መንፈሳዊ ህይወት
4.01K subscribers
437 photos
5 videos
8 files
62 links
✟✟✟በስመአብ ወወልድ በመንፈስ ቅድስ አሀድ አምላክ አሜን ✞✞✞
በዚህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ ስርአት የጠበቁ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ይጠቅሙናል ያስተምሩናል የምንላቸውን መንፈሳዊ
ትምህርቶች ብሒሎች ምክሮች እናስተላልፋለን።
ለሌሎች ሼር በማድረግ ቻናሉን ያጋሩ ✟✟✟

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
✍️✍️ ሀሳብ ወይም አስተያየት ;👇👇

https://t.me/Ortodoxe21 በዚ ይላኩልን
Download Telegram
✝️መንፈሳዊ ተጋድሎ✝️

2.መንፈሳዊ ተጋድሎ ዓላማው ምንድነው?

ሀ. የድል አክሊል (የዘለዓለም ሕይወት) ለመቀበል

እግዚአብሔር አምላካችን ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ከአምላካቸው ጋር መኖር ከመረጡ ሊሰጣቸው ያዘጋጀው ከመነገርና ከመታሰብ በላይ የሆነ የዘለዓለም  ሕይወት አለ፡፡ የሰው ልጅ ሕሊናዊ ነፃ ፈቃዱ ደግሞ ከአዳምና ከሔዋን ውድቀት በኋላ በየጊዜው እየደከመና ወደ ኃጢአት እያዘነበለ መጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ዘንድ ከብሮ ባየ ጊዜ ከአባቶቻችን ጀምሮ ዘወትር የሚቀና ክፉ ጠላትም (ዲያብሎስ) አለን፤ ባገኘው አጋጣሚ ስንፍናችንንና ድካማችንን እየተከተለ እነዚህንም በመጠቀም ዘወትር ከአምላካችን ሊለየን እንደሚተጋም ከላይ ተመልክተናል፡፡

ሽልማት፣ አክሊል የሚሰጠው ደግሞ ማሸነፍ ለሚችል ጎበዝ ሰው ነው፡፡ ሰነፍና ቸልተኛ ሰው ግን ሊሸለም አይገባውም አንድ ሰው ጎበዝ ወይም ሰነፍ መሆኑ የሚታወቀው ደግሞ በፊቱ ያጋጠመውን ውድድር ወይም ፈተናና መከራ ማሸነፍና ማለፍ ሲችል ብቻ ነው፡፡

ስለዚህ የመንፈሳዊ ተጋድሎ ዓላማ በገዛ ባሕርያችን ያለን መጥፎ የኃጢአት ዝንባሌና ጠላታችን ዲያብሎስ የሚያመጣብንን ፈተናና ሽንገላ ከእግዚአብሔር ርዳታና ቸርነት ጋር ሕሊናን በማንቃት፣ ራስን በመግዛትና ጠንክሮ በመጋደል አምላካችን ያዘጋጀልንን የድል አክሊል የዘላለም ሕይወትን መቀበል ነው፡፡ ‹‹ የተጠራህለትን የዘለዓለም ሕይወት ትቀበል ዘንድ መልካሙን የሃይማኖት ገድል ተጋደል›› አንዲል (1ኛ ጢሞ 6፥12) ሐዋርያቅ ቅዱስ ጳውሎስ ብዙ መከራዎችን አልፎ ገድሉን በድል አድራጊነት ሲፈጽም ‹‹ መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫዬን ጨርሻለሁ፤ ሃይማኖቴንም ጠብቄያለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤ ይህም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፤ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱ ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም፡፡›› ብሏል ( 2ኛ ጢሞ 4፥7-8)

ከተማራችሁበት ለሌሎች ሼር በማረግ አድርሱ !

ይቀጥላል ....

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
✝️መንፈሳዊ ተጋድሎ✝️

ለ.ለመንፈሳዊ እድገት

ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለፍሬ የሚበቃው የድል አክሊልን መቀዳጀት የምንችለው የማያቋርጥ (የማይቆም) መንፈሳዊ ዕድገት ሲኖረን ነው፡፡ በጥምቀት ያገኘነው አዲሱ ሕይወታችን ዘወትር ማደግ ይኖርበታል፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን በዛፍ ተክል ይመሰላል፡፡ ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ፍሬ እስከሚያፈራለት ጊዜ ድረስ ያለው ድካም ቀላል አይደለም፡፡ የዛፉ ችግኝ እንዲያበቅል፣ እንዲለመልም፣ አንዲያብብና እንዲያፈራ አትክልተኛው ያልተቆጠበ ጥረት ማድረግ ይኖርበታል፤ በየጊዜው ውሃ ማጠጣት፣ ማረምና መኰትኰት፣ ፀረ ዕፅዋትና ፀረ ሕይወት የሆኑ በሽታዎችን መከላከል ያስፈልጋል፡፡ እንደዚሁ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን አድጎ ለፍሬ እስኪበቃ ድረስ ዕለተ ዕለት ጠንክረን በትዕግሥት መሥራት በመንፈሳዊ ተጋድሎ መጽናት ይገባል፡፡ የመንፈሳዊ ተጋድሎም ዓላማው መንፈሳዊ ሕይወታችንን የሚያቀጭጩ  ከጸጋ እግዚአብሔርም የሚያራቁቱ ኃጢአትና የዲያብሎስ ፈተናን በመቃወም መንፈሳዊ ምግቦችንም በመመገብ አዲሱ ሕይወታችንን ማሳደግ ነው፡፡

መንፈሳዊ ተጋድሎ በሚለው ርዕስ የጀመርነው ትምህርት ጨርሰናል ከተማራችሁበት ለሌሎች ሼር በማረግ አድርሱ

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
👍1
ምን ፍሬ አፈራን???

ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፡፡

“ልጆቼ!

👉እስኪ ፍቀዱልኝና ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ትመላለሳላችሁ፡፡ መልካም ነው፡፡

👉 ግን ምን ለውጥ አመጣችሁ? ምን ፍሬ አፈራችሁ? ታገለግላላችሁን? ከአገልግሎታችሁ ምን ረብሕ አገኛችሁ? ጥቅምን ካገኛችሁ በእውነት ምልልሳችሁ የጥበበኛ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡

👉 ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ወንጌላውያን እንዲህ እያስተማሩን ሳለ የማንለወጥ ከሆነ ግን የእስከ አሁን ምልልሳችን የአይሁድ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ 

👉አይሁዳውያን ሕገ ኦሪትን የተሰጠቻቸው ኃጢአታቸውን በእርሷ መስታወትነት አይተው ንስሐ እንዲገቡባት ነበር፡፡

👉እነርሱ ግን የንስሐ ፍሬ ሳያፈሩባት እንዲሁ ይመኩባት ነበር፡፡

👉 ስለሆነም ለሕይወት የተሰጠቻቸው ሕግ ሞት ሆና አገኟት፡፡

👉እኛም እንዲህ ለኵነኔ ያይደለ ለጽድቅ የተሰጠችን ወንጌል ፍሬ የማናፈራበት ከሆነ ከአይሁዳውያን የባሰ ቅጣት ትፈርድብናለች፡፡

👉እስኪ ምሳሌ መስዬ ላስረዳችሁ፡፡

👉አንድ የሚታገል ሰው (wrestler) በየጊዜው ተጋጣሚውን እንደምን ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፡፡

👉 ተጋጣሚውም በቀላሉ ማሸነፍ ይቻሏል፡፡

👉 በየጊዜው ራሱን የሚያሻሽል (Update የሚያደርግ) ሐኪም ጐበዝ አዋቂና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል፡፡

👉በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምን ፍሬ አፈራን? እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን የቆዩትን ምእመናን አይደለም፡፡

👉እየተናገርኩ ያለሁት ከልጅነታችን አንሥተን በቤቱ ለምንመላለስ እንጂ፡፡

👉ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው? አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናት ያነጹልን ለምንድነው? ዝም ብለን እንድንሰባሰብ ነውን? እንደዚህማ በገበያ ቦታም መሰባሰብ አንችላለን፡፡

👉አበው አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹለን ቃሉን እንድንማር፣ በተማርነው ቃልም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራ፣ ሥጋ ወደሙን እንድንቀበል፣ እርስ በእርሳችን እንድንተራረም እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም፡፡

👉ታድያ ምን ፍሬ አፈራን???…”


የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
'"የንጉስ ስልጣን በስጋ ላይ ነው የካህን ስልጣን ግን በነፍስ ላይ ነው '"
@linkortodoxe21
"የጭንቅ ቀን አማላጅ ወላዲተ አምላክ "

""እንደአንቺ ያለ አማላጅ እንደ ልጅሽ ያለ መሀሪ የለም የተራበ ሰው ምግብ ለመብላት እንደሚቸኩል ክርስቶስም ለመማር ይቸኩላል ""

@linkortodoxe21
(ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 28)
----------
16፤ ያዕቆብም ከእንቅልፉ ተነሥቶ። በእውነት እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ ነው፤ እኔ አላወቅሁም ነበር አለ።

17፤ ፈራ፥ እንዲህም አለ። ይህ ስፍራ እንዴት ያስፈራ፤ ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህም የሰማይ ደጅ ነው።

" ዳዊትም። ይህ የእግዚአብሔር ቤት ነው፥አለ "
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 22:1)

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
" ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:15)

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
🔘ሰባቱ አባቶች የምንላቸው

▪️.ልዑል እግዚአብሔር
▪️.የንስሐ አባት
▪️.ወላጅ አባት
▪️.የክርስትና አባት
▪️.የጡት አባት
▪️.የስልጣን አባት
▪️.የቀለም አባት

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
⚪️ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ 7 ጊዜ እኔ ነኝ እኔ እያለ የተናገራቸው

🔶የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ

🔶የዓለም ብርሀን እኔ ነኝ

🔶እኔ የበጎች በር እኔ ነኝ

🔶መልካም እረኛ እኔ ነኝ

🔶ትንሳኤ ህይወት እኔ ነኝ

🔶እኔ መንገዱና እውነት ህይወት እኔ ነኝ

🔶እውነተኛ የህይወት ግንድ እኔ ነኝ

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
🔶አምስቱ ፍኖተ ጻድቅ የተባሉት🔶

✏️ፍቅር
✏️ትህትና
✏️ጾም
✏️ፀሎት
✏️ምጽዋት ናቸው

@linkortodoxe21
🔶አምስቱ ፍኖተ ኃጢአት የተባሉት 🔶
✏️ትዕቢት
✏️ስስት
✏️ምቀኝነት
✏️ስርቆት
✏️ዝሙት ናቸው

@linkortodoxe21