MENU
ሐገርኛ
የባህል ህክምናን የማዘመን ሂደት
— January 27, 2023
   

ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ስብጥር፤ በእምቅ የሀገረሰብ እውቀት ክምችትና ተያያዥ ጠቀሜታ ባላቸው መድኃኒታማ እጽዋት ብዛት በዓለም ከታወቁ አገሮች መካከል በግንባር ቀደምትነት ትጠቀሳለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተለዩት ከ50 ሺ ለመድኃኒትነት የሚውሉ እጽዋቶች መካከልም ስድስት ሺ ያህሉ በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ከዚህ ውስጥም አንድ ሺ የሚሆኑት ለመድኃኒትነት የሚውሉ የእጽዋት ዓይነቶች ሲሆኑ፤ 240ዎቹ አገር በቀል መሆናቸውን ነው የዘርፉ ተመራማሪዎች የሚያስረዱት።
ሀገሪቱ እነዚህን ሀገር በቀል እፅዋቶችን ለመድሃኒትነት ጥቅም ላይ በማዋል ረገድም ረጅም ዘመናትን ማስቆጠሯን ሰነዶች ያመለክታሉ። በተለይም የሀገሪቱ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ኑሯቸውና የጤና አጠባበቃቸው በባህላዊ ሕክምና እና መድኃኒት ዙሪያ የሚያጠነጥን መሆኑ ከዕፅዋቶቹ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ያመለክታል።
ይሁንና በተለይም የዘመናዊ ህክምና መስፋፋት ጋር ተያይዞ እፅዋቶችን ለህክምና የመጠቀሙ ባህል እየተዳከመ ስለመምጣቱ ይነሳል። በዚህ ረገድ በአውሮፓ እንደጀርመን፤ በኢዢያ ደግሞ ቻይና እና ህንድ የመሳሳሉት ሀገራት ያላቸውን የእፅዋት ሀብትም ሆነ ባህላዊ ህክምና ከማሳደግ ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀሙ ካሉ የዓለም ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም በቻይና ዘርፉ ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በመተሳሰሩና ለተጠቃሚዎች ምቹ በመደረጉና ወደ ተለያዩ ዓለም ሃገራት ጭምር በመላክ ለሀገራቸው ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ነው የሚገኘው። ቻይና በባህላዊ ህክምና እጅግ እየተራመደች ያለች ሀገር በመሆንዋም የባህል ህክምና ኢንስቲትዩት፤ በጣም የተደራጀ የባህል ህክምና እና መድሀኒት ፣ ኢንሳይክሎፒዲያ (የባህል መዝገባ ቃላት)፤ በሙያው በየጊዜው የሰለጥኑ እና እውቅና የተሰጣቸው ዶክተሮችና የመታከሚያ ቦታዎችን በማዘጋጀት ከፍተኛ ተጠቃሚ ሆናለች።
ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የበርካታ እፅዋቶች ባለቤት ብትሆንም ከዘርፉ የሚገባትን ጥቅም እያገኘች አይለም። ይልቁንም ከዘመናዊ ህክምና መስፋፋት ጋር ተያይዞ የምዕራብውያኑ እውቀትና ተሞክሮ በማምጣት ያላትን እምቅ ሀብትም ሆነ እውቀት እየጣለች እንደምትገኝ ነው በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የሚናገሩት። ይህ ሁኔታ በእጅጉ ከሚያስቆጫቸው ሰዎች መካከል የሚና ባህል ህክምና ማዕከል ባለቤትና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኡስታዝ ኑሩ ጀማል አንዱ ናቸው። የባህል ህክምናውንም ሆነ በዕፅዋት ላይ ያላቸውን ጥልቅ እውቀት ያገኙት ከአባታቸው መሆኑት የሚናገሩት እኚሁ ሰው ‹‹ያለንን ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት አለማወቃችን ብቻ ሳይሆን ለዘርፉ ትኩረት ባለመስጠታችን የምዕራባውያኑ ሸቀጥ ማራገፊያ መሆናችንን ሳስብ ያንገበግበኛል›› በማለት ይገልፃሉ።
ባለፉት ሁለት አስርተ -ዓመታት ከጎንደር እስከ አዲስ አበባ ድረስ በባህላዊ ህክምና ዘርፍ የሰሩት ኡስታዝ ኑሩ ከባህላዊ ህክምናው ባሻገር ዘመናዊ ሳይንስንም ጭምር በማጥናት ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ የሚገኙ ሰው ናቸው። ግለሰቡ ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ ቡሬ ግብርና ኮሌጅ በመግባት እፅዋት ሳይንስ ያጠኑ ሲሆን ከአባታቸው የተረከቡትን በአረብኛ ቋንቋ የተፃፉ የእፅዋትና ባህላዊ ህክምና መጻህፍትን በማንበብ አቅማቸውን አጎልብተዋል። ከዚህም ባሻገር እነዚህን መጻህፍትን ወደ አማርኛ በመተርጎም በማህራዊ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለህብረተሰቡ ተደራሽ አድርገዋል።
ከልጅነታቸው ጀምሮ ከአባታቸው እግር ስር እየተከተሉ የባህል ህክምና እውቀት እየቀሰሙ ያደጉት ኡስታዝ ኑሩ በተለይም ባህላዊ እውቀቱን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማጣመር በተለያዩ ህመም ውስጥ ያሉ ለአካባቢያቸው ነዋሪዎች አገልግሎት በመስጠት ፤ በባህል ህክምናም ሆነ በሃኪሞቹ ዙሪያ ያለውን የተዛባ አመለካከት በመቀየር፤ በመድሃቶቹ ፈዋሽነት ላይ ያሉ ጥርጣሬዎችን በማጥራት ረገድ ከፍተኛ የሆነ ስራ እያከናወኑ ነው ያሉት።
እንደ ኡስታዝ ኑሩ ማብራሪያ፤ በኢትዮጵያ የባህል ህክምና የጀመረበት ጊዜ በውል ባይታወቅም የሺ ዘመናት ታሪክ እንዳለው በዘርፉ የተፃፉ ጥንታዊ መጻህፍት ያስረዳሉ። ባህላዊ ህክምና የሕረተሰቡን ብቻ ሳይሆን የከብቶችንም ጤና በመጠበቅ ትልቅ ባለውለታ የሆነ ዘርፍ ነው። ከአፄ ኃይለስላሴ ጀምሮ የባህል ህክምና በሕግ እንዲመራ ተሞክሮ ነበር። ይሁንና ዘርፉ ካለው ፋይዳ አንፃር የሚገባውን ትኩረት አልተሰጠውም። በተለይ የደርግ መንግሥት መምጣቱን ተከትሎ የባህል ህክምና የሚሰጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጫና ማሳደርና የመሳሰሉት ችግሮች ነበሩበት።
ከዚሁ በላይ ግን ጊዜው እየሰለጠነ በመጣ ቁጥር አብዛኛው ማህበረሰብ የአባቶችን የቀደመ እውቀት በመተው ወደ ምዕራባውያኑ እውቀትና ህክምና ላይ ማተኮር መጀመሩ የዘርፉ እድገት እንዲያሽቆለቁል ምክንያት እንደሆነ ኡስታዝ ኑሩ ያስረዳሉ። ‹‹በዚህ ትልቅ እሴታችን ዙሪያ አባቶቻችን ሰንደው ያዘጋጇቸው በርካታ መጻህፍት አሉ፤ ነገር ግን እነዚህን መጻህፍት አዋራቸውን አራግፈን እንዳንጠቀም ብዙ መሰናክሎች አሉብን›› ይላሉ።
እንደኡስታዝ ኑሩ ማብራሪያ፤ ጀርመን ከኢትዮጵያም ሆነ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እፅዋቶችን በመውሰድና ባህላዊ እውቀት በመቀመር ከፍተኛ ደረጃ ደርሳለች። ጀርመን በቅርቡ 3ሺ 500 የሚደርሱ ባህላዊ መድሃኒቶችን ገበያ ላይ አውላለች። የዘመናዊ ህክምና ባለቤት የምትባለው አሜሪካም 1 ሺ800 የሚሆኑ የዕፅዋት መድሃኒቶችን ለገበያ አቅርባለች። ኢትዮጵያ ከዚያ በላይ ሀብት ቢኖራትም ያሏትን መጻህፍቶች በህገመጥ መንገድ ወደውጭ በመውጣታቸውና ለዘርፉ በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱ ከዘርፉ ከሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ አድርጓታል።
ቻይናም የራሷ ባህል እና ጥንታዊ እውቀት ለማሳደግ በጣም ብዙ ጥረት ማድረጓን ያነሳሉ። ‹‹ቻይና በባህል ህክምና ዘርፉ ዩኒቨርሲቲ እስከማቋቋም ደርሳለች። በዩኒቨርሲቲው 60 በመቶ ባህላዊ፤ 40 ደግሞ ዘመናዊ ትምህርት ነው የሚሰጠው› ይላሉ። ጀርመንም በተመሳሳይ ለባህላዊ ህክምና ትምህርት ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥ አንስተው፤ ‹‹በጀርመን ማንኛው ዶክተር የስራ ፈቃድ የሚሰጠው በባህል ህክምና ዘርፍ ፈተና ወስዶ ፈተናው ማለፍ ሲችል ብቻ ነው›› ሲሉ ይጠቅሳሉ።
በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የተለያየ የአየር ፀባይ እና እንደየአካባቢው የሚበቅሉ በርካታ መድሃኒትነት ያላቸው እፅዋቶች ቢኖሯትም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ከመጠቀም ወደኋላ ቀርታለች። ‹‹ሱዳን ብትሄጂ ግን እንደሁኔታው የሚመች የአየር ፀባይ የለም። እኛ ደግሞ በተቃራኒው የአየር ፀባይም ሆነ መድሃኒታማ እፅዋቶች ባለሀብቶች ነን። ግን ደግሞ ፈጣሪ አሟልቶ የሰጠንን ሀብት በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም›› ይላሉ።
ለዚህ ደግሞ በዋናነት በኢትዮጵያ የምዕራብውያኑ ተፅዕኖ በመዋጥ የራስን እወቅት፤ ታሪክ ቅርስና ማንነት በመተው የሌሎችን ከፍተኛ ወጪ በማውጣት የመጠቀም ልምዱ በመጎልበቱ እንደሆነ ያስረዳሉ። ‹‹ይህ ደግሞ አሁንም በሌሎች ሀገራት ላይ ጥገኛ እንድሆን ከማድረጉም ባሻገር በእጃችን ያለውን አቅም እያጣነው ነው ያለነው›› ሲሉ ስጋታቸውን ይገልፃሉ። በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ ከመካከለኛ ገቢ ካላቸው ጋርም ተርታ መሰለፍ ያለመቻሏንና ዛሬም በሌሎች ሀገራት ጥገኛ በመሆን ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬም እየተዳረገች መሆኑን ነው ያመለከቱት።
MENU
ሐገርኛ
የባህል ህክምናን የማዘመን ሂደት
— January 27, 2023
   

ኢትዮጵያ በብዝሃ ሕይወት ስብጥር፤ በእምቅ የሀገረሰብ እውቀት ክምችትና ተያያዥ ጠቀሜታ ባላቸው መድኃኒታማ እጽዋት ብዛት በዓለም ከታወቁ አገሮች መካከል በግንባር ቀደምትነት ትጠቀሳለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተለዩት ከ50 ሺ ለመድኃኒትነት የሚውሉ እጽዋቶች መካከልም ስድስት ሺ ያህሉ በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ከዚህ ውስጥም አንድ ሺ የሚሆኑት ለመድኃኒትነት የሚውሉ የእጽዋት ዓይነቶች ሲሆኑ፤ 240ዎቹ አገር በቀል መሆናቸውን ነው የዘርፉ ተመራማሪዎች የሚያስረዱት።
ሀገሪቱ እነዚህን ሀገር በቀል እፅዋቶችን ለመድሃኒትነት ጥቅም ላይ በማዋል ረገድም ረጅም ዘመናትን ማስቆጠሯን ሰነዶች ያመለክታሉ። በተለይም የሀገሪቱ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ኑሯቸውና የጤና አጠባበቃቸው በባህላዊ ሕክምና እና መድኃኒት ዙሪያ የሚያጠነጥን መሆኑ ከዕፅዋቶቹ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት ያመለክታል።
ይሁንና በተለይም የዘመናዊ ህክምና መስፋፋት ጋር ተያይዞ እፅዋቶችን ለህክምና የመጠቀሙ ባህል እየተዳከመ ስለመምጣቱ ይነሳል። በዚህ ረገድ በአውሮፓ እንደጀርመን፤ በኢዢያ ደግሞ ቻይና እና ህንድ የመሳሳሉት ሀገራት ያላቸውን የእፅዋት ሀብትም ሆነ ባህላዊ ህክምና ከማሳደግ ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ደረጃ እየተጠቀሙ ካሉ የዓለም ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም በቻይና ዘርፉ ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በመተሳሰሩና ለተጠቃሚዎች ምቹ በመደረጉና ወደ ተለያዩ ዓለም ሃገራት ጭምር በመላክ ለሀገራቸው ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ነው የሚገኘው። ቻይና በባህላዊ ህክምና እጅግ እየተራመደች ያለች ሀገር በመሆንዋም የባህል ህክምና ኢንስቲትዩት፤ በጣም የተደራጀ የባህል ህክምና እና መድሀኒት ፣ ኢንሳይክሎፒዲያ (የባህል መዝገባ ቃላት)፤ በሙያው በየጊዜው የሰለጥኑ እና እውቅና የተሰጣቸው ዶክተሮችና የመታከሚያ ቦታዎችን በማዘጋጀት ከፍተኛ ተጠቃሚ ሆናለች።
ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የበርካታ እፅዋቶች ባለቤት ብትሆንም ከዘርፉ የሚገባትን ጥቅም እያገኘች አይለም። ይልቁንም ከዘመናዊ ህክምና መስፋፋት ጋር ተያይዞ የምዕራብውያኑ እውቀትና ተሞክሮ በማምጣት ያላትን እምቅ ሀብትም ሆነ እውቀት እየጣለች እንደምትገኝ ነው በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የሚናገሩት። ይህ ሁኔታ በእጅጉ ከሚያስቆጫቸው ሰዎች መካከል የሚና ባህል ህክምና ማዕከል ባለቤትና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኡስታዝ ኑሩ ጀማል አንዱ ናቸው። የባህል ህክምናውንም ሆነ በዕፅዋት ላይ ያላቸውን ጥልቅ እውቀት ያገኙት ከአባታቸው መሆኑት የሚናገሩት እኚሁ ሰው ‹‹ያለንን ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት አለማወቃችን ብቻ ሳይሆን ለዘርፉ ትኩረት ባለመስጠታችን የምዕራባውያኑ ሸቀጥ ማራገፊያ መሆናችንን ሳስብ ያንገበግበኛል›› በማለት ይገልፃሉ።
ባለፉት ሁለት አስርተ -ዓመታት ከጎንደር እስከ አዲስ አበባ ድረስ በባህላዊ ህክምና ዘርፍ የሰሩት ኡስታዝ ኑሩ ከባህላዊ ህክምናው ባሻገር ዘመናዊ ሳይንስንም ጭምር በማጥናት ለዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ የሚገኙ ሰው ናቸው። ግለሰቡ ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ ቡሬ ግብርና ኮሌጅ በመግባት እፅዋት ሳይንስ ያጠኑ ሲሆን ከአባታቸው የተረከቡትን በአረብኛ ቋንቋ የተፃፉ የእፅዋትና ባህላዊ ህክምና መጻህፍትን በማንበብ አቅማቸውን አጎልብተዋል። ከዚህም ባሻገር እነዚህን መጻህፍትን ወደ አማርኛ በመተርጎም በማህራዊ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለህብረተሰቡ ተደራሽ አድርገዋል።
ከልጅነታቸው ጀምሮ ከአባታቸው እግር ስር እየተከተሉ የባህል ህክምና እውቀት እየቀሰሙ ያደጉት ኡስታዝ ኑሩ በተለይም ባህላዊ እውቀቱን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማጣመር በተለያዩ ህመም ውስጥ ያሉ ለአካባቢያቸው ነዋሪዎች አገልግሎት በመስጠት ፤ በባህል ህክምናም ሆነ በሃኪሞቹ ዙሪያ ያለውን የተዛባ አመለካከት በመቀየር፤ በመድሃቶቹ ፈዋሽነት ላይ ያሉ ጥርጣሬዎችን በማጥራት ረገድ ከፍተኛ የሆነ ስራ እያከናወኑ ነው ያሉት።
እንደ ኡስታዝ ኑሩ ማብራሪያ፤ በኢትዮጵያ የባህል ህክምና የጀመረበት ጊዜ በውል ባይታወቅም የሺ ዘመናት ታሪክ እንዳለው በዘርፉ የተፃፉ ጥንታዊ መጻህፍት ያስረዳሉ። ባህላዊ ህክምና የሕረተሰቡን ብቻ ሳይሆን የከብቶችንም ጤና በመጠበቅ ትልቅ ባለውለታ የሆነ ዘርፍ ነው። ከአፄ ኃይለስላሴ ጀምሮ የባህል ህክምና በሕግ እንዲመራ ተሞክሮ ነበር። ይሁንና ዘርፉ ካለው ፋይዳ አንፃር የሚገባውን ትኩረት አልተሰጠውም። በተለይ የደርግ መንግሥት መምጣቱን ተከትሎ የባህል ህክምና የሚሰጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጫና ማሳደርና የመሳሰሉት ችግሮች ነበሩበት።
ከዚሁ በላይ ግን ጊዜው እየሰለጠነ በመጣ ቁጥር አብዛኛው ማህበረሰብ የአባቶችን የቀደመ እውቀት በመተው ወደ ምዕራባውያኑ እውቀትና ህክምና ላይ ማተኮር መጀመሩ የዘርፉ እድገት እንዲያሽቆለቁል ምክንያት እንደሆነ ኡስታዝ ኑሩ ያስረዳሉ። ‹‹በዚህ ትልቅ እሴታችን ዙሪያ አባቶቻችን ሰንደው ያዘጋጇቸው በርካታ መጻህፍት አሉ፤ ነገር ግን እነዚህን መጻህፍት አዋራቸውን አራግፈን እንዳንጠቀም ብዙ መሰናክሎች አሉብን›› ይላሉ።
እንደኡስታዝ ኑሩ ማብራሪያ፤ ጀርመን ከኢትዮጵያም ሆነ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እፅዋቶችን በመውሰድና ባህላዊ እውቀት በመቀመር ከፍተኛ ደረጃ ደርሳለች። ጀርመን በቅርቡ 3ሺ 500 የሚደርሱ ባህላዊ መድሃኒቶችን ገበያ ላይ አውላለች። የዘመናዊ ህክምና ባለቤት የምትባለው አሜሪካም 1 ሺ800 የሚሆኑ የዕፅዋት መድሃኒቶችን ለገበያ አቅርባለች። ኢትዮጵያ ከዚያ በላይ ሀብት ቢኖራትም ያሏትን መጻህፍቶች በህገመጥ መንገድ ወደውጭ በመውጣታቸውና ለዘርፉ በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱ ከዘርፉ ከሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ አድርጓታል።
ቻይናም የራሷ ባህል እና ጥንታዊ እውቀት ለማሳደግ በጣም ብዙ ጥረት ማድረጓን ያነሳሉ። ‹‹ቻይና በባህል ህክምና ዘርፉ ዩኒቨርሲቲ እስከማቋቋም ደርሳለች። በዩኒቨርሲቲው 60 በመቶ ባህላዊ፤ 40 ደግሞ ዘመናዊ ትምህርት ነው የሚሰጠው› ይላሉ። ጀርመንም በተመሳሳይ ለባህላዊ ህክምና ትምህርት ከፍተኛ ትኩረት እንደምትሰጥ አንስተው፤ ‹‹በጀርመን ማንኛው ዶክተር የስራ ፈቃድ የሚሰጠው በባህል ህክምና ዘርፍ ፈተና ወስዶ ፈተናው ማለፍ ሲችል ብቻ ነው›› ሲሉ ይጠቅሳሉ።
በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የተለያየ የአየር ፀባይ እና እንደየአካባቢው የሚበቅሉ በርካታ መድሃኒትነት ያላቸው እፅዋቶች ቢኖሯትም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ከመጠቀም ወደኋላ ቀርታለች። ‹‹ሱዳን ብትሄጂ ግን እንደሁኔታው የሚመች የአየር ፀባይ የለም። እኛ ደግሞ በተቃራኒው የአየር ፀባይም ሆነ መድሃኒታማ እፅዋቶች ባለሀብቶች ነን። ግን ደግሞ ፈጣሪ አሟልቶ የሰጠንን ሀብት በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም›› ይላሉ።
ለዚህ ደግሞ በዋናነት በኢትዮጵያ የምዕራብውያኑ ተፅዕኖ በመዋጥ የራስን እወቅት፤ ታሪክ ቅርስና ማንነት በመተው የሌሎችን ከፍተኛ ወጪ በማውጣት የመጠቀም ልምዱ በመጎልበቱ እንደሆነ ያስረዳሉ። ‹‹ይህ ደግሞ አሁንም በሌሎች ሀገራት ላይ ጥገኛ እንድሆን ከማድረጉም ባሻገር በእጃችን ያለውን አቅም እያጣነው ነው ያለነው›› ሲሉ ስጋታቸውን ይገልፃሉ። በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ ከመካከለኛ ገቢ ካላቸው ጋርም ተርታ መሰለፍ ያለመቻሏንና ዛሬም በሌሎች ሀገራት ጥገኛ በመሆን ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬም እየተዳረገች መሆኑን ነው ያመለከቱት።
በድሬዳዋ እና በዙሪያው ያላችሁ ወዳጆቸ ለመጀመሪያ ጊዜ የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በድሬዳዋ መክፈቴን ሳበስር በጣም ደስ እያለኝ ነው ።
ይሄው በወንድሞቸ ምክር ከብዙ ንግግር በኃላ ቅርንጫፍ በድሬዳዋ ሳቢያን እሸት ሆቴል ፊት ለፊት መክፈቴን እነግራችሁዋለሁ ።
አትታመሙ !!! ከታመሙ ግን ኑ ተፈጥሮን በተፈጥሮ እናክማለን !!!!!!!
ሚና የባህል ህክምና
0920525200
0994777777
0929686868
ይሄው በወንድሞቸ ምክር ከብዙ ንግግር በኃላ ቅርንጫፍ በድሬዳዋ ሳቢያን እሸት ሆቴል ፊት ለፊት መክፈቴን እነግራችሁዋለሁ ።
አትታመሙ !!! ከታመሙ ግን ኑ ተፈጥሮን በተፈጥሮ እናክማለን !!!!!!!
ሚና የባህል ህክምና
0920525200
0994777777
0929686868
Channel name was changed to «Mina Traditional medicine -ሚና ኑሩ»
በመላው ዓለም ለምትገኙ ሙስሊሞች እንኳን ለዒድ አል አድሀ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።አደረሰን
ተቀበለሏሁ ሚና ወሚንኩም ሷሊሀል አዕማል !!!!!
ተቀበለሏሁ ሚና ወሚንኩም ሷሊሀል አዕማል !!!!!
