Mind Morning/ ማይንድ ሞርኒንግ
6.44K subscribers
1.34K photos
16 videos
9 files
510 links
-ስልጠናዎቹ ህይወት ለዋጭ ናቸው!
-የሬድዮ ፕሮግራሙ ራስን አመልካች ነው!
-ጥናቶቹ ችግር ፈቺ ናቸው!
-ምክክሮቹ አሃ የሚያስብሉ ናቸው!
-ዓላማው ሰዎች የራሳቸውን ታላቅነትና ያላዩትን አቅማቸውን እንዲያዩት ማስቻል ነው!
ቤተሰብ ይሁኑ!
@mindmorning
Download Telegram
ልጆች በራሳቸው ምንም ነገር እንዲያደርጉ አለመፍቀድ
        (ይወድቃሉ፣ ይታመማሉ፣ ሲያድጉ፣ አሁን አይችሉትም፣ የሆነ ነገር ቢሆኑስ… የሚል የተሳሳተ በመውደድ የተተካ አስተሳሰብና ሰበብ)
          ይህም ማለት የምናጎርሰው እኛ፣ የምናለብሰው እኛ፣ ሁሉን ነገራቸውን የምናከናውነው እኛ እንሆንና የልጆቹ ድርሻ መተንፈስ ያህል ብቻ ይሆናል ከዛም ልጆቹ ሲያድጉ እጅ ይኖራቸዋል ግን አቅም የሌለው  እጅ፣  እግር ይኖራቸዋል ግን ርቆ የማይራመድና ቶሎ የሚደክመው እግር፣ በአካል ያድጋሉ ግን ትንንሽ እንቅፋትን ማለፍ የሚከብዳቸው፣ እራሳቸውን ችለው መቆም የማይችሉና ጥገኛ፤ እስኪደረግላቸው ጠባቂ ይሆናሉ በዚህም ምክንያት ብዙ ጊዜ የሚሰሩት ነገር ስለሚያጡ (ነፃ ስለሚሆኑ) በቀላሉ ለሱስ የተጋለጡ ይሆናሉ ፡፡ 

ሁሉን ነገር ልጆች ጥያቄ ሳይጠይቁ ማቅረብ (መልስ መስጠት)
       ይህም እኔ ለልጄ አላንስም፣ የኢኮኖሚም የጊዜም ችግር የለብኝም፣ እኔ እንዳደኩት ልጄን አላሳድግም… በሚል አስተሳሰብና ሰበብ የልጆች የወደፊት ህይወት ላይ ትልቅ እንቅፋት የሆነ የአስተዳደግ ዘይቤ ነው፡፡ ይህም ሲሆን ልጆቹ መምረጥ የማይችሉ፣ መወሰን የማይችሉ፣ መብታቸውን የማያውቁ እና የማይጠይቁ፣ ዝም ብሎ ብቻ እንዲሆንላቸው የሚፈልጉ፣ ጠባቂነት (expectation) ያላቸው, ማግኘትን ብቻ እንጂ የማጣትን ትርጉም የማያውቁ፣ የህይወትን ሙሉ ገፅ የማያውቁ ይሆናሉ፡፡ 

በአጠቃላይ የሚያለሙንንና የሚያጠፉንን  በአስተዳደግ ዘይቤዎቻችንን እንቃኝ
ወላጅነት በልዩነት
ማይንድ ሞርኒንግ
4ተኛው የወላጆች መድረክ ይህን ይመስላል ነበር። ሁላችሁንም እናመሰግናለን!
ወዳጆቻችሁ ይህን ሃሳብ መጋራት እንዲችሉ ይህንን link ሼር አድርጓቸው።
@mindmorning
🚩🚩አሁን ላይ ብዙ ግዜ ብዙ ልጆች ምክር አይሰሙም
ይላሉ ---ወላጆችና አሳዳጊዎች።

🚩🚩 በጣም የማልወደው ነገር ምክር ነው
ይላሉ ---ልጆች ሲጠየቁ።
ምክር ያለመስማቱም፤ ምክር የመጥላቱም ዋናው ምንጭ
👉እኛ ያልሆነውን
👉 እኛ ያልቻልነውን
👉 እኛ ያቃተንን
👉 በተግባር ሆነን ማሣየት የተሳነን
በቃላት፣ በንግግርና በምክር ልጆችን መምራት እናስብና ልጆች ከምክራችን ይልቅ ተግባራችንን ያዩብንና ምክራችን እንዳይሰራ ያደርገዋል።
ከዛም
ብመክረው፣ ብመክራት፣ ባስመክረው ባስመክራት አልሰማ አለ፣ አልሰማ አለች ብለን የኛን ድክመት የሌሎች እናደርገዋለን፨

እንዲህ እንደማለት ነው፦

🤔 ሲያነብ አይደለም በእጁ ላይ ጋዜጣ እንኳ ይዞ ልጆቹ አይተውት የማያውቅ ወላጅ ልጆቹን ስለ ንባብ ጥቅም ቢመክር እንደማለት ነው።
እናንተ ደግሞ ሌላ እይታችሁን ጨምሩበት...

ከንግግራችን ተግባራችን ይቅደም!!