳጣቸው እያየን ነው።

Fasil Yenealem
የአንበጣ መንጋ‼️

በአፋር ክልል የተከሰተው የአንበጣ መንጋ በአረንጓዴ አሻራ በተተከሉ ችግኞችና ለእንስሳት ምግብ በሚሆኑ የደረሱ ተክሎች ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የክልሉ የእንስሳት፣ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው የዕጽዋት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀቢብ አብደላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ መነሻውን ከቀይ ባህር አካባቢ ያደረገው የአንበጣ መንጋ ከሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአፋር ክልል የትግራይ አጎራባች ዞኖች ላይ ተከስቷል፡፡
የምሽት መረጃ!

#AddisAbaba

አራት ኪሎ አካባቢ ውጥረት ነበር፣ ስልክም ኢንተርኔትም ለስዓታት ተዘግቶ ነበር አሁን ነው የተለቀቀው።
ሰበር ዜና

መከላከያ ተቆጣጥሬዋለሁ ሰላማዊ እንቅስቃሴው ተመልሷል እያለ በሚያቅራራበት ፍኖተሰላም ከተማ ውስጥ አደባባዩ ላይ አካባቢ የሚገኝ የነዳጅ ማደያ ላይ የድሮን ጥቃት በማድረስ በቁጥር ያልተገለፁ ንፁሃን ሰዎች ተገድለዋል።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በታጣቂዎች ጥቃት ከ10 በላይ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ መስከረም 20 እና 21 የብሄር ማንነትን መሠረት አድርገው ጥቃቱን የፈጸሙት፣ በርበሬ፣ ቆሮ፣ ራቾ፣ ሰለልኩላና ሳላይሽ በተባሉ የወረዳው የገጠር ቀበሌዎች ነው። ነዋሪዎች፣ ጥቃቱን የፈጸሙት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው ብለዋል።

በወረዳው ዋና መቀመጫ ግንደ መስቀሉ ከተማ የሠፈሩ የመከላከያ ሠራዊት፣ ፌደራል ፖሊስና የኦሮሚያ ክልል ጸጥታ ኃይሎች ጥቃቱን ለማስቆም በታጣቂዎቹ ላይ ርምጃ እንዳልወሰዱ ታውቋል።

በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መኾኑንና ኾኖም መንገዶች በመዘጋታቸው ለተጎጂዎች የሕክምና ዕርዳታ መስጠት እንዳልተቻለ በጉንደ መስቀሉ በአንድ የግል ጤና ተቋም የሚሠሩ ሐኪም ለዋዜማ ሬዲዬ ተናግረዋል።
"ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች ይመለሱልን" የአፋር ወጣቶች‼️

አፋር ክልል ኤላ-ውሃ ከተማ መውጫ ላይ ከ3:00 ጀምሮ መንገድ በድንጋይ ተዘግቶ ጎማ እየተቃጠለ ውሏል። ምክንያቱ ደግሞ ሁለት ወጣቶች በክልሉ የፀጥታ ሃይሎች ታፍነው ተወስደዋል፣ይመለሱልን የሚል ነው።

አብዱ ኤሊ ወሃ እና ሰዲቅ በድሩ የተባሉት ወጣቶች ሃሳባቸው ስለገለፁ ነው የታሰሩት ይፈቱ ሲሉ መንገዱን የዘጉት ፍትህ ጠያቂዎች ገልፀዋል። ከፌደራል መንግስቱ ጋር ምንም ችግር የለብንም ችግሩበየክልሉ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

ከ10:00 በኋላ መንገዱን ለማስከፈት የክልሉ ልዩ ሀይል ከአካባቢ አስተዳደሮች ጋር ሲመክሩ ቆይተው 12:00 መንገዱ መከፈቱን  ምንጮቼ ነግረውኛል።
"ከፈጣሪ ትዕዛዝ ተሰጥቶኛል" ያለ ፓስተር የጊምቢቹን ከተማ ስያሜ ለመለወጥ ሲያደርገዉ የነበረዉ ጥረት በከተማ አስተዳደሩ እንዲቋረጥ ተደረገ‼️

"ረዕይ ታይቶኛል" ያለ አንድ "የሀይማኖት መምህር" በሀድያ ዞን የምትገኘዉ የጊምቢቹ ከተማን ስያሜ ለመለወጥ ሲያደርግ የነበረዉ ጥረት እንዲቋረጥ መደረጉን የከተማ መስተዳድሩ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ባለሙያ አቶ አብነት ሞገስ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

የሀይማኖት መምህሩ አርፊጮ የሚባል የቤተ-እምነት መሪ ሲሆን 4 ወራትን ጾም ጸሎት በመያዝ ካሳለፈ በኋላ "ራዕይ ታይቶኛል ከፈጣሪም ትዕዛዝ ተሰጥቶኛል" በሚል የጊሚቢቹ ከተማ ስያሜን "ኤንጃሜ" በሚል ቀይሯል ነዉ የተባለዉ።

ለዚህም ደግሞ ጊምቢቹ የሚለዉ መጠሪያ ነዋሪዉን የማይወክል ነዉ በሚል ለመለወጥ እንዳነሳሳዉ አቶ አብነት ተናግረዋል።ይህም በቤተ እምነት ተቋሙ አንዳንድ ተከታዮች በኩል ተቀባይነት ያለዉ ጉዳይ ነዉ ያሉት አቶ አብነት ፤ ሆኖም የከተማዉ ነዋሪም ሆነ መስተዳድሩ በዚህ የስም ቅያሪ እንደማይስማማ ተናግረዋል። የከተማዋን ስያሜ ለመወለጥ ቢፈለግም በከተማዉ ም/ቤት ቀርቦ ድምጽ ሊሰጥበት ይገባል ብለዋል።

መምህሩ አዲስ ለከተማዋ የሰጠዉ ስያሜ በቅድሚያ በቤተ እምነት ተቋሙ አካባቢ የጀመረ ሲሆን በኋላ ታፔላ እና ባነር እንዲሁም ባንዲራ ጭምር በማሰራት በወጣቶች ማዘዉተሪያ ላይ ለጥፏል ብለዋል። ከዚህም ድርጊት በኋላ ነዋሪዉ በማህበራዊ ሚዲያዎች ተቃዉሞዉን በማሰማቱ የከተማዋ ከንቲባ በተገኙበት ድርጊቱ እንዲቋረጥ ተደርጓል ብለዋል።

በዛሬዉ እለትም የእምነት ተቋሙን መሪ እና ተከታዮች የከተማ መስተዳድሩ ተወካዮች ችግሩን በንግግር ለመፍታት መወያየታቸዉን አቶ አብነት ጨምረዉ ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡

Via ዳጉ_ጆርናል
ህወህሓቶች ሄርሜላ አረጋዊ ከስራ እንድትታገድ አድርግናል በማለት ጮቤ እየረገጡ ነው:: ይህ ለፍትህ ሃይሎች ሽንፈት ነው:: ለዚች ጀግና ያልሆንን ለማን ልንሆን ነው? አሁንም አልረፈደም:: አሜሪካ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ዛሬውኑ ከታች በተቀመጠው ስልክ እየደወላችሁ ለሄርሜላ ያላችሁን ድጋፍ ግለፁ: : ይህ የአፈና መንገድ ነገ በሁላችንም ላይ ይከሰታል:: ውጭም ሆነን በነፃነት ሰርተን እንዳንኖር ሊያደርጉን ነው? የእብሪታቸው ልክ ድንበር ተሻግሯል:: ገዢዎች ይህ መንገድ መስራቱን ካዩ ነገም እኛም እንተግብረው ማለታቸው አይቀርም::


URGENT‼️Call everyday! Call Congresswoman Waters’ DC office now 202-225-2201 She is from LA! Tplf ites have been calling so they may stop you and assume you’re calling on their side. 🚨 BUT MAKE SURE THEY KNOW YOU ARE CALLING IN SUPPORT OF HERMELA 🚨 Tell her she shouldn’t give into the mob that is attacking Hermela. We know exactly who they are. They’ve done it to us for decades.
Call her office now and let her know: 202-225-2201
Via Fasil Yenealem
የሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ጽ/ቤት የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ብሏል ብሏል። የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ታፍነዋል በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ሲል ጽ/ቤቱ ገልጧል።
የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ለባላገሩ ቴሌቪዥን

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ለባላገሩ ቴሌቪዥን የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ታውቋል። ቴሌቪዥን ጣቢያው በየትኛው ፕሮግራሙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንዳሰጠው ተነጥሎ አልተገለፀም።

Via - Wasu
ሰበር ዜና
======
ደብረብርሃን ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር  ስር ሆናለች :: የሰሜን ሸዋ  ዋና ከተማ የሆነችውን ደብረብርሃን ነፃ ያወጡት ጀግኖቹ ፋኖዎች:-
1- መብረቁ ብርጌድ
2- ጋጠው ብርጌድ እና
3- አስራት ወልደየስ ሻለቃ ናቸው::
በኦፕሬሽኑ የደብረብርሃን እና የአካባቢው ህዝብ ከፍተኛ ተጋድሎ ፈፅሟል::