ETHIO ≈ SCHOOL
2.51K subscribers
5.02K photos
10 videos
225 files
1.97K links
ይህ ለተማሪዎች እና ለትምህርት ፈላጊዎች ተብሎ የተዘጋጀ ፈጣን የሆነ መረጃ የሚያገኙበት ቻናል ነው።
እንዲሁም በተጨማሪ መረጃወችን በመሰብሰብ በሁሉም የ ት/ት ደረጃ ተማሪን የሚመለከት መረጃ በፍጥነት እናደርሳለን።
ለCross ፦
👇👇👇

👍 @yesshsammmits
👍 @gashtiman1990

Join
👇👇👇
@merejamnch
Download Telegram
#ExitExamSelfVerification

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ተብሏል።

የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው።

በመሆኑም ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የብሔራዊ መታወቂያ FAN ቁጥርዎን በመጠቀምና የግል መረጃ በማማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል።

https://verify.ethernet.edu.et/ ከተጫኑ በኋላ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "ሀገር በቀል እውቀት ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት’’ በተሰኘ የመወያያ ርዕስ የፓናል ውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።

መድረኩ በዘርፉ ከፍተኛ ምሁራን አቅራቢነት እና በፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ አወያይነት ይከናወናል።

መድረኩ ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 በአዲስ አበባ ቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5 ኪሎ ካምፓስ አዳራሽ ይካሔዳል።

በአካል መገኘት ለማትችሉ በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ ተብሏል።

🔗 Zoom link:
https://us06web.zoom.us/j/88912129718?pwd=dsMHaxcSlsu3cEXXxfnbAT6zWnaIFh.1

👉 Meeting ID: 889 1212 9718
👉 Passcode: 802890

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
👌ብዙ ሰወች የተቀየሩበትን እና እየተቀየሩበት ያሉት Hilton ድርጅትን
በመቀላቀል እራስን መለወጥ ይቻላል

👏👏👏👏👏👏👏👏👏


በ አምስት አይነት የገቢ ዓይነቶች ማግኘት ይችላሉ፡-
1. የምርት ገቢ
2. የማሻሻያ ጉርሻ
3. የሪፈራል ጉርሻ
4. የቡድን ኮሚሽን
5. የቪአይፒ ወርሃዊ ደሞዝ እና የነጥብ ሽልማቶች


ይህንን ሊንክ  ከተጫኑ በኃላላ


https://www.apphlts.com/#/login/469118
https://www.apphlts.com/#/login/469118


1.በመጀመሪያ ስልክ ቁጥር
ከ9....... ጀምሮ ማስገባት
2. የማይረሳ የግል passward ማስገባት... ይህን ቁጥር ከ እርስወ ውጭ ማንም ማውቅ የለበትም...



.....

ከዛ  #login# የሚለውን መጫን

.....ከዚህ በኃላ ሁሉንም ነገር አስረዳ....


በጣም ቀላል እና አዲስ ነው... ፈጥነው ሥራ ይጀምሩ


ለበለጠ... ግልፅ ካልሆነለውት...በውስጥ መስመር ያውሩኝ...

👌@yesshsammmits
👌@gashtiman1990
#RemedialExamProtocols

የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከነገ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል።

የሪሚዲያል ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦

➫ ተፈታኞች የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡

➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡

➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡

➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል።

➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
#SamaraUniversity
 
ከሠመራ ዩኒቨርሲቲ ተመርቃችሁ ዋናውን ዲግሪ (Original Degree) ያልወሰዳችሁና እንዲሠራላችሁ የምትፈልጉ የቀድሞ የተቋሙ ምሩቃን፣ ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የመጀመሪያ ዙር ህትመት ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
 
በመሆኑም ይህን ሊንክ https://forms.gle/qMwRKY43AQ2RflnX8 በመጠቀም አስፈላጊውን መረጃ እስከ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም በመሙላት እንድትልኩ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
 
በወጭ መጋራት የተማራችሁ አመልካቾች ዋናውን ዲግሪያችሁን ለመውሰድ ክፍያ መፈፀማችሁን ወይም በአገልግሎት መወጣታችሁን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ እና ደረሰኝ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል ተብሏል፡፡
 
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
#RemedialExam

የ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ዛሬ መሠጠት ጀምሯል፡፡

በዛሬው የመጀመሪያ ቀን ፈተና የባዮሎጂ እና ታሪክ ትምህርት አይነት ፈተናዎች በጠዋት እና ከሰዓት ሦስት ፈረቃዎች (2፡00፣ 5፡00 እና 9፡00 ሰዓት) ይሰጣሉ፡፡

ፈተናው ከዛሬ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል።

ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
ለብሔራዊ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች በሙሉ የተላለፈ መረጃ!

እባክዎን ይህንን መረጃ ለሁሉም ተፈታኞች ሼር Share በማድረግ የበኩላችሁን እገዛ አድርጉ።

https://gibi-info.yaisoftwares.com?ref=user4312

ከትምህርት ሚኒስቴር ለተላለፈው ይፋዊ ማሳሰቢያ ተጨማሪ ማብራሪያ ይሆን ዘንድ፤ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ራሳቸውን በሚገባ ማዘጋጀት እንዲችሉ የተሠራው የ "Gibi Info" ድረ-ገጽ (Website) ከ100,000 በላይ ጥያቄዎችን የያዘ ነው። መድረኩ ለእያንዳንዱ የትምህርት ክፍል (Department) ከእውነተኛው የኤግዚት ፈተና ጋር የቅርብ ተዛማጅነት ያላቸውን ጥያቄዎች አካቷል።

የመመዝገቢያ ሊንክ:- https://gibi-info.yaisoftwares.com?ref=user4312

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
#JimmaUniversity
 
ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ ለማክበር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡
 
ዩኒቨርሲቲው የ75 ዓመታት ጉዞውን በሚዘክረርበት ታሪካዊ ኹነት ላይ የተቋሙ የቀድሞ ተማሪዎች፣ ሠራተኞች እና ወዳጆች እንዲገኙ ጥሪ አድርጓል።
 
በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የምትገኙ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን እና ወዳጆች፣ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን ኅብረት መስራች አባል እንዲሆኑ ዩኒቨርሲቲው የአለምናይ መመዝገቢያ ድረ ገጽ አዘጋጅቷል።
 
https://alumni.ju.edu.et/ ላይ በመግባት የአባልነት ቅፁን እንድትሞሉ ተጋብዛችኋል፡፡
 
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
🔔 የመውጫ ፈተና ተፈታኝ ነዎት? መረጃዎችዎን አረጋግጠዋል?

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች በአስቸኳይ መረጃቸውን እንዲያረጋግጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው።

በመሆኑም #ለመጀመሪያ_ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የFAN ቁጥራችሁን በመጠቀምና የግል መረጃ በማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል።

https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ ይግቡ፣ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” የተሰኘ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልፅጎ በሙከራ ደረጃ ሥራ ላይ አውሏል።

Agentic AI Teacher Assistant የተባለው መተግበሪያው፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት የሚሠራ፣ ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የሥራ ጫና የሚቀንስ መሆኑ ተገልጿል፡፡

መተግበሪያው በውስጥ አቅም የበለፀገና በአካባቢያዊ ኮምፒውተር (Local Machine) ላይ በቀላሉ ተጭኖ የሚሠራ መሆኑን በሚኒስቴሩ ‎የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

‎መተግበሪያው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉትን መፅሐፍቶች በሙሉ ዳታሴት አድርጎ በመውሰድ፣ መፃሕፍቱን ሙሉ በሙሉ እንዲመረምርና እንዲገነዘብ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

‎መተግበሪያው ምን ምን ይሠራል?

የትምህርት እቅድ (Lesson Plan) ያዘጋጃል፣
የፈተና ጥያቄዎችና አሳይመንቶችን ያመነጫል፣
ማስተማሪያ ስልቶችን (Pedagogical Strategies) በራሱ ማቀናጀት ይችላል።

መተግበሪያው በማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ላይ ተጭኖ የሚሠራ ሲሆን፤ ‎በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ አጥጋቢ ውጤት ማስገኘቱ ተመላክቷል፡፡

መተግበሪያውን ለመጠቀም ምንም አይነት ወርሃዊ የኢንተርኔት ካርድ፣ የኔትዎርክ ዝርጋታ ወይም የኤአይ አጠቃቀም ክፍያ እንደማይጠይቅ በሚኒስቴሩ ‎የአይሲቲ አማካሪ ሙሉነህ አጥናፉ (ዶ/ር) አስረድተዋል።

ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ መምህራን እና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች በመተግበሪያው አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።

ለበለጠ መረጃ
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
በሀረሪ ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ

የ6ኛ ክፍል ፈተና
➫ ከሰኔ 02 እስከ 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የ8ኛ ክፍል ፈተና
➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

በክልሉ 6,418 የ6ኛ ክፍል እና 4,624 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በተገለፁት ቀናት ፈተናቸውን እንደሚወስዱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አርሰላን አብዲ ተናግረዋል፡፡

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018/2019 ዓ.ም የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ዝውውር አጠናቆ በየደረጃው በሚገኝ የትምህርት መዋቅር ይፋ አድርጓል።

በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ዝውውሩ ለሁለት ዓመት ተቋርጦ መቆቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደምስ እንድሪስ አስታውሰዋል።

ቢሮው አዲስ የዝውውር መመሪያ በማዘጋጀትና በየደረጃው ለሚገኙ አካላት ግንዛቤ በመፍጠር ዝውውሩን ተግባራዊ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡

ከቅድመ አንደኛ እስከ 2ኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ዝውውር የሞሉ ሲሆን፤ ከነዚህ ውስጥ 6,378 መምህራንና የትምህርት አመራሮች የዝውውር ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
በድሬዳዋ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎች ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ

የ6ኛ ክፍል ፈተና
➫ ከሰኔ 02 እስከ 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የ8ኛ ክፍል ፈተና
➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልል ትምህርት ቢሮዎች ትብብር እየተገነቡ የሚገኙ 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እስከ መጪው ነሐሴ መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር

ከአጠቃላይ 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 726 በትምህርት ሚኒስቴር እና 726 በክልል ትምህርት ቢሮዎች አማካኝነት የሚገነቡ ናቸው።

ትምህርት ቤቶቹን በ2019 የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ለማብቃት የግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን በሚኒስቴሩ የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከተማ መስቀላ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

እስካሁን በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልሎች የሚገነቡ ከ400 በላይ ትምህርት ቤቶች የኮንትራት ስምምነት ከተቋራጮች ጋር ተፈርሞ ወደ ሥራ የተገባ መሆኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ፤ 25 ትምህርት ቤቶች የግንባታ ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን አብራርተዋል።

በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሒደታቸው የዘገየባቸው ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች፣ ትምህርት ቤቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በቀሪው ጊዜ አስፈላጊውን ትኩረትና ክትትል እንዲያደርጉ ኃላፊው አሳስበዋል።

ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
     👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]