Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹
9.9K subscribers
18.4K photos
269 videos
16 files
507 links
This is the official Telegram page of Ministry of Urban and Infrastructure
Download Telegram
ምክክሩ በስኬት ተጠናቋል- ኮሚሽኑ

ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሳምንታት የምክክር ሂደት በኋላ በዛሬው እለት በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ስላሴ የጉባኤውን መጠናቀቅ አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ በዚህ ታሪካዊ መድረክ 4ሺ ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ በመሰባሰብ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ስምንት ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ሲመካካሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡

ተመካካሪዎቹ በመጨረሻም ለዘመናት ለቆዩ አለመግባባቶች መፍትሄ የሚሆኑ ምክረሃሳቦችን አጠናቅረው ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን አክለዋል፡፡

በሂደቱ ተመካካሪዎች በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በቀላሉ እየተግባቡ፣ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ጊዜ ወስደው ጠንከር ያሉ ውይይቶችን እያደረጉ በመጨረሻም በአብዛኞቹ ጉዳዮች ላይ መግባባት መቻላቸውንም ተናግረዋል፡፡

ኮሚሽኑ ሂደቱን ሲከታተል ሁሉም የምክክር መድረኮች በመደማማጥ፣ በመከባባር እና በመቻቻል ሲከናወኑ እንደነበር ማረጋገጥ እንደቻለም ነው ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት የተናገሩት፡፡

የሀገራዊ ምክክሩ ዓላማ ልዩነት ያላቸው ባለድርሻ አካላት ተወያይተው የጋራ መግባባት በመፍጠር በጋራ ወደፊት መራመድ የሚችሉበትን እድል መፍጠር እንደሆነም አስረድተዋል፡፡

ሀገራዊ ምክክር አሸናፊና ተሸናፊን የመለየት ሂደት አይደለም ያሉት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ይህ ሂደት አንዱ ወገን ተሸንፎ ሌላው ወገን የሚያሸንፍበት ውድድርም አይደለም ብለዋል።

እንደ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገለፃ በዚህ የምክክር ሂደት ኢትዮጵያዊያን እርስ በእርስ ተዋውቀዋል፣ ጠንካራ ግንኙነቶችን ፈጥረዋል፣ የተለያዩ አመለካከቶችን አዳምጠዋል፣ እንዲሁም የሀገራችንን ፈተናዎች በተመለከተ ሃሳቦችን ተለዋውጠዋል፤ በመጨረሻም መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

ይህ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ያሉባትን የሃሳብ ልዩነቶች በምክክር መፍታት መቻሏን ያሳየችበት ታሪካዊ ምእራፍ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ በኮሚሽኑ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
#ENDC
❤5
ለዘርፉ የልማት ስራዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደምቀጥል የዓለም ባንክ አስታወቀ

የዓለም ባንክ የመሠረተ ልማት ዘርፍ ሪጂናል ዳይሬክተር ኤሪክ ማግነስ በዘርፍ የልማት ስራዎች ዙሪያ ከሚኒስቴሩ አመራሮች ጋር መክረዋል

አዲስ አባባ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም (ከመልሚ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ በዘርፉ ፕሮጀክቶች  አሁናዊው ሁኔታ፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና በቀጣይም  በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው  ጉዳዮች ዙሪያ  ነው የተወያዩት፡፡

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ፈንታ ደጀን የዓለም ባንክ  በዘሪፉ የልማት ስራዎች እያበረከተ ያለውን ድጋፍ አድንቀው ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል። አሁን ላይ ከተሞች ከመቸውም ጊዜ በላይ በመንግሥት ከፍተኛ ሪብርብ ምቹ
የመኖሪያ እና የመሥሪያ ማዕከላት ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዓለም ባንክ ድጋፍ እየተሰራ ያሉ ፕሮጀክቶች ዝርዝር አፈጻጸም እና ቀጣይ ባንኩ ድጋፍ ማድረግ በሚገባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዋና አማካሪ አቶ ተስፋዬ ወ/ሚካኤል በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጓል ፡፡  

በዓለም ባንክ የመሰረተ ልማት ዘርፍ ሪጂናል  ዳይሬክተር  ኤሪክ ማግነስ  ባንኩ በኢትዮጵያ  ትልልቅ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መጠነ ሰፊ ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸው ይሄው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በዝርዝር በቀረበው ሰነድ መሰረት ዘሪፉን ለማገዝ ባንኩ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።