መንፈሳዊ ህይወት
4.01K subscribers
437 photos
5 videos
8 files
62 links
✟✟✟በስመአብ ወወልድ በመንፈስ ቅድስ አሀድ አምላክ አሜን ✞✞✞
በዚህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ ስርአት የጠበቁ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ይጠቅሙናል ያስተምሩናል የምንላቸውን መንፈሳዊ
ትምህርቶች ብሒሎች ምክሮች እናስተላልፋለን።
ለሌሎች ሼር በማድረግ ቻናሉን ያጋሩ ✟✟✟

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
✍️✍️ ሀሳብ ወይም አስተያየት ;👇👇

https://t.me/Ortodoxe21 በዚ ይላኩልን
Download Telegram
የታወረ ትውልድ

ከእናቱ አፈንግጦ እምነት ወዲያ ብሎ በአለም የታለለ
በዚህ በእኔ ዘመን ልበ ስውር ወጣት እጂግ ብዙ አለ
ዶግማና ቀኖና መፈፀም ሲያቅተው በስጋው ሲታለል
ይችን ቅድስት እምነት መፍትሄ ነው ብሎ ትታደስ ይላታል
የመለውጥ ትርጉም ጠንቅቆ ያልገባው ልበ ስውር ጓዴ
በኃጢያት ያደፈ እሱነቱን ይዞ ትታደስ ይለኛል ያላረጀ ነገር ይታደሳል እንዴ?
እነዲዎስቆሮስ ፂም የተነጩላት የፀናች ሀይማኖት
ቆዳቸው እንደ ድንች በአህዛብ ጭካኔ ያኔ የተላጡላት
በሚያስፈራ እሳት ነጎድጓድ በላበት
ለኛ ያቆዩልን ህይወትን ሰውተው
ተዋህዶ እምነቴ ምኗ ነው ያረጀው
በሀጥያት አረንቋ የተቆሳቆለ እርሱ ተቀምጦ
ፍርሀት እንኳን አያውቅ ትታደስ ይለኛል ካፉ ቃል አውጥቶ
መላ በሉት'ማ ምከሩት ይህን ስው
የመታደስ ትርጉም ምን አልባት ቢገባው!!!

https://t.me/linkortodoxe21
https://t.me/linkortodoxe21
https://t.me/linkortodoxe21
​​​​​​††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †††

ኅዳር ፲፪

†††"እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በአል በሰላም አደረሳችሁ"†††

#ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት

➤ ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር።

➤ ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ፺፰ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል።

➤ ከፍጥረት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን ያህል ክብርና ርኅሩኅ የለም። በምልጃውም፣ በረዳትነቱም የታወቀ መልአክ ነው።

➤ መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ ለእግዚአብሔር" ይለዋል። "ወስሙ መስተሣሕልም" ይለዋል። ቂም የሌለው ለምሕረት የሚፋጠን ደግ መልአክ ነውና።

➤ በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ፣ ረዳትና አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል። እስራኤልን ፵ ዘመን በበርሃ መርቷል፤ መግቧልም። ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል።

➣ “ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ፥ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅም ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ።”
— ዘፍጥረት ፵፰፥፲፮

➣ “ማኑሄም የእግዚአብሔርን መልአክ፦ ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው? አለው።”
— መሳፍንት ፲፫፥፲፯

➣ “ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።”
— ዳንኤል ፲፥፳፩

➣ “በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል።”
— ዳንኤል ፲፪፥፩

➣ “በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ። ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፥ አልቻላቸውምም፥”
— ራዕይ. ፲፪፥፯

➤ ደስ የሚለው ደግሞ ርኅሩኁ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው። ከእናቷ ማኅጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ። ደስ ብሎት ይታዘዛታል።

➤ ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ።" ይላታል። ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን፣ በረከትን ያወርዳሉ።

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

✞✞✞"የመላኩ ቅዱስ ሚካኤል ጠብቆነት አይለየን ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያማልደን።"✞✞✞

✞✞✞✞✞ አሜን ✞✞✞✞✞

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

📖ወስብሐት ለ እግዚአብሔ📖

📖✞✞✞✞✞📖


✞✞✞

✞✞✞✞✞✞✞

✞✞✞
Channel name was changed to «✝️መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)✝️»
አንድን አባት ሰዎች መጡና "ዘወትር ጸሎት በማድረግህ በሕይወትህ ላይ የጨመረልኽን ነገር ንገረን?" አሉት::

** እርሱ ግን "ጸሎት በማድረጌ ከጨመርኩት ይልቅ የቀነስኹት ይበዛልና እርሱን ልንገራችኹ፡፡
ጸሎት በማድረጌ ከሕይወቴ ውስጥ ጭንቀት፣ ፍርኃት፣ ተስፋ መቁረጥና ቁጡነትን ቀንሻለኹ" አላቸው፡፡
ጾመ ነቢያት

በመ/ር ቀሲስ ኃይለ ሚካኤል ብርሃኑ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰባት የአዋጅ አጽዋማት አሉ፡፡ ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ደግሞ ጾመ ነቢያት የነቢያት ጾም ነው፡፡ ይህም ነቢያት አምላክ ይወርዳል ይወለዳል ብለው ትንቢት እየተናገሩ ሱባኤ እየቆጠሩ ያንን የተስፋ ቃል በመጠባበቅ የጾሙትን በማሰብ የምንጾመው ጾም ነው፡፡
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የታነጸች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህንን ጾም ስታውጅ ነቢያትን ትንቢት ያናገርክ፣ የተስፋውን ቃል የሰጠህ አምላካችን ሆይ ለአባቶቻችን የሰጠሃቸውን ተስፋ ፈጽመህ አዳንከን፣ ሞታችንን ሞተህ ሕይወትን ሰጠኸን፣የጨለማውን ዘመን አስወግደህ የብርሃን ዘመን ዓመተ ምህረትን በቸርነትህ ሰጠኸን ብለን የእግዚአብሔርን ማዳን እየመሰከርን መጾም እንደሚገባ በማስተማር ነው፡፡
ያንን የጨለማ ዘመን፣ይልቅሶ ዘመን፣የመከራ ዘመን ብሉይ ኪዳንን በመወለድኅ በሐዲስ ኪዳን የተካህልን አስቀድመህ ቅዱሳን አበው፣ሱባኤ እንዲቆጥሩ ነቢያት ትንቢት እንዲናገሩና ሕዝብህን እንዲያጽናኑ አስቀድመህ የላክ አምላካችን ለአባቶቻችን በገባኃው ቃል መሠረት ጊዜውን እና ሰዓቱን ጠብቀህ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ተወለድክልን ሰው ሆነህም በአዲስ ተፈጥሮ አሮጌአችንን አስወግደህ አዲስ ሰው አደረከን በማለት እንጾማለን፡፡
ጸምንም ስንጾም የጾምን ትርጉምና ዓላማ አስቀድመን መማርና ማወቅ ያስፈልጋልና እነሆ…
ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከቱ በአንድ ምዕራፍ ውስጥ አንቀጸ ምጽዋትን፣አንቀጸ ጸሎትን፣አንቀጸ ጾምን አያይዞ በሰፊው አስተምሯል፡፡በዚህም የምንማረው ምጽዋት፣ ጸሎት፣ጾም የማይለያዩ መሆናቸውን ነው፡፡ይህም ማለት እየጾምን መመጽወት እየጾምን መጸለይ ይገባል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱሳን አበው ጾምን የጸሎት እናት፣ የጽድቅ መሠረት፣የበጎነት ምንጭ እያሉ የገለጹአት፡፡ ጌታችንም ጾምን ስንጾም መጸለይና መመጽወት እንደሚገባ ካሳየን በኋላ እንዴት መጾምና ስንጾም እንዴት መሆን እንዳለብን ያስተማረውን ቀጥለን እንመለከታለን፡፡

እንደ ግብዞች አትጠውልጉ ግብዞች ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋእውነት እላችኋለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል እናንተ ግን ስትጦሙ .…ይልና ምን ማድረግ እንደሚገባ ይዘረዝራል፡፡

እሱም፡- 1ኛራሳችሁን ቅቡ(ተቀቡ) ይህም ማለት መንፈስ ቅዱስ ይደርባችሁ ፍቅርን ያዙ፡፡ማለት ሲሆን ፍቅረ እግዚአብሔር እና ፍቅረ ቢጽ ይኑራችሁ ማለት ነው፡፡

2ኛ ፊታችሁን ታጠቡ፡-ማለት ኃጢአታችሁን አስወግዱ፣ንስሓ ግቡ ማለት ነው፡፡

3ኛ በስውር ለሚያይ ለአባታችሁ እንጂ ለሰዎች እንደ ጾማችሁ እንዳትታዩ በስውር የሚያያችሁ አባታችሁም ዋጋችሁን በግልጥ ይሰጣችኋል፡፡ በማለት እውነተኛ ጾም እንዲኖረን አስተምሮናል፡፡

ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ጾም በነገረ ድኅነት ውስጥ ያለውን ጥቅም ሲገልጽ “ጾም ትፌውስ ቊስለ ነፍስ፤ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች” ይላል (ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ)፡፡ የጾምንም ትርጉም ስንመለከት የሚያሳዩን ጥቅሙ ሰውን ለድኅነት ማብቃት እንደሆነ እንረዳለን ይህም ጾም ማለት:- ጾመ ፤ተወ፣ ታረመ፣ ተከለከለ ከሚል የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ጾም ከመባልዕት መከልከል ማለትም ለተወሰነ ሰዓት ከምግብ ተከልክሎ መቆየት እና ከጥሉላት ምግቦች ለአንድ ቀንም ሆነ ለሦስት ቀን፣ለሳምንት፣ ለሁለት ሳምንት ለወርና ለሁለት ወር ወዘተ በመታቀብ ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ከላመ ከጣመ ምግብ መከልከል ማለት ነው፡፡ በዚህም ሁሉ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ማስገዛት ነው፡፡ ጾም ሥጋን አድልበው ለፈቃደ ሥጋ ከሚገፋፋ ስሜት ተላቆ ፍትወተ ሥጋን አጥፍቶ ለፈቃደ ነፍስ ማደር እንዲቻል የመንፈስን ጥንካሬ ገንዘብ ማድረጊያ የጽድቅ መሣሪያ ነው፡፡

የጾም መሠረታዊው ዓላማም ሕዋሳትን ሁሉ ለእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲኖሩ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ያሬድ፡-“ይጹም ዐይን ይጹም ልሳን እዝንኒ ይጹም እምሰሚዓ ኅሡም ዐይን ይጹም አንደበትም ይጹም ጆሮም ክፉ ከመስማት ይጹም ” በማለት የገለጸው(ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ) ፡፡

ስለዚህ ዓይን ክፉ ከማየት ተቆጥቦ የክርስቶስን መስቀል በመመልከት የእግዚአብሔርን ማዳን በመጠባበቅ ደጅ መጥናት መቻል፣ጆሮም ክፉ ከመስማት ርቆ መልካሙን የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ሲችል፣ እጅ ክፉ ከማድረግ ተቆጥቦ ለምጽዋት ሲዘረጋ፣የደከመውን ሲደግፍ የወደቀውን ማንሣት ሲችል
፣እግር ወደ አልባሌ ስፍራ ከመሄድ ይልቅ በቅድስና ስፍራው ተገኝቶ በእግዚአብሔር ፊት መንበርከክ
ሲችል፣ልብም ክፉ ከማሰብ ይልቅ በጎ በጎውን በማሰብ ለእግዚአብሔር የተከፈተ በር ለኃጢአት ግን
የተዘጋ በር ሆኖ ለእግዚአብሔር የሚመች መሆን ማለት ነው፡፡ እነዚህን ሕዋሳት ስም ጠቅሰን ዘረዘርናቸው እንጂ ሰው እንዚህን ከላይ የዘረዘርናቸውን ሁሉ መጠበቅ ሕዋሳቱን መግዛት ስሜቱን መቆጣጠር ሃይማኖታዊም ተፈጽሮአዊም ግዴታው ወይም ኃላፊነቱ ነው ፡፡

ጾም ከእግዚአብሔር ጋር ታስታርቃለች፡፡ “ወታጸምም ኩሉ ፍትወታተ ዘሥጋ፤ የሥጋ ፍልጎትን ሁሉ ታጠፋለች” የሥጋ ፍላጎት ደግሞ ኃጢአት ነው፡፡ እንዲሁም “ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና በወጣትነት ዕድሜ ያሉትን እግዚአብሔርን መፍራት ታስተምራቸዋለች” እንዲል ቅዱስ ያረድ፡፡

ጾም በበደል ምክንያት ከእግዚአብሔር የራቀን ሰው ወደ እግዚአብሔር ታቀርባለች፡፡ ምክንያቱም ጾም እንዲሁ በልማድ ከእህልና ከውኃ ለተወሰነ ጊዜ ተከልክሎ መቆየት ብቻ ሳሆን ልማድነቱ ቀርቶ ፍጹም መጸጸት ያለበት ኃጢአትን በደልን እያሰቡ በጸሎት የእግዚአብሔርን ምህረት በመጠባበቅ በፍቅሩ ተማርኮ የሚጾሙት መሆን ሲቻል በእውነትም ከእግዚአብሔር ጋር መታረቂያ መንገድ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ የሚያስችል የንስሓ ጉዞ ነው፡፡

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የበጎ ምግባር መጀመሪያ ጾም እንደሆነ በመግለጽ በአብዛኛው በዓላቶቿን ከማክበሯ አስቀድማ ጾምን ታውጃለች እነዚህንም ለአብነት ያህል ጠቅሰን እንመለከታለን፡-

የትንሣኤን በዓል(ፋሲካን) ከማክበራችን አስቀድመን ዓቢይ ጾምን፣ ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስን በማሰብ በዓለ ዕረፍታቸውን ከማክበራችን አስቀድሞ ቅዱሳን ሐዋርያትም መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ አገልግሎታቸውን ከመጀመራቸው አስቀድሞ ሱባዔ እንደገቡና እንደ ጾሙ እኛም ጾመ ሐዋርያትን፣ የእመቤታችንን በዓለ ፍልሰት ከማክበራችን አስቀድሞ ቅዱሳን ሐዋርያት ዕረፍቷን ዓይተን ትንሣኤዋን ሳናይ ብለው ሱባኤ እንደ ገቡና እንደ ጾሙ እኛም በዓሏን ከማክበራችን አስቀድመን እንጾማለን፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ከማክበራችን አስቀድመን ቅዱሳን ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው ትንቢት እየተናገሩ ቅዱሳን አበው ሱባዔ እየቆጠሩ ሲጠብቁት እንደ ነበረ የተስፋው ፍጻሜ ሲደርስ በገባው ቃል መሠረት ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የነቢያትም ትንቢት እንደፈጸመ እያሰብን ከበዓለ ልደት አስቀድመን እንጾማለን፡፡ በመሆኑም ጾምን የምግባራት ሁሉ መጀመሪያ ብላ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምታስተምረው ለዚህ ነው፡፡
ጾም የሕግ መጀመሪያም ነው፡፡ ይህንንም ሊቀ ነቢያት ሙሴ የሥነ ፍጥረትን ነገር በአስተማረበት መጽሐፉ እንደ ጠቀሰው እግዚአብሔር አምላክ በኤዶም በስተ ምሥራቅ ገነትን እንደ ተከለ እና የፈጠረውን ሰው በዚያ እንዳኖረው ገልጾ አድርግ እና አታድርግ ወይም ብላ እና አትብላ የምትል የጾም ሕግን እንደሰጠው ይናገራል፡፡

“እግዚአብሔር አምላክም አዳምን እንዲህ ብሎ አዘዘው በገነት ካለው ዛፍ ሁሉ ብላ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያሳየውና ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና”(ዘፍ. ) በዚህም ቃል መሠረት ጾም ትእዛዘ እግዚአብሔር ፣ሕገ እግዚአብሔር፣እንደሆነና በጾም ሕግ ሕይወትና ሞት እንዳለ ተረዳን፡፡ ማለትም ጾምን ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብለን ደስ ብሎን ብንጾም ሕይወትን እንደምናገኝ ሁሉ ጾምን እንደ ግዳጅ ወይም ግዳጅን እንደመወጣት መጾም ስላለብን ብቻ እና ስለ ታዘዝን ብለን ትእዛዝ ለመፈጸማችን ማረጋገጫ አድርገን ለይስሙላ የምንጾም ከሆነ ዋጋ የምናጣበት ነው፡፡ በሌላም መንገድ ጭራሹኑ የጾምን ሕግ በመጣስ ለጾም ያለን አመለካከት ዝቅተኛ ሆኖ ብንገኝ ሞትን እንደምንሞት ከእግዚአብሔር እንደምንለይ ከላይ የተመለከትነው በሙሴ መጽሐፍ የተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል ያስረዳናል፡፡

በመጀመሪያ የጾምን አዋጅ ያወጀው የሁሉ ባለቤት የሆነው አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህም “መልካሙንና ክፉን ከሚያሳየውና ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ” ያለው ነው፡፡ ከዚህ ተነሥተው አበው ቅዱሳን፣ነቢያት ካህናት፣ሐዋርያት ሁሉ ጾምን ሰበኩ፡፡ በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር የተለየውን ሰው በጾም ወደ እግዚአብሔር አቀረቡት፡፡ እግዚአብሔርም በጾም፣በጸሎት፣በምጽዋት፣በስግደት፣በፍጹም ፍቅር እና ትሕትና ሆነው ለተመለሱት ቁጣውን በትዕግሥት መዓቱን በምህረት ይመልሳልና አባታችን አዳም በጾም በጸሎት ወደ እግዚአብሔር በመመለሱ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ገብቶለት ጊዜው ሲደርስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ አዳነው(ነገር ግን ቀጠሮው በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ የኦሪትንም ሕግ ፈጸመ”(ገላ.፬፥፬)እንዲል፡፡

የነነዌ ሕዝቦችም እንዲሁ በነቢዩ ዮናስ ስብከት በጾም በጸሎት በንስሓ ወደ እግዚአብሔር በመመለሳቸው ከተቃጣባቸው መዓት ዳኑ(ዮና.፫፥፩ )፡፡ ሌሎችም በዚህ ክፍል ያልጠቀስናቸው ብዙዎች በጾም በጸሎት የእግዚአብሔር ምህረት ተደርጎላቸዋልና ጾም ሰውና እግዚአብሔር የሚታረቁባት ደገኛ ሕግ ናት፡፡ ለዚህም ነው ነቢዩ ኢዩኤል “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ምህላንም ዐውጁ”(ኢዩ. በማለት ለጾም ልዩ ፍቅር እንዲኖረን እና ስንጾም በደስታ ሆነን የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ሞልቶ ምስጋናውን እያቀረብን መሆን እንዳለበት ያስረዳናል፡፡

ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም “ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ ሥጋዬም ቅቤ በማጣት ከሳ” (መዝ.109፡24)ይላል፡፡ ዳንኤልም “ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም ሦስት ሳምንትም እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም”(ዳን.10፡3) ይላልና ጾምን ጾመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስ እንድናገኝ የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡አሜን
❤️አንዳንድ ሰዎች የተለየ የህይወት ጫወታ ይጫወታሉ፤ ሁሌም በህብረተሰቡ ዉስጥ የሚነገረን ሰዉ ስኬታማ ለመሆን ተምሮ ፡ዲግሪ ይዞ ፡አግብቶ ጥሩ ስራ ይዞ መኖር እንዳለበት ነዉ፡፡ ግን ህይወትን በሌላ ትምህርት፡ በሌላ ዲግሪ፡ በሌላ ስራ ይተዋወቋታል

♦️ የሆነ ነገር ለማግኘት በፈለክ ቁጥር የበለጠ እየራቀህ ይሄዳል፡፡ በህይወቴ ከተረዳሁት ነገር ዉስጥ የፈለኩት ነገር ጥሎኝ ሲሄድ አይቻለሁ፡፡

💙 ሰዎች ህይወታቸዉን ሊያደላደሉ ሲጥሩ አያለሁ፡፡ ቦታ ካስያዙት በኋላ ሁሉም ነገር ወደነሱ እንደሚመጣ ያስባሉ ነገር ግን ይህ በገሃዱ አለም የማይሆን ነገር ነዉ፡፡

🔶 ሰዎች የሚያወሩትን ሳይሆን የሚያደርጉትን አስተዉል፡፡ ሰዎች አቁስለዉኛል ምክንያቱም ተግባራቸዉን አተኩሬ ጊዜ ስላልሰጠሁት ዉስጤን አደሙት!

🔷 ከሚሰጡት በላይ የሚቀበሉ ሰዎችን አትታገሳቸዉ፡፡ ከሚጠቅሙበት ነገር በበለጠ የሚጎዱበት ማንነታቸዉ የጎላ ሰዎችን ከህይወትህ ካላወጣሃቸዉ ውስጥህን እንደ'ብል'ይበሉታል

🔶 ብዙ መሰናክሎች እራስህ የምትፈጥራቸዉ ናቸዉ፡፡ ማህበረሰቡ፣ ጓደኞቼ ወይም ቤተሰቦቼ መሰናክል እንደሆኑብኝ አምን ነበር ግን በመስታወት የማየዉ ማንነቴ እርስ በእርሱ ተሰነካክሏል፡፡

🔶 ህይወት አጭር ናት፡፡ ሞት ደግሞ የማይቀር ጉዳይ ነዉ፡፡ ይህን ማሰብ ላትፈልግ ትችላለህ ግን አንድ ቀን ትሞታለህ፡፡ አንተ ብቻ ሳትሆን የምታየዉ ሰዉ ሁሉ ቀኑን ጠብቆ ይሞታል፡፡ ስለዚህ ሕይወትህን እስከ እንጥፍጣፊዋ ድረስ ኑርባት!
┉┉✽̶»̶̥ĵøïņ✿śĥăŕę»̶̥✽̶┉┉
@ መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)

             
ከቅዱሱ ስፍራ ከቤተክርስቲያን በቅዳሴው፣ በትምህርቱ፣ ሚስጥራቱን ሁላ ተሳትፋችሁም ሆነ የግል ጸሎት አድርጋችሁ እንዲሁ በጎ ነገር ሰርታችሁ ስትጨርሱ ውስጣችሁን የደስታ፣ የእረፍት፣ የተስፋ፣ አንዳች ስሜት በውስጣችሁ ከተሰማችሁ እርሱ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ አስተውሉ ።

#ብጹዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
በቀዳማዊት ሔዋን አለመታዘዝ ምክንያት ሞት በሰው ላይ ሰለጠነ፤ በዳግማዊት ሔዋን (ድንግል ማርያም) መታዘዝ ምክንያት ሕይወት ወደ ዓለም መጣ፡፡ ሞት ኃይሉን አጣ፡፡

ቅዱስ ሄሬንዮስ
“ተወዳጆች ሆይ! ስለ ቅዱሳን ሰማዕታት ብቻ የምትሰሙ አትሁኑ፡፡ እነርሱን ለመምሰልም ተጣጣሩ እንጂ፡፡ ለጊዜው ብቻ የምታደንቋቸው አትሁኑ፡፡ ወደ ቤታችሁ ብቻ ሳይሆን ወደ ልቡናችሁ ውሳጤም ዘልቀው እንዲገቡ አድርጉ፡፡ ዘወትር አስቧቸው፡፡ በልቡናችሁ ጓዳ እንዲገቡ አድርጓቸው፡፡ እናንተን ትተው ይሔዱ ዘንድ አትፍቀዱላቸው፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደሆነ ዘወትር እያያችኋቸው ትበረታላችሁ፡፡ በእምነት ትጸናላችሁ፡፡ የለበሱትን የጽድቅ ጥሩር፣ የያዙትን ምግባረ ወንጌል፣ የእምነት ጋሻ፣ የመዳን ራስ ቁር፣ የመንፈስ ቅዱስንም ሰይፍ እየተመለከታችሁ ትበረታላችሁ፡፡”
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ )
እዘ ላይ ለመንፈሳዊ ሕይወት የሚጠቅም አንድ ቃል ልንገርህ! እግዚአብሔርን የምትወድ ከሆነ ታውቀዋለህ ፡፡ እግዚአብሔርን የምታውቀውም ከሆነ ትወደዋለህ፡፡ ከሁለቱ በአንዱ ጀምር ወደ ሌላው ትደርሳለህ፡፡
አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ
✿የማታ ማታ መስቀሉ የሰው ልጆች ሁሉ መድሃኒት መሆኑን ቢያውቅ ኖሮ ሰይጣን ሳጥናኤል ከመጀመሪያውም ክርስቶስ ኢየሱስ ይሰቀል ዘንድ መስቀሉን አይተክልም ነበር::
አበው ቀደምት
"ስለ እግዚአብሔር ብለህ ለሰዎች ታዘዝ እንጂ ስለ ሰዎች ብለህ ለእግዚአብሔር አትታዘዝ፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
አንድን በክፉ ምግባር የተያዘን ሰው ወደ መልካም ነገር ልትመልሰው ብትወድድ መጀመርያ ሰላሙን እንዲያገኝ አድርገው፡፡ በፍቅር ቃል ከፍ ከፍ አድርገው። እንዲህ ያለን ሰው ከክፉ ስራው እንዲመለስ ለማድረግ ከዚህ የተሻለ ዘዴ የለምና። ሰው በተግባር የሚያደርገው ፍቅር ሰዎችን የመለወጥ ፍጹም ሀይል አለውና።

ቀጥለህ በፍቅር አንድ ሁለት ቃልን ንገረው፣ በቁጣ አትንገረው። በእርሱ ላይ አንዳች የጠላትነት ስሜት አታሳይ። ፍቅር ሰዎችን ለመለወጥ መንገዱን እርሱ ያውቅበታል። ብቻ እንተ እድሉን ስጠው። የፍቅር ሰውም ሁን።

(መክስምያኖስ ባህታዊ ዘሶርያ - የበረሃ ፈርጦች)

አንተ ፡ ደካማ ፡ ሰው ፡ ሆይ ፡ ድንግል ፡ ማርያምን ፡ መውደድ ፡ ከሚገባኝ ፡ መጠን ፡ በላይ ፡ አልፌ ፡ ወድጃት ፡ ይሆን?፡ ብለህ ፡ ስጋት ፡ አይግባህ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ከወደዳት ፡ በላይ ፡ ልትወዳት ፡ አትችልምና።
+...ቅዱስ ፡ ማክስሚልያን...+
ምን አለ ያጎደልክብኝ
ሳትነፍገኝ ሁሉን ሰጠኸኝ
ሁነኸኝ እናት እና አባት
አለፈ ብዙ ዘመናት (2)
አዝ...
አኖርከኝ ዛሬም በጤና
ወጥቸ ገባሁ በደና
መንገዴን ሰጥቸሀለው
ስትመራኝ እከተላለው
አዝ...
ወረት አታውቅም ጌታየ
መች ቀረ ፈሶ እንባየ
ህይወቴ በመድሀፍህ ነው
መፍራቴ ከቶ ለምን ነው
አዝ...
አውቀኸኝ ሳሰራኝ ገና
ሞልተኸኝ ቅኔ ምስጋና
ካንተ ነው የተቀበልኩት
በመዝሙር የሰለጠንሁት
አዝ....
መዛሌ በውሀ ጥም
በባእድ ሀገር መድከም
በብዙ ስጋት ተጉዤ
ቁሜአለው ስምህን ይዤ
አዝ....
በትዳር በልጅ ባርከኸኝ
የልቤን ደስታ ሰጠኸኝ
ስለያዝኩ ጌታ ያንተን እጅ
ተባልኩኝ የንጉሱ ልጅ

-
አትንኩን ስትነኩን ቁጥራችን ይበዛል /2x/
የቅዱስ ጊዮርጊስ የጳውሎስ ልጆች ነን /2x/
አዝ............
ጥቂቶች ሆነን ተነስተን ነው
እንዲሁ ምድርን የሞላ ነው
ብንጣል ከውሀ ከእሳት
ፅኑ ነው የያዝነው እምነት

አትንኩን ስትነኩን ቁጥራችን ይበዛል /2x/
የተክለ ሐይማኖት የጴጥሮስ ልጆች ነን /2x/
አዝ.........
ድሆች ስንባል ባለ ፀጋ
ሁሉን የያዘ ነው ከእኛጋ
ብርቱዉን ጎልያድ የጣለ
በወንጭፋችን ጠጠር አለ

አትንኩን ስትነኩን ቁጥራችን ይበዛል /2x/
የክርስቶስ ሰምራ የአርሴማ ልጆች ነን /2x/
አዝ...........
በሕይወት በቃል ያስተማረን
አምላካችን ነው የነገረን
የዚአለም ጨው ተብለናል
አልጫውንም አጣፍጠናል

አትንኩን ስትነኩን ቁጥራችን ይበዛል /2x/
የቅዱስ መርቆርዮስ የማርቆስ ልጆች ነን /2x/
አዝ.........
እንደ ደመና የከበቡን
የእግዚአብሔርን ቃል የነገሩን
ስላሉን ብዙ ምስክሮች
ደካሞች ሲሉን ነን ሀይለኞች

ቤተክርስቲያን እማማ ዝናሽ በአለም ይሰማ
ቤተክርስቲያን እማማ ዝናሽ በአለም ይሰማ

እስካረጅም እስክሸመግልም ድረስ
ለሚመጣ ትውልድ ሁሉ
ክብርህን ሃይልህን ፅድቅህን እስክነግር ድረስ
አቤቱ አትተወኝ
አትንኩን
ሊቀመዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች #share እናድርግ !
"አንድ ሰውስ እንኳ ድኻ ነኝ ወይም ድኻ አደግ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ፤ ከድኻ ማኅበረሰብ የተገኘሁ ነኝ ብሎ ማንም አይዘን፤ ከአንካሳ ልብና ከሰነፍ ሕሊና በቀር የሚያሳዝን ምንም ምን የለምና። በጎ ምግባርን እንዳንይዝ የሚከለክለን አንዱና ብቸኛው ዕንቅፋት መንፋሳዊ ድካም እና የሕሊና ዓቅመ ቢስነት እንጂ ሌላ ምንም አይደለምና።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ውዳሴ ጳውሎስ መጽሐፍ
ጾመ ነቢያት

ጾመ ነቢያት የተባለበት ምክንያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለ ተፈጸመበት እንዲሁም በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ስለ ጾሙ ስለ ጸለዩ ነው፡፡

ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ። ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡

#የነቢያት_ጾም
ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት
ባይችሉም እግዚአብሔር «የማያደርገውን አይናገር የተናገረውን አያስቀር» ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ፡፡ ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩት እነ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋልም፡፡ ኢሳ 58-1፡፡ በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለ ተፈጸመበት ይህ ጾም «የነቢያት ጾም» ይባላል፡፡

#ጾመ_ስብከት
የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት የምሥራቹ የተነገረበት ስለሆነም «ጾመ ስብከት» ይባላል፡፡ ዘመነ ስብከት ከታኅሣሥ 7 ቀን እስከ ታኅሣሥ 13 ቀን ድረስ ያሉት ዕለታት ናቸው፡፡ ምን ጊዜም ወደ ታኅሣሥ 6 አይወርድም ወደ 14ም አይወጣም፡፡ ስብከት ማለት ዐዋጅ ትምህርት ማለት ነው፡፡ ይህም ከልደተ አብርሃም እስከ ልደተ ዳዊት ያለው ትውልድ የሚታሰብበት ሙሴ በኦሪት፣ ነቢያት በትንቢት፣ ዳዊት በመዝሙሩ በብዙ ምሳሌ ይወርዳል ይወለዳል ሲሉ የተናገሩት የሚታሰብበት ወቅት ነው፡፡ መዝ.143-7 ፤ ኢሳ 64-1፡፡ የሚዘመረው መዝሙር «ወልደ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ ከዓለም በፊት የነበረውንና መድኃኒት የሆነውን ወልድን እንሰብካለን» የሚል ነው ቅዱስ ያሬድ፡፡ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው ትንቢት የተናገሩለትንና ሱባዔ የቆጠሩለትን ሐዋርያት ያላቸውን ትተው ተከተሉት ፈቃዱንም ፈጸሙ፡፡ ስለዚህ ምእመናን ክፉ ሐሳባቸውን አርቀው ርኩሰትን አስወግደው ፍጹም ለእግዚአብሔር እንዲገዙ ትምህርት ይሰጣል፣ ስብከት ይሰበካል፡፡ የሚነበበውም ምንባብ ይህንኑ የሚያመለክት ነው፡፡ ዮሐ.1÷44-49 ፤ ዕብ.1÷1-2፡፡

#ብርሃን
ከስብከት ቀጥሎ ያለችው ሰንበት ስትሆን እንደ ኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት አስተምህሮ ከልደተ ዳዊት እስከ ፍልሰተ ባቢሎን ያለው 14 ትውልድ ይታሰብበታል፡፡ ክቡር ዳዊት «አቤቱ ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ» /መዝ. 42÷3/ እያለ ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ ከርሱ ወገን እንዲወለድ ትንቢት ስለተናገረ ይህ የሚታሰብበት ነው፡፡ ነቢዩ ዓለም በጨለማ ስለሆነች ብርሃንህን ላክ፣ ሐሰትና የሐሰት አባት ነግሦባታልና እውነትህን ላክ አለ፡፡ ወልድን ላክልን ማለቱ ነው፡፡ ይህንም ቅዱስ ዮሐንስ «ብርሃን ዘመጽአ ውስተ ዓለም፤ ብርሃን ወደ ዓለም መጣ» ብሎ ሲመሰክር ጌታም ራሱ «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም» ብሎ ተናግሯቸዋል፡፡ ዮሐ. 8÷12 ፡፡ እንዲሁም ብርሃንን እውነት ማለቱ ኢየሱስ ክርስቶስን ነው፡፡ ላክልን ሲል ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ስደድልን ማለቱ ነው፡፡ ከጨለማ ወደ ብርሃን አውጣን፣ ሥጋህንና ደምህን ስጠን ሲልም ነው፡፡ በዚህ ወቅት የሚዘመሩት መዝሙራት «ብርሃን ዘመጽአ ውስተ ዓለም አቅዲሙ ነገረ በኦሪት ከመ ይመጽእ ወልድ በስብሐት ወይዜንዎ ለጽዮን በቃለ ትፍሥሕት፤ ብርሃን ወደ ዓለም መጣ፣ የምስጋናን ቃል ለጽዮን የሚነግራት ወልድ በክብር፣ በጌትነት እንደሚመጣ አስቀድሞ በኦሪት ነገረ፤ አስታወቀ፡፡» የሚሉ ናቸው፡፡ ንስሐ ከመግባት ቸል እንዳይሉ ይነግራቸዋል፡፡
ነቢያት የጥል ግድግዳን ሰብሮ መለያየትን አጥፍቶ ከጨለማ ወደ ብርሃን የሚያወጣቸውን ሽተው ውረድ ተወለድ አድነንም እያሉ ጮኹ፣ እውነተኛ ብርሃን ጌታችን ጊዜው ሲደርስ ወደ ዓለም ወጣ፡፡ በመምጣቱም በጨለማ ያለው በብርሃን እንዲገለጥ ለሰው ልጆች እግዚአብሔርን የሚያውቁባት ዕውቀት ተሰጠች፡፡

#ኖላዊ
ኖላዊ ተብሎ የሚጠራው ከብርሃን ቀጥሎ ያለው ሳምንት ነው፡፡ የቃሉ ፍች እረኛ ማለት ነው፡፡ እረኞች ለበጎቻቸው
የሚያስፈልጋቸውን ሣር ውኃ ሳያጓድሉ እንዲጠብቁ
እግዚአብሔርም ሕዝቡን በነፍስ በሥጋ የሚጠብቅ ቸር እረኛ ነው፡፡ ይኽንን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሲያብራሩ ከፍልሰተ ባቢሎን እስከ ልደተ ክርስቶስ ድረስ ያለው 14 ትውልድ ነው ይላሉ፡፡ በዚህ ዘመን እሥራኤላውያን ከሀገራቸው ተሰደው በባቢሎን 70 ዘመን ከኖሩ በኋላ ዘሩባቤልን አንግሦላቸው ይዟቸው እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ ከዚያ በፊት እሥራኤል ጠባቂ እንደሌለው መንጋ ተበታትነው ሲኖሩ ነቢያት ከኪሩቤል ላይ የሚገለጥ እረኛቸው እንዲገለጥ የእሥራኤል ጠባቂያቸው ሆይ፣ አድምጥ እያሉ የጠየቁበት መታሰቢያ ነው፡፡ መዝ.79-1-3፡፡ መዝሙሩም «ኖላዊ ዘመጽአ ውስተ ዓለም ወልዱ ወቃለ እግዚአብሔር ዘወረደ እምላዕሉ፤ የእግዚአብሔር ልጅና ቃሉ የሆነ ክርስቶስ ከላይ የወረደ ወደ ዓለም የመጣ እረኛ» የሚል ሲሆን የሚነበበው ደግሞ አንቀጸ አባግዕ የተባለው የዮሐንስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ ዮሐ. 10÷1-22፡፡ እረኛ የሌለው በግ ተኩላ ነጣቂ እንዲበረታበት በበደሉ ከትጉኅ እረኛው የተለየው የሰው ልጅም በሲኦል አጋንንት በርትተውበት ሲጠቀጠቅ ኖሯል፡፡ እንዲሁም ከመንጋውና ከእረኛው የተለየ በግ እንዲቅበዘበዝ አምላኩን ዐውቆ አምልኮቱን ከመግለጽ የወጣው ሕዝብ በየተራራው መስገጃዎችን እየሠራ የሚታደገውን አምላክ በመፈለግ ሲንከራተት ኖሯል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ «እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበር» እንዳለ፡፡ 1ኛ ጴጥ.2÷25፡፡ ነቢያት በዓለም ተበትነው የሚቅበዘበዙትን ሕዝቡን በቤቱ ሰብስቦ የሚጠብቃቸው እውነተኛ ቸር እረኛ እንዲወለድ ስለተናገሩ ያን ለማስታወስ ሳምንቱ ኖላዊ ተባለ፡፡

ነቢያት ይወርዳል፣ ይወለዳል ብለው የተናገሩት ቃል ይፈጸም ዘንድ የሰው ልጆችም ድኅነት ማረጋገጫ እውን ይሆን ዘንድ እንደጾሙ እንደጸለዩ በልደቱም እንስሳት፣ ሰዎች እንዲሁም መላእክት በአንድነት በደስታ እንደዘመሩ የእኛም ደስታ የተረጋገጠበት ነው፡፡ በመሆኑም በፍቅር፣ በጾም በጸሎት ዛሬም እናስበዋለን፡፡ ነቢያት በረከት እንዳገኙ እኛም ከእግዚአብሔር በረከት እናገኛለን ለዚህም አምላካችን ይርዳን አሜን፡፡

ጾሙን ጾመ ሥርየት ፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግል!