(መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ 6)
----------
20፤ ልጄ ሆይ፥ የአባትህን ትእዛዝ ጠብቅ፥ የእናትህንም ሕግ አትተው፤
21፤ ሁልጊዜም በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው።
@linkortodoxe21
----------
20፤ ልጄ ሆይ፥ የአባትህን ትእዛዝ ጠብቅ፥ የእናትህንም ሕግ አትተው፤
21፤ ሁልጊዜም በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው።
@linkortodoxe21
በስመአብ በወልድ በመንፈስ ቅድስ አሀዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ የቻናላችን ተከታዮች ለትንሽ ጊዜ ጠፍተን ነበር ለዛም ይቅርታ እየጠየቅን
በቻናላችን፦
🌷 ብሒለ አበው (የአባቶቻችን ለሕይወታችን መርህ የሚሆኑ ብሒሎች ) እናቀርባለን
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
ውድ የቻናላችን ተከታዮች ለትንሽ ጊዜ ጠፍተን ነበር ለዛም ይቅርታ እየጠየቅን
በቻናላችን፦
🌷 ብሒለ አበው (የአባቶቻችን ለሕይወታችን መርህ የሚሆኑ ብሒሎች ) እናቀርባለን
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
"እግዚአብሔር ፀጋ ከሰጠህ እሱን የምትሸከምበት ትህትናን እንዲሰጥህ ለምነው ካልሆነ የሰጠህን ፀጋ ይወስድልህ ዘንድ ተማፀነው"
🌹 ቅድስ ማር ይስሀቅ በረከታቸው ይደርብን
🌸 @linkortodoxe21
🌹 ቅድስ ማር ይስሀቅ በረከታቸው ይደርብን
🌸 @linkortodoxe21
"ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻለን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻለናል"
🌹ቅድስ አትናቴዎስ በረከታቸው ይደርብን
🌸 @linkortodoxe21
🌹ቅድስ አትናቴዎስ በረከታቸው ይደርብን
🌸 @linkortodoxe21
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅድስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
ቅድሳት ስዕላት በሚል ርዕስ በክፍል በክፍል ትምህርት ልንሰጥ ዝግጅት አርገናል እና ስለ ቅድሳት ስዕላት ምን ያህል ታውቃላቹ በሚል ጥያቄ አዘጋጅተናል ሞክሩ
1.ቅድሳት ስዕላት ለምን አገልግሎት ይውላሉ?
2.ስለ ቅድሳት ስዕላት ከመጽሀፍ ቅድስ ጥቀስ ?
3.ቅድሳት ስዕል መቼ መሳል ተጀመረ ? ማነው የሳለው?
ሞክሩ @Eyasues
@Mentesnhot
መልሱን
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
ቅድሳት ስዕላት በሚል ርዕስ በክፍል በክፍል ትምህርት ልንሰጥ ዝግጅት አርገናል እና ስለ ቅድሳት ስዕላት ምን ያህል ታውቃላቹ በሚል ጥያቄ አዘጋጅተናል ሞክሩ
1.ቅድሳት ስዕላት ለምን አገልግሎት ይውላሉ?
2.ስለ ቅድሳት ስዕላት ከመጽሀፍ ቅድስ ጥቀስ ?
3.ቅድሳት ስዕል መቼ መሳል ተጀመረ ? ማነው የሳለው?
ሞክሩ @Eyasues
@Mentesnhot
መልሱን
<<አንተም÷ የሰው ልጅ ሆይ÷ ጡቡን ወስደህ በፊት አኑራት፤ የኢየሩሳሌምንም ከተማ ሥዕል ሳልባት፤ ክበባት›› (ሕዝ.፬፥፩)
ቅድሳት ሥዕላት ክፍል ፩
ቅዱሳት ሥዕላት አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈጸምባቸው ንዋያተ ቅድሳት ናቸው፡፡ እስራኤላውያን ቀደም ሲል ሰዎች ድንጋይን በማዘጋጀት፣ እንጨትን በመጥረብ፣ ቆዳን በመፋቅ፣ ኅብር ባላቸው ቀለማት በመሳል ለትውልድ እንዲተላለፉ ያደርጉ ነበር፡፡ የቅዱሳት ሥዕላት አጀማመር ዘመነ ኦሪትን መነሻ ያደረገ ነው፤ አስቀድሞ ልዑል እግዚአብሔር ለነቢዩ ሙሴ በታቦተ ሕጉ ላይ ሥዕለ ኪሩብን እንዲሥል አዘዘው፡፡ ‹‹ከስርየት መክደኛውም ጋር አንዱን ኪሩብ በአንድ ወገን÷ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ወገን አድርገህ በአንድ ላይ ትሰራዋለህ፡፡ ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ወደ ላይ ይዘረጋሉ፤ የስርየት መክደኛውንም በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፤ ፊታቸውም እርስ በርሱ ይተያያል፤ የኪሩቤልም ፊቶቻቸው ወደ ስርየት መክደኛው ይመለከታሉ››፡፡ (ዘጸ. ፳፭፥፲፱-፳)
ይቀጥላል ...
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቅድሳት ሥዕላት ክፍል ፩
ቅዱሳት ሥዕላት አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈጸምባቸው ንዋያተ ቅድሳት ናቸው፡፡ እስራኤላውያን ቀደም ሲል ሰዎች ድንጋይን በማዘጋጀት፣ እንጨትን በመጥረብ፣ ቆዳን በመፋቅ፣ ኅብር ባላቸው ቀለማት በመሳል ለትውልድ እንዲተላለፉ ያደርጉ ነበር፡፡ የቅዱሳት ሥዕላት አጀማመር ዘመነ ኦሪትን መነሻ ያደረገ ነው፤ አስቀድሞ ልዑል እግዚአብሔር ለነቢዩ ሙሴ በታቦተ ሕጉ ላይ ሥዕለ ኪሩብን እንዲሥል አዘዘው፡፡ ‹‹ከስርየት መክደኛውም ጋር አንዱን ኪሩብ በአንድ ወገን÷ ሁለተኛውንም ኪሩብ በሌላው ወገን አድርገህ በአንድ ላይ ትሰራዋለህ፡፡ ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ወደ ላይ ይዘረጋሉ፤ የስርየት መክደኛውንም በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፤ ፊታቸውም እርስ በርሱ ይተያያል፤ የኪሩቤልም ፊቶቻቸው ወደ ስርየት መክደኛው ይመለከታሉ››፡፡ (ዘጸ. ፳፭፥፲፱-፳)
ይቀጥላል ...
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቅድሳት ሥዕላት ከፍል ፪
ስለ ቅዱሳትሥዕላት አጀማመር በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡፡ ‹‹በቅድስተ ቅዱሳኑም ውስጥ ቁመታቸው አሥር ክንድ የሆነ ከወይራ እንጨት ሁለት ኪሩቤልን ሠራ፡፡ የኪሩብም አንደኛው ክንፍ አምስት ክንድ÷ የኪሩብም ሁለተኛው ክንፍ አምስት ክንድ ነበረ፤ ከአንደኛው ክንፍ ጫፍ ጀምሮ እስከ ሁለተኛው ክንፍ ጫፍ ድረስ አሥር ክንድ ነበረ፡፡ ሁለቱም ኪሩቤል አንድ ልክና አንድ መልክ ነበረ፡፡ የአንዱ ኪሩብ ቁመት አሥር ክንድ ነበረ÷ የሁለተኛውም ኪሩብ እንዲሁ ነበረ፡፡ ኪሩቤልንም በውስጠኛው ቤት አኖራቸው፤ የኪሩቤልም ክንፎቻቸው ተዘርግተው ነበር፡፡ የአንዱም ኪሩብ ክንፍ አንደኛውን ግንብ ይነካ ነበር÷ የሁለተኛውም ኪሩብ ክንፍ ሁለተኛውን ግንብ ይነካ ነበር፤ የሁለቱም ክንፎች በቤቱ መካከል እርስ በርሳቸው ይነካኩ ነበር፡፡ ኪሩቤልንም በወርቅ ለበጣቸው፡፡ በቤቱም ግንብ ሁሉ ዙሪያ በውስጥና በውጭ የኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ የፈነዳም አበባ ምስል ቀረጸ››፡፡(፩ኛ ነገሥት ፮፥፳፫-፳፱) በትንቢተ ሕዝቅኤልም ‹‹አንተም÷ የሰው ልጅ ሆይ÷ ጡቡን ወስደህ በፊት አኑራት፤ የኢየሩሳሌምንም ከተማ ሥዕል ሣልባት፤ ክበባት›› ይላል ሕዝ.፬፥፩)፡፡
ይቀጥላል ......
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ስለ ቅዱሳትሥዕላት አጀማመር በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡፡ ‹‹በቅድስተ ቅዱሳኑም ውስጥ ቁመታቸው አሥር ክንድ የሆነ ከወይራ እንጨት ሁለት ኪሩቤልን ሠራ፡፡ የኪሩብም አንደኛው ክንፍ አምስት ክንድ÷ የኪሩብም ሁለተኛው ክንፍ አምስት ክንድ ነበረ፤ ከአንደኛው ክንፍ ጫፍ ጀምሮ እስከ ሁለተኛው ክንፍ ጫፍ ድረስ አሥር ክንድ ነበረ፡፡ ሁለቱም ኪሩቤል አንድ ልክና አንድ መልክ ነበረ፡፡ የአንዱ ኪሩብ ቁመት አሥር ክንድ ነበረ÷ የሁለተኛውም ኪሩብ እንዲሁ ነበረ፡፡ ኪሩቤልንም በውስጠኛው ቤት አኖራቸው፤ የኪሩቤልም ክንፎቻቸው ተዘርግተው ነበር፡፡ የአንዱም ኪሩብ ክንፍ አንደኛውን ግንብ ይነካ ነበር÷ የሁለተኛውም ኪሩብ ክንፍ ሁለተኛውን ግንብ ይነካ ነበር፤ የሁለቱም ክንፎች በቤቱ መካከል እርስ በርሳቸው ይነካኩ ነበር፡፡ ኪሩቤልንም በወርቅ ለበጣቸው፡፡ በቤቱም ግንብ ሁሉ ዙሪያ በውስጥና በውጭ የኪሩቤልና የዘንባባ ዛፍ የፈነዳም አበባ ምስል ቀረጸ››፡፡(፩ኛ ነገሥት ፮፥፳፫-፳፱) በትንቢተ ሕዝቅኤልም ‹‹አንተም÷ የሰው ልጅ ሆይ÷ ጡቡን ወስደህ በፊት አኑራት፤ የኢየሩሳሌምንም ከተማ ሥዕል ሣልባት፤ ክበባት›› ይላል ሕዝ.፬፥፩)፡፡
ይቀጥላል ......
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቅድሳት ሥዕላት ክፍል ፫
በጥንት ዘመን ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ በዋሻ ውስጥ በሥዕል እያስደገፉ ያስተምሩ ነበር፡፡ ከዚህም ባሻገር ለእምነታቸው ሲሉ ለተጋደሉ እና መሥዕዋትነትን ለከፈሉ ቅዱሳን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ሥዕል በመሣል ታሪካቸውን አስቀምጠዋል፡፡ ክርስቲያኖች ይህንን እያደረጉ ለዘመናት ከቆዩ በኋላ በስምንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሮማውያን ክርስቲያኖች እና በቢዛንታይን ክርስቲያኖች ዘንድ አለመግባባት ተፈጠረ፡፡ በዚህም ዘመን ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላትን ምክንያት በማድረግ በሁለት ጽንፍ ተከፈሉ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ኢኮኖላትሪያ ሲባሉ እነዚህም ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላትን ከመጠን በላይ አብዝተው ከመውደዳቸው የተነሳ እንደ አማልክት የሚቆጥሩ ናቸው፡፡ ሁለተኛዎቹ ደግሞ ኢኮኖማኺያ ሲባሉ እነዚህም ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላት ከነጭራሹ አያስፈልጉም በማለት ከአምልኮት ሥፍራ መወገድ አለባቸው የሚል አመለካከት የያዙ ነበሩ፡፡ ይህም አለመግባባት ለረጅም ዘመናት ከቀጠለ በኋላ በ፯፻፹፯ እ.ኤ.አ ሁለተኛው የኒቅያ ጉባኤ ተደርጎ ለቅዱሳት ሥዕላት አክብሮት እና ስግደት እንደሚገባ ተወሰነ፡፡ በዚህም ጉባኤ መሠረት ቅዱሳት ሥዕላት በቤተክርስቲያን ውስጥ የእግዚአብሔር ክብሩ መገለጫ ሁነው የሚያገለግሉ የቅድስት ሥላሴ፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የቅዱሳን መላእክት፤ የነቢያትና ሐዋርያት የጻድቃንና ሰማዕታት ሥዕላት ናቸው፡፡ (ዐምደ ሃይማኖት ምዕራፍ ፲፫)
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምንገለገልባቸው ቅዱሳት ሥዕላት የተሣሉት ባለቤቱ እግዚአብሔር በመረጣቸው ሰዎች አማካኝነት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም ለመጀመሪያ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለቱን ሥዕል ለንጉሥ ጢባርዮስ የሣለው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነበር፡፡ ቅዱሳት ሥዕላት ቀኖና ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረገ የአሣሣል እና የአጠቃቀም ሥርዓት አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሚሰቀሉ ምእመናን በሥዕሉ ፊት በመቆም የሚጸልዩበትና ልመናቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
በጥንት ዘመን ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ በዋሻ ውስጥ በሥዕል እያስደገፉ ያስተምሩ ነበር፡፡ ከዚህም ባሻገር ለእምነታቸው ሲሉ ለተጋደሉ እና መሥዕዋትነትን ለከፈሉ ቅዱሳን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ሥዕል በመሣል ታሪካቸውን አስቀምጠዋል፡፡ ክርስቲያኖች ይህንን እያደረጉ ለዘመናት ከቆዩ በኋላ በስምንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሮማውያን ክርስቲያኖች እና በቢዛንታይን ክርስቲያኖች ዘንድ አለመግባባት ተፈጠረ፡፡ በዚህም ዘመን ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላትን ምክንያት በማድረግ በሁለት ጽንፍ ተከፈሉ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ኢኮኖላትሪያ ሲባሉ እነዚህም ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላትን ከመጠን በላይ አብዝተው ከመውደዳቸው የተነሳ እንደ አማልክት የሚቆጥሩ ናቸው፡፡ ሁለተኛዎቹ ደግሞ ኢኮኖማኺያ ሲባሉ እነዚህም ክርስቲያኖች ቅዱሳት ሥዕላት ከነጭራሹ አያስፈልጉም በማለት ከአምልኮት ሥፍራ መወገድ አለባቸው የሚል አመለካከት የያዙ ነበሩ፡፡ ይህም አለመግባባት ለረጅም ዘመናት ከቀጠለ በኋላ በ፯፻፹፯ እ.ኤ.አ ሁለተኛው የኒቅያ ጉባኤ ተደርጎ ለቅዱሳት ሥዕላት አክብሮት እና ስግደት እንደሚገባ ተወሰነ፡፡ በዚህም ጉባኤ መሠረት ቅዱሳት ሥዕላት በቤተክርስቲያን ውስጥ የእግዚአብሔር ክብሩ መገለጫ ሁነው የሚያገለግሉ የቅድስት ሥላሴ፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የቅዱሳን መላእክት፤ የነቢያትና ሐዋርያት የጻድቃንና ሰማዕታት ሥዕላት ናቸው፡፡ (ዐምደ ሃይማኖት ምዕራፍ ፲፫)
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምንገለገልባቸው ቅዱሳት ሥዕላት የተሣሉት ባለቤቱ እግዚአብሔር በመረጣቸው ሰዎች አማካኝነት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም ለመጀመሪያ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለቱን ሥዕል ለንጉሥ ጢባርዮስ የሣለው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነበር፡፡ ቅዱሳት ሥዕላት ቀኖና ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረገ የአሣሣል እና የአጠቃቀም ሥርዓት አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሚሰቀሉ ምእመናን በሥዕሉ ፊት በመቆም የሚጸልዩበትና ልመናቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21