STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
39.7K subscribers
11.1K photos
272 videos
452 files
1.94K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
180 ሺህ የሚጠጉ ዕጩ ተመራቂዎች በቀጣይ ወር የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

በ208 የትምህርት ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና መዘጋጀቱን በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው የመውጫ ፈተና፣ ከሐምሌ 03 እስከ 08/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወቃል፡፡

"የመውጫ ፈተና የሥርዓተ ትምህርቱ አካል ሆኖ ይቀጥላል" ያሉት መሪ ሥራ አስፈጻሚው፤ በተቀመጠው መመሪያ መሠረት ተፈትነው 50 በመቶና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች እንደሚያልፉ አስረድተዋል፡፡

የመውጫ ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን የሚሰጥ በመሆኑ የተማሪዎች ስም ዝርዝር ተልኮ ወደ ዳታ ማዕከል መግባቱንም ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎቻቸውን የምረቃ መርሃግብር ከመውጫ ፈተና በኋላ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲዎቹ ምርጫ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሲጠናቀቅ ማካሄድ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። #ኢፕድ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#Update

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተከስቶ የነበረዉ የፀጥታ ችግር ተቀርፎ ሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ስራ ተጀመረ

በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጠውን የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና አንፈተንም በሚል  በዋናው ግቢ በዉስጥ ተከስቶ የነበረዉ የፀጥታ ችግር ተቀርፎ ሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ስራ መጀመሩ ተገልጿል።

ከዩኒቨሲቲውም ሆነ የሚመለከታቸዉ የፀጥታ ተቋማት  እውቅና ውጪ ባልተፈቀደ ሁኔታ ሰኔ  03 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የተደረገውን ሙከራ ተከትሎ በዩኒቨርሲቲዉ ሆነ በሰዉ ላይ ሊደርስ የሚችል ጉዳት ለማስቀረት የፀጥታ ኃይሉ ህግ የማስከበር ተግባሩን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን  በጥቂት የማህበራዊ ሚዲያዎች የፀጥታ ችግር እንዳለና መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ላይ መስተጓጎል እንዳለ በማስመሰል የሚሰራጩ መረጃዎች  ሀሰተኛና ተቀባይነት የሌላቸዉ ናቸው ተብሏል።በመሆኑም የተማሪ ወላጆችና መላው ህብረተሰብ  መረዳት ያለባቸው ከተፈጠረው አነስተኛ ግጭት ውጪ በተማሪዎች ላይ ምንም የደረሰ ጉዳት የሌለ መሆኑን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ክፍል ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
15 የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በጊዜያዊነት ታገዱ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር 15 የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በጊዜያዊነት ማገዱን አሰታወቀ።

ከጥቅምት 14/2015 እስከ ታህሳስ 30/ 2015 ዓ.ም ድረስ 15 ኤጀንሲዎች ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምንም አይነት ሪፖርት አለማድረጋቸውን ገልጿል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ በላይ የዜጎችን መብትና ደህንነት እንዲጠበቅ በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በህግ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሰረት የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዜጎችን ለሥራ ስምምነት ወደተደረሰባቸው መዳረሻ ሀገራት ለመላክ ፍቃድ በመውሰድ ወደ ሥራ እንዲገቡ ያደርጋል፡፡

ፍቃድ ወስደው የሚሰሩ የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችም በአዋጅ ቁጥር 923/08 እና በማስፈፀሚያ መመሪያ መሰረት ሊያሟሉ የሚገባቸውን አጠቃላይ እንቅስቃሴያቸውን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማሳወቅ ይኖርባቸዋል፡፡

በአዋጅ ቁጥር 923/08 መሰረት ድርጊቱ የሥራ ፈቃድ ስረዛ የሚያስከትል መሆኑን ጠቅሶ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎችን ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ አልቻሉም፡፡

ስለሆነም ስማቸው ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎ ከድርጊታቸው መማር እንዲችሉ ከግንቦት 11ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለመጨረሻ ጊዜ ለሦስት ወራት ታግደዋል ብሏል።

(ኢ ፕ ድ)
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
Research paper ማማከር ጀምረናል።
How to choose research title?
How to write proposals?
How to generate essay?
How to check Plagiarism?
How to correct Advisor comments?
How to write research papers?
How to present and defense thesis papers?
How to conduct literature reviews:
How to select a research methodology:
How to collect and analyze data:
How to interpret research findings:

inbox via 👇👇👇
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
ለ 2015 ዓ.ም የማትሪክ ፈተና ብቁ መሆን አንድትችሉ የተዘጋጀው Grand Plan (መሪ እቅድ) ቪዲዮ በዚህ https://t.me/eTemariNetetemari.net ግሩፕ አንዲሁም https://t.me/edutech_plc ቴሌግራም ቻናል ላይ pin ተድርጎ ታገኙታላችሁ
Research paper ማማከር ጀምረናል።
How to choose research title?
How to write proposals?
How to generate essay?
How to check Plagiarism?
How to correct Advisor comments?
How to write research papers?
How to present and defense thesis papers?
How to conduct literature reviews:
How to select a research methodology:
How to collect and analyze data:
How to interpret research findings:

inbox via 👇👇👇
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
#Fake_News_Alert #የውሸት_ዜና_ማጋለጫ

የዘንድሮ ማለትም የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች ለመውጫ ፈተና ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ይወሰዳሉ በሚል በተለያዩ ቻናሎች እና ግሩፖች ላይ የሐሰት መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል።

ይሁንና ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ድረስ ተመራቂ ተማሪዎች ከአንዱ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንደሚዘዋወሩ የሚገልጽ ምንም አይነት መረጃ አላወጣም። ዩኒቨርሲቲዎችም ኮምፒውተሮቻቸውን እና መፈተኛ ክፍሎችን እያዘጋጁ ይገኛሉ።

ስለሆነም በሚኒስቴሩ የሚለቀቅ አዲስ መረጃ ካለ ቻናላችን አጣርቶ የሚያሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን ።

📡 STUDENTS NEWS CHANNEL 📡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ

📡 @NATIONALEXAMSRESULT 📡
🌟 የምስራች ለመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች 🌟

🔔 ለመውጫ ፈተና በብቃት የሚያዘጋጅዎ
       Mock እና Model  Exam
       Online ይለማመዱ!

አድቫንስድ የትምህርት ማማከር አገልግሎት ማዕከል ከአተርቴክ የቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ ጋር በመተባበር ፦

➭ በዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና መምህራን የተዘጋጀ፣
➭ የትምህርት ሚኒስቴርን የብቃት መስፈርት መሰረት ያደረገ፣
➭ ተገቢውን ሳይንሳዊ  የምዘና ሥርዓት የተከተለ፣
➭ ለአንድ ፕሮግራም ከ1,000 በላይ መለማመጃ ጥያቄዎችን የያዘ፣
ሁሉንም የፈተና ኮርሶች ያካተተ
ለእያንዳንዱ ጥያቄ መልስና ማብራሪያ
     የያዘ

➭ በየትኛውም ቦታ በማንኛውም ሰዓት የሚያገኙት የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) መለማመጃ አቀረበልዎ!

ለሙሉ መረጃው፡-

➧ www.http://elts.com.et ይጎብኙ፣
https://t.me/aec_ethiopia ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

#AdvancedEducationalConsultingCenter
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ የ8ኛ ክፍል እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።

የ 8ኛ ከፍል ፈተናን አስመልክቶ

ለፈተናው 490,167 ተማሪዎች ተዘጋጅተዋል ( ከዚህም ውስጥ ወንድ 260,807 እና ሴት 229,360 ናቸው )

በኦሮሚያ ክልል የ8ኛ ክፈል ፈተና የሚሰጥበት ቀን #ሐምሌ 26 እና 27/2015 መሆኑን አሳውቋል።

የ 12ኛ ክፈል ብሄራዊ ፈተናን አስመልክቶ የፈተና ፕሮግራሙን እንደሚከተለው ገልጸውታል።

በክልሉ 323,149 ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ፈተና በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ።

የፈተናው ፕሮግራም

👉ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፣
   
   - ሐምሌ 16 -17/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

- ሐምሌ 18, የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

- ከሐምሌ ከ 19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3'ት ቀናት ይሰጣል ።

- ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች

- ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

- ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

- ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይሰጣል።

- ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#Update

የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ለ 2015 ዓ.ም የማትሪክ ፈተና ብቁ መሆን አንድትችሉ የተዘጋጀው Grand Plan (መሪ እቅድ) ቪዲዮ በዚህ https://t.me/eTemariNetetemari.net ግሩፕ አንዲሁም https://t.me/edutech_plc ቴሌግራም ቻናል ላይ pin ተድርጎ ታገኙታላችሁ
በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን የትምህርት ማስረጃቸው እንዲጣራ በመደረጉ ተደናግጠው የተሰወሩ መምህራንን ፖሊስ እያደናቸው መሆኑ ተገለፀ‼️

የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በስልጤ ዞን የትምህርት ማስረጃቸው እንዲጣራ በመደረጉ ተደናግጠው የተሰወሩ መምህራንን አድኖ በመያዝ  ለፍርድ ለማቅረብ ብርቱ ክትትል እያደረኩ ነው ሲል አስታወቀ።

በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች በተለያዩ ሴክተር መስሪያቤቶች ተቀጥረዉ በሚሰሩ የአራት ሺህ አራት መቶ ሰባአራት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ እንዲጣራ በመደረጉ 67 መምህራን ተደናግጠዉ ስራቸዉን ጥለዉ መጥፋታቸዉ ተነግሯል።

ኮሚሽኑ ሀሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አቅርበዉ ከተቀጠሩ 82 መምህራኖች  ዉስጥ 28 መምህራንን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ አጣርቶባቸዋል ብሏል። ምርመራ ከተጣራባቸዉ 28 ተከሳሾች ዉስጥ ፍርድ ቤት ቀርበዉ የተቀጡት 13 ተከሳሾች ናቸዉ ሲልም አስታውቋል።

ነገር ግን የተቀሩት በፍርድ ቤት በዋስ ከተለቀቁ በኋላ አካባቢያቸዉን ጥለዉ የተሰወሩ በመሆኑ ተከሳሾችን አድኖ በመያዝ  ለፍርድ ለማቅረብ ብርቱ ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ የክልሉ ፖሊስ ገልጧል።

📡 STUDENTS NEWS CHANNEL 📡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ

📡 @NATIONALEXAMSRESULT  📡
Research paper ማማከር ጀምረናል።
How to choose research title?
How to write proposals?
How to generate essay?
How to check Plagiarism?
How to correct Advisor comments?
How to write research papers?
How to present and defense thesis papers?
How to conduct literature reviews:
How to select a research methodology:
How to collect and analyze data:
How to interpret research findings:

inbox via 👇👇👇
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች በተለይም በገጠር የመማር ማስተማር ሂደት ካቋረጡ ሦስት ዓመት የሆናቸው በርካታ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መኖራቸው ተገልጿል።

ለአብነትም በክልሉ በሰሜን ሸዋ ዞን ያያ ጉለሌ ወረዳ እንደ ጎደጀባ፣ ሸከኬ፣ ቀሬቶኬ፣ አሊዴራ እና አሬሬ በመሳሰሉ ቀበሌዎች በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት ከተቋረጠ ሦስት ዓመታት ማስቆጠሩን የአካባቢውን ነዋሪዎች ዋቢ አድርጎ ቪኦኤ ኦሮምኛ ዘግቧል።

በዚህም ምክንያት በዘንድሮ ዓመት የሚሰጠውን የስምንተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና እንደማይወሰዱ ነው የተገለጸው።

በዚህም የወረዳው የትምህርት ጽህፈት ቤት እንዳስታውቀው፣ በወረዳው ከሚገኙት አጠቃላይ 18 ትምህርት ቤቶች አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ስምንት ብቻ መሆናቸውን እና ቀሪዎቹ ባለው በሰላም ችግር ምክንያት ሙሉ ለሙሉ የመማር ማስተማር ሂደቱ አቁመዋል።

በተመሳሳይ በሆሮ ጉዱሩ ዞን አሙሩ ወረዳ በከተማ ያሉ ትምህርት ቤቶች ብቻ ትምህርት እየሰጡ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በገጠር የሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ትምህርት ማቋረጣቸው እና ከገጠር ወደ ከተማ መጥተው ያቋረጡትን ትምህርት ለመቀጠል የመሸኛ ደብዳቤ ማግኘት አለመቻላቸው ተመላክቷል።

እንዲሁም በወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት መረጃ መሰረት በወረዳው በሰላም ችግር ምክንያት ዘጠኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው አንጻራዊ ሠላም ባለባቸው የተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ብቻ 1 ሺሕ 270 ተማሪዎች ለስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንደሚቀመጡ ጠቀሰዋል።

በዞኑ ሥር ባሉ እንደ ጃርቴ፣ ኪረሙ እና አቤደምቦሮ በመሳሰሉ ወራዳዎችም ተመሳሳይ ችግሮች መኖራቸው ተጠቅሷል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
Research paper ማማከር ጀምረናል።
How to choose research title?
How to write proposals?
How to generate essay?
How to check Plagiarism?
How to correct Advisor comments?
How to write research papers?
How to present and defense thesis papers?
How to conduct literature reviews:
How to select a research methodology:
How to collect and analyze data:
How to interpret research findings:

inbox via 👇👇👇
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
በሃዋሳ ከተማ በተፈጸመው ከተማሪ ሜላት መሃመድ ጠለፋ ጋር በተገናኘ 8 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ፡፡

ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም ተማሪ ሜላት መሃመድ ከትምህርት ቤት ተመልሳ ቤት ልትደርስ ጥቂት ሜትሮች ሲቀራት በሁለት ተሽከርካሪ መጠለፏን ቤተሰቦቿ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡

ከዚህ የጠለፋ ድርጊት ጋር በተገናኘ 8 ተጠርጣሪዎች መያዛቸውንና እየተደረገ በሚገኘው ክትትልም ጠላፊውን በጥቂት ቀናት ውስጥ ይዘን ይፋ እናደርጋለን ሲሉ የተናገሩት የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ናቸው፡፡

በቅርቡ ተጠልፋ የነበረችውና ከቀናቶች በኃላ ነጻ የሆነችው ጸጋ በላቸውም ይሁን በተማሪ ሜላት መሃመድ ላይ የተፈጸሙት ጠለፋዎች በምርመራ በተረጋገጠው መሰረት ከዚህ በፊት በነበሩ ትውውቆች ላይ የተመሰረቱ እንጂ በማያውቁት ሰው የተፈጸመ እገታ አይደለምም ብለዋል፡፡

በከተማው በግለሰብ ደረጃ ከሚያጋጥሙ ጥቃቅን ወንጀሎች በስተቀር በክልሉ በሚነገረው ልክ የዝርፊያ እና እገታ ወንጀሎች እየተፈጸሙ አይደለም ሲሉም ገልጸዋል፡፡ እነዚህ ችግሮችም ለዜጎች የመኖር ዋስትናን ሊያሳጡ የሚችሉ ጉዳዮች አይደሉም ሲሉ ነዉ ሃሳባቸዉን የገለጹት፡፡

መንግስት የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ ግዴታው በመሆኑ የክልሉ የጸጥታ ሃይል አስፈላጊውን ተግባር እያከናወነ እንደሚገኝም አንስተዋል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
🌟 የምስራች ለመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች 🌟

🔔 ለመውጫ ፈተና በብቃት የሚያዘጋጅዎ
       Mock እና Model  Exam
       Online ይለማመዱ!

አድቫንስድ የትምህርት ማማከር አገልግሎት ማዕከል ከአተርቴክ የቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ ጋር በመተባበር ፦

➭ በዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና መምህራን የተዘጋጀ፣
➭ የትምህርት ሚኒስቴርን የብቃት መስፈርት መሰረት ያደረገ፣
➭ ተገቢውን ሳይንሳዊ  የምዘና ሥርዓት የተከተለ፣
➭ ለአንድ ፕሮግራም ከ1,000 በላይ መለማመጃ ጥያቄዎችን የያዘ፣
ሁሉንም የፈተና ኮርሶች ያካተተ
ለእያንዳንዱ ጥያቄ መልስና ማብራሪያ
     የያዘ

➭ በየትኛውም ቦታ በማንኛውም ሰዓት የሚያገኙት የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) መለማመጃ አቀረበልዎ!

ለሙሉ መረጃው፡-

➧ www.http://elts.com.et ይጎብኙ፣
https://t.me/aec_ethiopia ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

#AdvancedEducationalConsultingCenter
For Wolkite University Remedial students Final Exam Schedule


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
Update ‼️

በ 2015, የ 12ኛ ክፈተናን የሚወስዱ ተማሪዎች 869,765 ናቸው።

ከዚህ ውስጥ
      🪭 Natural Science 365,954 ተማሪዎች
      🪭 Social Science 503,812 ተማሪዎች ናቸው ።

በመጀመሪያ ዙር ፈተና የ Social Science ተማሪዎች

    🍬ሐምሌ 16 -17/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

    🍬ሐምሌ 18, የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

    🍬 ከሐምሌ ከ 19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3'ት ቀናት ይሰጣል ።

     🍬ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

በሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች

       🍢ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

        🍢ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

         🍢ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይሰጣል።

          🍢ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
Nifa silk.xlsx
558.6 KB
የ 2015 የ12 ክፍል ፈተና መፈተኛ ዩንቨርስቲዎች ምድባ

የሁሉም ክልሎች እንዲሁም ሁለቱ የከተማ መስተዳድሮች በውስጣቸው ባላቸው ወረዶች ተከፋፍለው ምደባው ተከናውኗል

አዲስ አበባ 2491-2502,2517-2526,2562-2620,2643-2662
ኦሮሚያ
621-1017,1029-1627,1818-1833,2252-2278,2503-2516,2527-2561,2662-2714,2730-2742
አማራ
45-311,326-380,401-620
አፋር5-44
ትግራይ 311-322
ሲዳማ 2743-2841
ቤ.ጉምዝ 385-400,1779-1816
ደቡብ 1834-2251
ጋምቤላ 2446-2502
ድሬዳዋ 2663-2671
ሀረሪ 1020-1026
ሱማሊያ 1628-1778,2715-2729
ከአገር ውጭ 2985-2987

#ማሳሰቢያ ከላይ ባለው ቁጥር መሠረት ወረዳቹን ስትፈልጉ (fx) ባለበት ተርታ ነው ሚጀመረው 5 አፋር ላይ ነው


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot