Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹
9.9K subscribers
18.4K photos
269 videos
16 files
507 links
This is the official Telegram page of Ministry of Urban and Infrastructure
Download Telegram
ዹኹተማና መሰሹተ ልማት ሚኒስ቎ር አመራሮቜ አዲስ በጾደቁ ፖሊሲዎቜ ዙሪያ ውይይት አደሹጉ

አዲስ አባባ፣ ነሐሮ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (ኹመልሚ)  ዹኹተማና መሰሹተ ልማት ሚኒስ቎ር  ዹኹተማ ልማት ፖሊሲ፣ ዚኮንስትራክሜን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ እና ዚቀት ልማት ፖሊሲ መጜደቃ቞ውን ተኚትሎ ዚጋራ ግንዛቀ እንዲኖር ዚሚያስቜል ዚሚኒስ቎ር መስሪያ ቀቱ አመራሮቜ ውይይት አድርገዋል፡፡

ፖሊሲዎቹ በ2030 ዚኢትዮጵያ ኚተሞቜ ለሀገራዊ እድገትና ብልጜግና ስኬት መሪ ሚና ያላ቞ው፣ ተወዳዳሪ፣ ዘላቂ፣ ምርታማና ለስራና ለኑሮ ምቹ ሆነው ማዚትን ያለሙ ና቞ው፡፡

መድሚኩን በንግግር ያስጀመሩት ዹኹተማና መሰሹተ ልማት ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ዎኀታ ክቡር አቶ ፈንታ ደጀን ዚኚተሞቜ እድገት በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚ መምጣቱን እና ኹላይ እስኚታቜ ያለው አመራር ትኩሚት ሰጥቶ ኹመደገፉ ጋር ተያይዞ ፖሊሲ ማሻሻልና ማዘጋጀት ውጀታማ ስራ ለመስራት ያስቜላል ብለዋል፡፡

ዹኹተማ ልማት ፖሊሲ ዓላማው አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ኚተሞቜ ውብና ጜዱ፣ ለነዋሪዎቻ቞ው ምቹ እንዲሆኑ ማድሚግ፣ ዚዜጎቜን ኑሮ ለማሻሻልና ዚስራ እድል ዚሚፈጥሩ ኹመሆኑም ባሻገር ፈጣን እና ተደራሜ አገልግሎት እንዲኖር ዚሚያደርግ እንደሆነ ተናግሚዋል፡፡

በኹተማና መሰሹተ ልማት ሚኒስ቎ር ዚፖሊሲና ስትራ቎ጂ ጥናትና ምርምር  ስራ አስፈጻሚ  አማን አሰፋ(ዶ/ር) አዲሱ ዹኹተማ ልማት ፖሊሲ ዓላማ ኚተሞቜ በፕላን ዚሚመሩ፣ በመሰሹተ ልማት ዚተቀናጁ፣ ቀልጣፋና ዘላቂ ልማት ዚሚሚጋገጥባ቞ው አካታቜ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ብልጜግና እንዲኖራ቞ው ማድሚግ ታሳቢ ያደሚገ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ዚኮንስትራክሜን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ እና ዚቀት ልማት ፖሊሲ በዝርዝር ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባ቞ዋል፡፡
❀1
በሚኒስ቎ር መ/ቀቱ ዚክሚምት በጎ ፈቃድ ሥራዎቜና በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ዚሪፎርም ሥራዎቜ ላይ ዚጋራ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሮ 25/ 2018 ዓ.ም፣ (ኹመልሚ) በአሹንጓዮ አሻራ፣ በCOP 32 ቜግኝ ተኚላ፣ ዹአቅመ-ደካማ ዜጎቜን ቀት በማደስና መልሶ ግንባታ  በተማሪዎቜ ዚትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ በማዕድ ማጋራት፣ በደም ልገሳ፣ ወጣቶቜን በማነቃቃት፣ እንዲሁም በሆስፒታል ለሚገኙ ህሙማን ተደሹገ ዚንጜህና መጠበቂያ ዕቃዎቜ ድጋፍ እና መሰል ዹበጎ አድራጎት ስራዎቜ በ2018 በጀት ዓመት በሚኒስ቎ር መ/ቀቱና በተጠሪ ተቋማት ትብብር ዚተሰሩ ስራዎቜ ጥቅል ሪፖርት ቀርቩ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በተመሳሳይ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ዚሪፎርም ስራዎቜ ላይ ያተኮሚው ዚሪፎርም ጥናት ዚቅድመ-ዝግጅት ስራና ጥናቱን አጠናቆ ወደ ትግበራ ምዕራፍ ለመሾጋገር እዚተሰሩ ያሉ ዚቅድመ-ዝግጅት ስራዎቜ ያሉበት ደሹጃ ዝርዝር ሪፖርትም ለውይይት ቀርቧል። ዚሲስተም ልማትና በዘርፉ ወደ መሶብ አገልግሎት ለመግባት ዚተለዩ ስራዎቜና ያሉበትን ሁኔታ ዹተመለኹተ ሪፖርት ቀርቩ ዚጋራ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ክቡር ሚኒስትር ዎኀታ አቶ ፈንታ ደጀን በመሩትና ክቡራን ሚኒስትር ዎኀታዎቜና ዚሚመለኚታ቞ው ዚስራ ክፍል ኃላፊዎቜና ባለሙያዎቜ በተሳተፉበት በዚሁ መድሚክ ላይ በቀጣይ ዚጳጉሜ ቀናት ዹበዓል አኚባበርን በተመለኹተ ሚኒስ቎ር መ/ቀታቜን ጳጉሜ 2 ዚማንሰራራት ቀንን ኚሌሎቜ ተቋማት ጋር በትብብርና በቅንጅት ለመስራት ስለሚቻልበት ሁኔታ መሚጃዎቜ ቀርበው ዚጋራ ግንዛቀ ተይዞባ቞ዋል፡፡

በመጚሚሻም ክቡር አቶ ፈንታ ደጄን በሰጡት ዚማጠቃለያ አስተያዚት ዚቀሚቡት ሪፖርቶቜም ሆነ ዚተሰሩ ስራዎቜ ውጀት በጥቅሉ ሲታይ ተቋማቜን ያለበት ዚአፈጻጞም ደሹጃ ጥሩ ዚሚባል እንደሆነና ቀሪ ስራዎቜ በተያዘላ቞ው ጊዜ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጾው ሚኒስ቎ር መ/ቀቱ ዹተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈጾም እስካሁን ድሚስ ኚተጠሪ ተቋማት ጋር ተቀራርቊ በመስራት ሚገድ ያደሚገው ጉዞ ውጀታማ እንደሆነ ተናግሚዋል፡፡ 
❀4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮጵያ 🇪🇹 በአኒሜሜን ጥበብፀ
‎ እጅግ ማራኪ ውበት፣ ዹማይደበዝዝ ዚታሪክ ትውፊት እና ድንቅ ብዝሃነት ያላት ምድር።

‎ዚሀገሬ ልጆቜ ዚኢትዮጵያን ድንቅ ዚብዝሃነት ውበት ትጎበኙ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ!
ዚፒያሳዎቹ ወግ፡ ኚዘመናዊነት ማዕበል እስኚ ዚኢኮኖሚው ሞተር

«ፒያሳ» ዹሚለው ቃል በኢትዮጵያ ዹኹተማ ሥነ ሕንጻ እና ማኅበራዊ ታሪክ ውስጥ ኹቀላል ዚስፍራ መጠሪያነት እጅግ ዚራቀ ትርጉም አለው።

ፒያሳዎቜ ዚኚተሞቜ ዚልብ ትርታ፣ ዚባህል መስተጋብር፣ ዚንግድ ማዕኹል እና ዹዘመን መሻገሪያ ሕያው ድልድዮቜ ና቞ው።

ታዋቂው አሜሪካዊ ዚታሪክና ዹኹተማ ባህል ተቺ ሉዊስ ሙምፎርድ ኹተማን ሲገልጻትፀ ኹተማ በተፈጥሮ ውስጥ እንዳለ ዋሻ ወይም ዚጉንዳን ክምር ያለ እውነታ ብቻ ሳትሆንፀ በተመሳሳይ ጊዜ ዹሰው ልጅ ዹንቃተ-ህሊና ዚጥበብ ሥራ ጭምር መሆኗን ያነሳል።

አእምሮ በኹተማ ውስጥ ቅርፅ ይይዛልፀ በምላሹም ዹኹተማ ቅርጟቜ ዚአንድን ማኅበሚሰብ አእምሮ ይቀርጻሉ። ሙምፎርድ እንደሚሞግተው ኚተሞቜ ዹሰውን ልጅ ሥልጣኔና ማኅበራዊ ትስስር ዚሚመግቡ ሕያው ዚኪነ-ጥበብ መድሚኮቜ ና቞ው።

ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ ኚተሞቜ በኹፍተኛ ፍጥነት እዚተተገበሚ ባለው ሀገራዊ ዚኮሪደር ልማት እና ዹኹተማ ዝመና ፕሮጀክት ምክንያት ዚሀገሪቱ አንጋፋ ዚሆኑት ዚአዲስ አበባ እና ዚሀዋሳ ፒያሳ ሰፈሮቜ ዚትናንት ዚጥበብና ዚማኅበራዊ ትስስር ትዝታ቞ውን ኚዛሬው ዘመናዊ መልክ፣ ምቹ ዚኑሮ ዘይቀ እና ግዙፍ ዚኢኮኖሚ አቅም ጋር እያዋሃዱ አዲስ ዚታሪክ ምዕራፍ እዚጻፉ ይገኛሉ።

ዚአዲስ አበባ ፒያሳ፡ ኚትዝታ ማዕኚልነት ወደ ግዙፍ ዚኢኮኖሚና ዚግብይት እምብርት..

ዚአዲስ አበባ ፒያሳ ዚዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ መናገሻ ናት። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ተቆርቁራ፣ በጣሊያን ወሚራ ወቅት ዹተለዹ ዚስነ-ሕንጻ ገጜታን ዚተላበሰቜው ይህቜ ሰፈርፀ በሲኒማ ቀቶቜ፣ በጥንታውያን ዹወርቅ ቀቶቜ እና በስፖርት ካፌዎቜ ዚምትታወቅ ዹኹተማዋ «ነፍስ» ናት።

ዚትናንቷ ፒያሳ ዹፍቅርና ዚውበት ማዕኚል፣ ግብይት ዚሚደራባትና በሁሉ ተወዳጅ ሰፈር ነበሚቜ። አሁን ግን ዚኮሪደር ልማቱን ተኚትላ ፒያሳ ፊቷን ሙሉ በሙሉ ወደላቀ ዚኚተሜነት ደሹጃ ተቀይራለቜ።

ዛሬ ላይ ፒያሳ ዚመንገድ ማሳለጫ ብቻ ሳትሆን፣ ግዙፍ ዚኢኮኖሚና ዚሥራ ዕድል ፈጠራ ሞተር ሆናለቜ።

በግርማ ሞገስ ዹቆመው ዚዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ አዲሱ ዚዓድዋ ገበያ ማዕኹል እና ዘመናዊው ዚትራንስፖርት ተርሚናል አካባቢውን ወደ ኹፍተኛ ዚንግድና ዚኢንቚስትመንት ማዕኚልነት አሞጋግሚውታል።

እነዚህ ዘመናዊ ዚግብይት ማዕኚላት በሺዎቜ ለሚቆጠሩ ወጣቶቜ ዚሥራ ዕድል ኚመፍጠራ቞ውም ባሻገር፣ ሞማቹ ማኅበሚሰብ በአንድ ማዕኹል ዹተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ አስቜለዋል።

ቀድሞ ዹነበሹውን መጹናነቅ በማስቀሚትፀ ሰፋፊና ደሹጃቾውን ዹጠበቁ ዚእግር ጉዞ መንገዶቜ፣ ደኅንነታ቞ው ዹተሹጋገጠ ዚብስክሌት መስመሮቜ፣ እንዲሁም ነዋሪው አዹር ዚሚቀበልባ቞ው አሹንጓዮ ፓርኮቜ ዚፒያሳን ዚድሮ ድባብ ወደ ዘመናዊ ዚቅንጊት እና ዚዕሚፍት መዳሚሻነት ቀይሚውታል።

ዚአካባቢው ነዋሪዎቜም ዚድሮዋን ፒያሳ ትዝታ እያደሱ፣ ዛሬ ላይ ዚሚታዚው ንጜህና፣ ውበትና ሥርዓት ያለው ዚንግድ እንቅስቃሎ ለትውልድ ዚምትመቜ ዘመናዊ ኹተማን ማስሚኚቡን ይመሰክራሉ።

ዚሀዋሳ ፒያሳ፡ ዚጥበበኞቜ ማሚፊያ እና ዚስማርት ሲቲ ጉዞ

ኚአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ስናመራ ዚምናገኛት ዚሀዋሳ ፒያሳ ደግሞ ዚራሷ ዹሆነ ዹተለዹ ዚታሪክ ውበትና አዲስ ዹዝመና ጉዞ አላት።

በ1950ዎቹ ዚተመሠሚተቜው ሀዋሳ፣ ኹሐይቁ በሚነፍሰው ቀዝቃዛ አዚር፣ በብስክሌት ተጠቃሚዎቿ፣ በሰላማዊ ማኅበራዊ ኑሮዋ እና በቡና ባህሏ ትታወቃለቜ። ይህቜ ኹተማ በታዋቂ ሀገር በቀል ኚዋክብት እይታ ስትገለጜ ይበልጥ ደማቅ ትሆናለቜ።

ለምሳሌ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም ዹኹተማዋን እድገት በምድራዊት ገነት መስለው፣ "ሀዋሳ ለእኔ ጥሩ አትክልተኛ እንዳገኘው አይነት ዚአትክልት ሥፍራ ናትፀ ኃላፊነት ዚወሰደፀ በተገቢው መልኩ ውሃ ዚሚያጠጣ እና ዚሚኮተኩት አካል ያላት ምርጥ ኹተማ"ሲሉ አሞግሰዋታል።

ዹዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በበኩላ቞ው "ዚትም ብትሆን መንፈስህን ታድሳለህ... ዚተሞላሚነት ሥራዎቌ ንድፈ ሃሳብ ዚተገኙት በዚህቜ ኹተማ ለማሹፍ ስመጣ ነው" በማለት ዚሀዋሳን ዚፈጠራ ማነቃቂያነት መስክሚዋል።

ዛሬ ላይ ይህቜው ዚሀዋሳ ፒያሳ፣ በኹተማዋ እዚተተገበሚ ባለው ዚኮሪደር እና ዹመሠሹተ ልማት ግንባታ አማካኝነት ወደ ስማርት ሲቲ እዚተለወጠቜ ትገኛለቜ።

ዚድሮዎቹ ዝቅተኛ ሕንጻዎቜ ቊታ቞ውን ለባለብዙ ፎቅ ሆ቎ሎቜ፣ ለዓለም አቀፍ ደሹጃ ላላቾው ዚገበያ አዳራሟቜ እና ለዘመናዊ ዚንግድ ኮምፕሌክሶቜ ለቀዋል።

ይህ ዚንግድ መሠሹተ ልማት መስፋፋት ሀዋሳን ዚሲዳማ ክልል ዋነኛ ዚቱሪዝምና ዚኮንፈሚንስ ማዕኹል ኚማድሚጉም በላይፀ ዚአካባቢውን ኢኮኖሚ በማነቃቃት ለበርካቶቜ ዚሥራ ዕድል ፈጥሯል።

ዚጎዳናዎቹ መብራት፣ ሰፋፊ ዚእግሚኛ መንገዶቜ እና አሹንጓዮ ልማት ነዋሪውም ሆነ ጎብኚው ያለምንም ስጋት ሌሊትና ቀን እንዲንቀሳቀስና እንዲገበያይ ምቹ ሁኔታን ፈጥሚዋል።

ኚአዲስ አበባ እና ኚሀዋሳ ዚፒያሳ ዝመናዎቜ ጀርባ አንድ ትልቅ ሀገራዊ ዹኹተማ ፕላን ፍልስፍና አለ። ይኾውም «ዚመደመር መንግሥት» በተሰኘው መጜሐፍ ላይ በግልጜ እንደተቀመጠው፣ መገንባት ዹምንፈልጋቾው ዚአዲሱ ዘመን ኚተሞቜ አካታቜነትን ማዕዘን ድንጋይ ያደሚጉ መሆን አለባ቞ው።

በነባር ኚተሞቜ እድሳትም ሆነ አዳዲሶቜን ኚመገንባት አኳያ ለአይበገሬነት ቅድሚያ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ዹመሠሹተ ልማት ዝርጋታዎቜ ለአዹር ንብሚት ለውጥ ዚማይበገሩ ሆነው መታቀድና ዹኹተማ ደኖቜን ጚምሮ አሹንጓዮ መሠሹተ ልማቶቜን ማካተት አለባ቞ው ይላል መጜሐፉ።

በመሆኑምፀ ዛሬ ላይ በሁለቱ ፒያሳዎቜ ዹምናዹው ዚጎዳና ማስፋፋት፣ ዚፓርኮቜ ግንባታ እና ዹመሠሹተ ልማት እድሳት እንዲሁ ለውበት ብቻ ዚተሠራ ሳይሆን፣ ኚተሞቹ ሁኔታዎቜን በቀላሉ ተላማጅ ዹሆነ ዹኹተማ አወቃቀር እንዲኖራ቞ው ታስቊ ነው።

ይህ ተላማጅ አወቃቀር ዚንግድ እንቅስቃሎን በማሳለጥ፣ ኢንቚስትመንትን በመሳብ እና ዚስነ ሕዝብ ለውጊቜን በቀላሉ በማስተናገድ ኚተሞቜ ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ዚኢኮኖሚ ዋልታ ሆነው እንዲያድጉ ያስቜላል።

አዲስ አበባ እና ሀዋሳ ዛሬ ላይ ዚሚያወጉን እውነት ቢኖርፀ ዚትናንቱ ጠባብ መንገድ እና ያሚጁ ቀቶቜ ለአሹንጓዮ አካባቢዎቜ፣ ለሰው ልጅ ምቹ ለሆኑ መንገዶቜ፣ ለዘመናዊ ዚግብይት ማዕኚላት እና ለአዹር ንብሚት ዚማይበገሩ መሠሹተ-ልማቶቜ ቊታ቞ውን መልቀቃቾው ዚማይቀሬ ዚዕድገት እና ዚስልጣኔ ጉዞ መሆኑን ነው።

ዚኢትዮጵያ ፒያሳዎቜ ትናንትም ዚፍቅር፣ ዚኪነ-ጥበብና ዚታሪክ መድሚክ ነበሩፀ ዛሬም ዚኢኮኖሚ ሞተር በመሆን፣ አካታቜነትንና አይበገሬነትን መሠሚት አድርገው በዘመናዊነት አሞብርቀው ዹነገዋን ውብ ኢትዮጵያ ዚሚኚትቡ ዚሥልጣኔ አውራ ጎዳናዎቜ ሆነው ቀጥለዋል።

#FBC
❀2
እዚተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ ዚሚያመላክቱ ስኬቶቜ ዚተመዘገቡበት ነው ።

ነሃሮ 27፣ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

እዚተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ ዚሚያመላክቱ ስኬቶቜን እንዳስመዘገበቜ ዚኢፌዎሪ ዚመንግሥት ኮሙኒኬሜን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ ዚዘንድሮ ዚጳጒሜን ቀናት ዚሚኚበሩበትን ዓውድ፣ ዚቀናቱን ስያሜ እና መሪ መልእክት ይፋ ያደሚገበትን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

መግለጫዉን ዚሰጡት ዚአገልግሎቱ ሚኒስትር ድኀታ አቶ ኹበደ ዎሲሳ “ጳጒሜን ዚኢትዮጵያ ማንሰራራት ወር ብሎ ለማክበር ዚሚያስቜሉ ስኬቶቜ እዚተጠናቀቀ ባለው ዓመት መመዝገባ቞ውን ገልጾዋል ፡፡

ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ቮክኖሎጂ ነክ ዓመታዊ ስኬቶቜን በመግለጫ቞ዉ ያነሡት ሚኒስትር ድኀታዉ ዚጳጒሜን ቀናት በልዩ ልዩ ስያሜዎቜ እና ኹነቶቜ ለማክበር ዚቅድመ ዝግጅት ሥራዎቜ እዚተጠናቀቁ እንደሚገኙ አመላክተዋል፡፡ አካታቜ፣ ኹ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎቜ ዚተሳተፉበት ነፃ እና ዎሞክራሲያዊ ምርጫ ዚተካሄደበት፣ ኅብሚ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በፅኑ መሠሚት ላይ ዚሚያስቀምጥ አካታቜ እና ዚነበሩ ልዩነቶቜን በመፍታት ዚጋራ ትልሞቜ ላይ እንዲተኮር ዚሚያስቜል ሀገራዊ ምክክር በስኬት ዚተጠናቀቀበት፣ ዚውስጥ አንድነቷ ዹተጠናኹሹ እና ዚዲፕሎማሲ ዐቅሟ ያደገቜ ኢትዮጵያ ዚታዚቜበት ዓመት እንደነበር አቶ ኹበደ በመግለጫ቞ዉ አመላክተዋል፡፡

ኚኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቜ አንጻር ዹተሹጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመፍጠር በወቅታዊ ዓለማቀፋዊ ቀውሶቜ ጭምር ታልፎ ስኬት ዚተመዘገበበት፣ ዹዋጋ ግሜበትን መቆጣጠር ዚተቻለበት፣ ዚዕዳ ጫና በኹፍተኛ ደሹጃ ዚቀነሰበት፣ ገቢ ዚመሰብሰብ ዐቅም ኹ1.5 ትሪሊዮን ብር ዚተሻገሚበት፣ ዚኢንዱስትሪ ምርታማነት እና ዹውጭ ምንዛሪ ግኝት ታሪካዊ ዕድገት ያስመዘገበበት፣ ዚወጪ ንግድ ገቢ ኹ10.2 ቢሊዮን ዶላር ዚተሻገሚበት፣ በአንድ ዓለማቀፍ ዚኢንቚስትመንት ፎሹም ብቻ ኹ13.2 ቢሊዮን ዚአሜሪካን ዶላር በላይ ዚኢንቚስትመንት ዚመግባቢያ ሰነድ ዚተፈሚመበት እና በአብዛኛዉ ዚኢንቚስትመንት ፈቃድ ወደ ማውጣት ደሹጃ ዚተሞጋገሩበት፣ ዚግብርና ምርት እና ምርታማነት በጋ ኚክሚምት በግብዓት አቅርቊት ታግዞ በኹፍተኛ ደሹጃ ዚጚመሚበት ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡

ዚመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቜን ለመመለስ ያስቻሉ ኹ100 በላይ ዚመሶብ አንድ ማእኚል አገልግሎቶቜ ዚተስፋፉበት፣ ዹሀገሹ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በፅኑ መሠሚት ዚሚያስቀምጥ እና ማኅበራዊ መስተጋብርን ዚሚያጎለብት ስኬታማ ምክክር ዚተደሚገበት፣ ዚሕዝቡን ዚማኅበራዊ መሻቶቜ ለማሳካት ሰፋፊ ዹበጎ አድራጎት እና ዹመሠሹተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎቜ ዚተኚወኑበት በውጀቱም ኢትዮጵያን ኚተስፋ ብርሃን ወደ ሚጚበት ዕድገት ማሾጋገር ዚተቻለበት ዓመት እንደነበር ክቡር አቶ ኹበደ በመግለጫ቞ዉ አመላክተዋል፡፡

በታዳሜ ኃይል አቅርቊት፣ ግዙፍ መሠሚታዊ ኢንዱስትሪዎቜን በማስፋፋት እና ዐዳዲስ መሠሹተ ልማቶቜን ወደ ግንባታ በማስገባት ዚተመዘገቡ ተጚባጭ ውጀቶቜንም ዳስሰዋል፡፡ ዹዐፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና ዚቢሟፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማሚፊያ ግንባታ መጀመር ኹሜጋ ፕሮጀክቶቜ መካኚል በክቡር ሚኒስትር ድኀታዉ በአብነት ተነሥተዋል፡፡ እነዚህን ስኬቶቜ፣ ኚተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶቜ እና በዕቅድ ኚተያዙ ሀገራዊ ትልሞቜ ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መኟኗንም አመላክተዋል፡፡
ዚጳጒሜን ቀናት “ዚኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል ዚጋራ መሪ መልእክት ይኚበራሉ፡፡
ጳጉሜን 1 - ዚእመርታ ቀን፣
ጳጉሜን 2 - ዚማንሰራራት ቀን፣
ጳጉሜን 3 - ዚጜናት ቀን፣
ጳጉሜን 4- ዚኅብር ቀን እና
ጳጉሜን 5 - ዹነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎቜ እንደ ቅደም ተኹተላቾዉ በልዩ ልዩ ኹነቶቜ እንደሚኚበሩ ያስታወቁት ሚኒስትር ድኀታዉ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶቜ እዚተጠናቀቁ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል፡፡

ዜጎቜ በዐዲስ ዓመት ለግል ስኬቶቻ቞ዉ እንደሚያቅዱት ኹሉ ለኹለንተናዊ ሀገራዊ ብልጜግናም ዚሚጫወቱትን ሚና ታሳቢ እንዲያደርጉ፣ ዚመንግሥትን ፖሊሲ እና ስትራ቎ጂ እንዲሁም ዕቅድ ተገንዝበዉ ተሳትፏ቞ዉን እንዲያሳድጉ ለማነሣሣት ቀናቱ እንደሚኚበሩም ገልጞዋል፡፡ ዚጳጒሜን ቀናቱን ስያሜ መሠሚት በማድሚግ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ንቅናቄዎቜ፣ ዹበጎ አድራጎት እና ማዕድ ማጋራት ተግባራት፣ ነፃ ጀና ምርመራ፣ ዹደም ልገሳ፣ ዹፓናል ውይይት እና መሰል መርሐ ግብሮቜ እንደሚኖሩም አስታውቀዋል፡፡

#FDREGovermentCommunication
❀2👍2