Mind Morning/ ማይንድ ሞርኒንግ
6.49K subscribers
1.34K photos
16 videos
9 files
509 links
-ስልጠናዎቹ ህይወት ለዋጭ ናቸው!
-የሬድዮ ፕሮግራሙ ራስን አመልካች ነው!
-ጥናቶቹ ችግር ፈቺ ናቸው!
-ምክክሮቹ አሃ የሚያስብሉ ናቸው!
-ዓላማው ሰዎች የራሳቸውን ታላቅነትና ያላዩትን አቅማቸውን እንዲያዩት ማስቻል ነው!
ቤተሰብ ይሁኑ!
@mindmorning
Download Telegram
Forwarded from Mind Morning
🌧ከዝናቡ ይልቅ ቆርቆሮው ይጮሀል🔊

ዝናቡና ቆርቆሮው ድብድብን እንዲወክሉ ሆነው የቀረቡ ናቸው።ደብዳቢና ተደብዳቢ ልዩነታቸው አንዱ ብትር አሳራፊ ሌላው በትር ተቀባይ ስለሆኑ እንጂ ሁለቱም ተማተዋል ።ተመተዋልም። ቆርቆሮው የሚጮኀው የተደበደበውን ያክልና እርሱም የመቋቋም የቻለውን ያክል ነው።ጩኀት ለምን?🤔 ሰንል የተደበደበውን ያክል፣ አንዳንድ ተማሪዎችም ሌሎች ተማሪዎችን በመደባደብ ይታወቃሉ፡፡ልክ እንድ ወንጭፍ እንዳለው እህል ጠባቂ አይነት፣ ወንጭፍ ወደሗላ የተጎተተውን ያክል ወደፊት ይማታል፡፡ አንድ ተማሪም የተመታውን ያክል ይማታል፡፡ የሚገርመው ነገር ደግሞ አንድ ወላጅ የልጁን ጉዳት ሳያይና ጊዜ እንዳጣ ዘንግቶ ተመትተህ እንዳትመጣ የሚሉት ባህል በጣም ያሳዝነኛል። ይህ ለልጆች የበለጠ ጉዳት እንጂ ጥቅም አይሆንምና ፡፡

ለምን ቢሉ
‼️አንድ ተማሪ ሌሎች ተማሪዎችን የሚደባደበው እሱ የተደበደበውንና ያጠራቀመውን ያክል ስለሆነ ነው።‼️

በሌላ መንገድ ተደባዳቢው ልጅ ባለበት ያኔ በተደበደበ ጊዜ እንደቆመ መማርም እንዳልጀመረ ስላልገባን ነው።በባህሪ ተደባዳቢ ተማሪዎችን ብንገልጽ
😣ተነጫቻጭ -የሰማቸው ስለሌለ
😔 የአእምሮ እድገታቸው የቀጨጨ - መትፋት እንጂ መቀበል ስለሚቸገሩ
🚶 ብቸኛ -ማህበራዊ አብሮነት ስለሌላቸው
በዚህ የተነሳ ልጆቹ ድብርት፣ ስጋት፣ ያጠራቸው ሲሆኑ መማር አይችሉም፡፡ይልቁን የሀገራችን አባባል የሆነውን "የመጣን መቀበል የሄደን መሸኘት" ብንረዳው ከሁሉ ያተርፈናል።
የመጣን መቀበል ማለት መስማትና መማርን እንረዳለን።
የሄደን መሸኘት ከሚለው ደግሞ ሰውን በግድ ያለፍላጎቱ መያዝ ይጎዳዋል እንጂ አይጠቅምም የሚለውን እናገኛለን።

ለማንኛውም ተደባደብ ለተባለው ልጅ መፍትሄው መስማት ፣ጊዜ መስጠት፣መረዳት፣ራሱን እንዲገልጽ እድል ማመቻቸት ያስፈልጋል።

🙏ቸር እንሰንብት 👋
7👍6👏1
🎉ደረሰ ደረሰ🎉

11ኛ ዙር የማይንድ ሞርኒንግ የክረምት ስልጠና ምርቃት

2017 ክረምትን ልጆቻቹን በማይንድ ሞርኒንግ ስልጠና ሲወስዱ ለነበሩ ውድ ወላጆች….. 11ኛ ዙር የክረምት የልጆች ስልጠናችን ማጠናቀቂያ ሰዓት ላይ እንገኛለን ።

ስለሆነም የፊታችን ቅዳሜ ነሀሴ 24 ፤ የ2017 ክረምት ልጆቻችንን የምናስመርቅ ይሆናል🎉

📆 ቅዳሜ ነሀሴ 24
ጠዋት 2:30-6:00
📍ቦሌ ዓለም ሲኒማ

እናመሰግናለን 🙏🏽
5
🎉11ኛ ዙር የማይንድ ሞርኒንግ የ2017 ክረምት ስልጠና ልጆቻችንን እንዲህ በሚያምር እና ደስ በሚል መልኩ አስመርቀናል 🎉

ይህን ክረምት በልዩ መልኩ እንዲጠናቀቅ ላገዛችሁ ሁሉ በተለይም ድንቅ ልጆቻቹን ለሰጣችሁን እናንተም በመገኘት ክረምታችንን ስኬታማ ላደረጋችሁ ወላጆች ሁሉ በጣም እናመሰግናለን።

🙏🏽🙏🏽
14👏8👍2
ለወላጆች
መልካም እድል!!

👉መቼ?
👉እንዴት?
👉ለምን?

👌ስለሚያስፈልግዎት

🌟ምዝገባ ጀምረናል
🌟ጥቂት ቦታ ብቻ ነው ያለን

📞 0912333020
4
ለቤተሰብ እረፍተ የሚሰጥ ምርጥ ስልጠና

        Don't miss your spot!!

📖 ልጆች በበጋው ወቅት ከሚማሯቸው ትምህርቶች እኩል ለህይወታችው ወሳኝ ከሆኑ ትምህርቶች ውስጥ አንዱ የህይወት ክህሎቶችን መማርና ማዳበር ነው፡፡

👉 የቀረን ቦታ ጥቂት ነው
👉 ሐሙስ ጥቅምት 6 ምዝገባ ያበቃል

🚫 ፈጥነው ልጆችዎን ያስመዝግቡ  !


🔐ልጆች በበጋው የቅዳሜ ስልጠናችን ምን ይጠቀማሉ

🔑 የጥናት ዘዴና ፕሮግራም ይኖራቸዋል
🔑 በራስ መተማመናቸው ይጨምራል
🔑 እንደሚችሉ ይሰማቸዋል
🔑 ትኩረት ማድረግን ይማራሉ
🔑 ደጋግመው መሞከር ይችላሉ
🔑 አቅማቸውን መጠቀም ይችላሉ
🔑 ጀምረው መጨረስ ይችላሉ
🔑 ሃላፊነት መውሰድ የሚችሉ ይሆናሉ

🗓 ለ2 ወር የሚቆይ ቅዳሜ ቅዳሜ ጠዋት ከ 2:30-5:30 ሰዓት 
🌟 ዕድሜ ከ8-11
🌟            ከ 12-14
🌟            ከ 15-19
        
ለበለጠ ማብራሪያ እና ለመመዝገብ

☎️ 0912 333020
      0970 414243

@mindmorning
3