<<ጾምና ጸሎት>>
ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር፤ እግዚአብሔርን ማመስገን፣ መለመን፣ መጠየቅ መማጸን ማለት ነው። እንዲሁም ሰው አሳቡን ለእግዚአብሔር የሚገልጥበት፣ እግዚአብሔር የሰውን ልመና ተቀብሎ ፍቃዱን የሚፈፅምበት ረቂቅ ምስጢር ነው። ጾምና ጸሎት ሁለቱ የማይለያዩ የእግዚአብሔር የበረከት ስጦታዎች ናቸው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ በምድር በነበረበት ጊዜ ከፈፀማቸው አበይት ተግባራት መካከል ጾምና ጸሎት ይገኙበታል። እርሱ የዲያብሎስን ፈተና በጾምና በጸሎት ድል እንደምንነሳው በገዳመ ቆሮንቶስ ለ40 ቀንና ለ40 ሌሊት ጾሞና ጸልዮ አሳይቶናል። ማቴ 4፥1 ስለጾም ኢትዮጵያዊ ቅዱስ ያሬድ “ንጹም ጾም ወናፈቅር ቢጸነ፣ ወንትፋቀር በበይናቲነ፣ ዓይን ይጹም እምርእየ ሕሱም፣ ዕዝን ይጹም እምሰሚዓ ሕሱም፣ ልሳንኒ ይጹም እምተናግሮ ሕሱም ትርጉም ጾምን እንጹም፣ ባልንጀራችንን እንውደድ እርስ በርሳችን እንዋደድ፣ ዓይን ክፉ ከማየት ጀሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበትም ክፉ ከመናገር ይጹም” በማለት እንዴት መጾም እንዳለብን በሚገባ ገልጾልናል።
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ” /ማቴ 26፥41/ ፈተና እንዳይገጥማችሁ ተግታችሁ ፀልዩ ብሎ እንዳስተማራቸው እኛም ወደ ፈተና እንዳንገባ በጸሎት መትጋት ያስፈልጋል። ጾምና ጸሎት ወደ ፈተና እንዳንገባ የምንጠበቅበትና ከፈተናም የምንወጣበት ታላቅ መሳሪያ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል። “ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጾም በቀር አይወጣም” /ማቴ 17፥21/ ”ሰይጣንን ልታስወጡ የምትችሉት፣ በፈተና ውስጥ ብትሆኑ ከገባችሁበት ፈተናና ችግር ልትወጡ፣ ልትፈወሱ የምትችሉት በጸሎትና በጾም ብቻ ነው”ሲል ጌታችን በሐዋርያት አማካኝነት ገልጾልናል። እኛም ካልጾምን ካልጸለይን ወደ ፈተና እንገባለን ከገባንም አንወጣም። ጾምና ጸሎት ከፈተና የምንወጣበትና የምንጠበቅበት ብቻም ሳይሆን የሚያስፈልገንን ሥጋዊ ነገርም እንድናገኝ አማላካችን በቸርነቱ እንዲጎበኘን ይረዳናል። “ለምኑ ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል” /ማቴ7፥7/ እያለ ቅዱስ ወንጌል የምንፈልገውን ነገር እግዚአብሔር አምላክን በጾምና በጸሎት ከለመንነው በሚስፈልገን ስዓትና ጊዜ እንደሚሰጠን ያስረዳናል። ስለዚህ እኛ ወደፈተና እንዳንገባ፣ ከገባንም ከፈተና እንድንወጣና የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ እንድናገኝ የስደትን ኑሮ፣ ባህልና የአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት ሳናደርግ እንደ አባቶቻችን እግዚአብሔርን በጸሎትና በጾም መለመን መማጸን አስፈላጊ ነው።
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር፤ እግዚአብሔርን ማመስገን፣ መለመን፣ መጠየቅ መማጸን ማለት ነው። እንዲሁም ሰው አሳቡን ለእግዚአብሔር የሚገልጥበት፣ እግዚአብሔር የሰውን ልመና ተቀብሎ ፍቃዱን የሚፈፅምበት ረቂቅ ምስጢር ነው። ጾምና ጸሎት ሁለቱ የማይለያዩ የእግዚአብሔር የበረከት ስጦታዎች ናቸው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ በምድር በነበረበት ጊዜ ከፈፀማቸው አበይት ተግባራት መካከል ጾምና ጸሎት ይገኙበታል። እርሱ የዲያብሎስን ፈተና በጾምና በጸሎት ድል እንደምንነሳው በገዳመ ቆሮንቶስ ለ40 ቀንና ለ40 ሌሊት ጾሞና ጸልዮ አሳይቶናል። ማቴ 4፥1 ስለጾም ኢትዮጵያዊ ቅዱስ ያሬድ “ንጹም ጾም ወናፈቅር ቢጸነ፣ ወንትፋቀር በበይናቲነ፣ ዓይን ይጹም እምርእየ ሕሱም፣ ዕዝን ይጹም እምሰሚዓ ሕሱም፣ ልሳንኒ ይጹም እምተናግሮ ሕሱም ትርጉም ጾምን እንጹም፣ ባልንጀራችንን እንውደድ እርስ በርሳችን እንዋደድ፣ ዓይን ክፉ ከማየት ጀሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበትም ክፉ ከመናገር ይጹም” በማለት እንዴት መጾም እንዳለብን በሚገባ ገልጾልናል።
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ” /ማቴ 26፥41/ ፈተና እንዳይገጥማችሁ ተግታችሁ ፀልዩ ብሎ እንዳስተማራቸው እኛም ወደ ፈተና እንዳንገባ በጸሎት መትጋት ያስፈልጋል። ጾምና ጸሎት ወደ ፈተና እንዳንገባ የምንጠበቅበትና ከፈተናም የምንወጣበት ታላቅ መሳሪያ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል። “ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጾም በቀር አይወጣም” /ማቴ 17፥21/ ”ሰይጣንን ልታስወጡ የምትችሉት፣ በፈተና ውስጥ ብትሆኑ ከገባችሁበት ፈተናና ችግር ልትወጡ፣ ልትፈወሱ የምትችሉት በጸሎትና በጾም ብቻ ነው”ሲል ጌታችን በሐዋርያት አማካኝነት ገልጾልናል። እኛም ካልጾምን ካልጸለይን ወደ ፈተና እንገባለን ከገባንም አንወጣም። ጾምና ጸሎት ከፈተና የምንወጣበትና የምንጠበቅበት ብቻም ሳይሆን የሚያስፈልገንን ሥጋዊ ነገርም እንድናገኝ አማላካችን በቸርነቱ እንዲጎበኘን ይረዳናል። “ለምኑ ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል” /ማቴ7፥7/ እያለ ቅዱስ ወንጌል የምንፈልገውን ነገር እግዚአብሔር አምላክን በጾምና በጸሎት ከለመንነው በሚስፈልገን ስዓትና ጊዜ እንደሚሰጠን ያስረዳናል። ስለዚህ እኛ ወደፈተና እንዳንገባ፣ ከገባንም ከፈተና እንድንወጣና የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ እንድናገኝ የስደትን ኑሮ፣ ባህልና የአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት ሳናደርግ እንደ አባቶቻችን እግዚአብሔርን በጸሎትና በጾም መለመን መማጸን አስፈላጊ ነው።
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ትዕግሥት
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ትዕግሥት ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ነው። /ገላ 5፥22-23/ የመንፈስ ፍሬ ብሎ የዘረዘራቸው ምግባረ ሰናያት እርስ በእርሳቸው ግንኙነት አላቸው። ዕምነት ያለው ሰው የውሃት፣ ቸርነት፣ በጎነት ሊኖረው ይገባል፤ ፍቅር ያለው ሰው ደስታ፣ ሰላም ከእነዚህም ጋር ትዕግሥትም አለው። ፍቅርና ዕምነት ያለው ሰው እራሱን መግዛት ይችላል። ፍቅር ይታገሳል እንዲል /1ቆሮ 13፥4/። ትዕግሥት ቻይ፣ ልበ ሰፊ፣ ትሁትና መሀሪ የሆነ ሰው ጠባይ መለያ ነው። ትዕግሥት ዘርፈ ብዙ ነው። በአገልግሎት፣ በጸሎት፣ በማህበራዊ ትዕግሥት አስፈላጊ ነው። ትዕግሥት የሌለው ሰው በቀላሉ ይጨነቃል፣ ይረበሻል፣ ይበሳጫል ምክንያቱም ለምን አሁን የምፈልገው ነገር አልሆነም ብሎ ስለማይረጋጋና ስለሚቸኩል ነው። በተለይ በስደት ዓለም ስንኖር የምናያቸው፣ የምንሰማቸው እና የምናገኛቸው ነገሮች በአብዛኛው ትዕግሥትን የሚፈታተኑ ስለሆኑ ትዕግሥት ከመቸውም በበለጠ ያስፈልጋል።
ጠቢቡ ሰሎሞን “ለሁሉም ጊዜ አለው” /መክ 3፥1/ እንዳለ ጸሎታችን ልመናችን መልስ የሚያገኝበት፣ የሚያስፈልገን ሥጋዊ ነገር የምንናገኝበት፣ እጅግ አስቸጋሪ መስሎ የሚታየን የብቸኝነት የስደት ኑሮ የሚያበቃበት ጊዜ አለና ይህን በትዕግሥት መጠበቅ ይኖርብናል። “ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሰው እርሱ አይዘገይም” /ዕን 2፥3/ እግዚአብሔርን እናውቀውና እናከብረው ዘንድ ልመናችን ሊዘገይ ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔር የእኛን ልመና አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው በሚያስፈልገን ሰዓት እንደ አባታችን ኢዮብ ትዕግሥትን አለማምዶ ቢዘገይም ይሰጠናል። ትዕግሥት ባለማወቅም እንኳ ቢፈጽሙት ፍሬው እጅግ ታላቅና ጽድቅንም ያፈራል። “በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርጋችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው? ነገር ግን ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።” /ዕብ 12፥2-11/ እንዲሁም አባታችን ኢዮብ “እነሆ ቢገድለኝ ስንኳ እርሱን በትዕግሥት እጠብቃለው ነገር ግን መንገዴን በፊቱ አጸናለው” /ኢዮ 13፥15/ በማለት ይህ የመጣብኝ ሥጋዊ ፈተና ለሞት ቢዳርገኝም እንኳ በትዕግሥት ሞቴን እጠብቃለው እንጂ እምነቴን በሥጋዊ ፈተና ምክንያት ከእምነቴ ወደ ኋላ አልልም እንዳለ እኛም እንደ አባቶቻችን የመጣብንን ፈተና ሁሉ ታግሰን፣ የጽድቅን ፍሬ እንበላ ዘንድ ትዕግሥትን ገንዘብ ማድረግ ያስፈልጋል።
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ትዕግሥት ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ነው። /ገላ 5፥22-23/ የመንፈስ ፍሬ ብሎ የዘረዘራቸው ምግባረ ሰናያት እርስ በእርሳቸው ግንኙነት አላቸው። ዕምነት ያለው ሰው የውሃት፣ ቸርነት፣ በጎነት ሊኖረው ይገባል፤ ፍቅር ያለው ሰው ደስታ፣ ሰላም ከእነዚህም ጋር ትዕግሥትም አለው። ፍቅርና ዕምነት ያለው ሰው እራሱን መግዛት ይችላል። ፍቅር ይታገሳል እንዲል /1ቆሮ 13፥4/። ትዕግሥት ቻይ፣ ልበ ሰፊ፣ ትሁትና መሀሪ የሆነ ሰው ጠባይ መለያ ነው። ትዕግሥት ዘርፈ ብዙ ነው። በአገልግሎት፣ በጸሎት፣ በማህበራዊ ትዕግሥት አስፈላጊ ነው። ትዕግሥት የሌለው ሰው በቀላሉ ይጨነቃል፣ ይረበሻል፣ ይበሳጫል ምክንያቱም ለምን አሁን የምፈልገው ነገር አልሆነም ብሎ ስለማይረጋጋና ስለሚቸኩል ነው። በተለይ በስደት ዓለም ስንኖር የምናያቸው፣ የምንሰማቸው እና የምናገኛቸው ነገሮች በአብዛኛው ትዕግሥትን የሚፈታተኑ ስለሆኑ ትዕግሥት ከመቸውም በበለጠ ያስፈልጋል።
ጠቢቡ ሰሎሞን “ለሁሉም ጊዜ አለው” /መክ 3፥1/ እንዳለ ጸሎታችን ልመናችን መልስ የሚያገኝበት፣ የሚያስፈልገን ሥጋዊ ነገር የምንናገኝበት፣ እጅግ አስቸጋሪ መስሎ የሚታየን የብቸኝነት የስደት ኑሮ የሚያበቃበት ጊዜ አለና ይህን በትዕግሥት መጠበቅ ይኖርብናል። “ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሰው እርሱ አይዘገይም” /ዕን 2፥3/ እግዚአብሔርን እናውቀውና እናከብረው ዘንድ ልመናችን ሊዘገይ ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔር የእኛን ልመና አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው በሚያስፈልገን ሰዓት እንደ አባታችን ኢዮብ ትዕግሥትን አለማምዶ ቢዘገይም ይሰጠናል። ትዕግሥት ባለማወቅም እንኳ ቢፈጽሙት ፍሬው እጅግ ታላቅና ጽድቅንም ያፈራል። “በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርጋችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው? ነገር ግን ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።” /ዕብ 12፥2-11/ እንዲሁም አባታችን ኢዮብ “እነሆ ቢገድለኝ ስንኳ እርሱን በትዕግሥት እጠብቃለው ነገር ግን መንገዴን በፊቱ አጸናለው” /ኢዮ 13፥15/ በማለት ይህ የመጣብኝ ሥጋዊ ፈተና ለሞት ቢዳርገኝም እንኳ በትዕግሥት ሞቴን እጠብቃለው እንጂ እምነቴን በሥጋዊ ፈተና ምክንያት ከእምነቴ ወደ ኋላ አልልም እንዳለ እኛም እንደ አባቶቻችን የመጣብንን ፈተና ሁሉ ታግሰን፣ የጽድቅን ፍሬ እንበላ ዘንድ ትዕግሥትን ገንዘብ ማድረግ ያስፈልጋል።
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
3.ምኵራብ
ሦስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ‹ምኵራብ› ይባላል፡፡ ምኵራብ አምልኮተ እግዚአብሔር ሲፈጸምበት፣ ሕገ ኦሪት ሲነበብበት የነበረ በአይሁድ የሚሠራ መካነ ጸሎት ነው፡፡ ዘወትር ቅዳሜ ብዙ ሕዝብ ይሰበሰብበት ስለ ነበር ጌታችን ለማስተማር ብዙ ጊዜ በምኵራብ ተገኝቶአል፡፡ ስያሜው የተወሰደው በዮሐንስ ፪፥፲፬ ‹‹ወረከበ በምኵራብ እለ ይሠይጡ አልህምተ ወአባግዐ ወአርጋበ …፤ በመቅደስም በሬዎችን፣ ላሞችን፣ በጎችን፣ ርግቦችን፣ የሚሸጡትን አገኘ …›› ተብሎ ከተገለጸው ኃይለ ቃል ላይ ሲኾን፣ ‹ምኵራብ› የሚለው ቃልም በአማርኛ ‹መቅደስ› ተብሎ ተተርጕሟል፡፡ ምኵራብ የሚባለው ሳምንት ጌታችን ወደ ምኵራብ ገብቶ ማስተማሩ የሚነገርበት፤ ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፤ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅና የብር መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከነሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፤ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የስሙ መጠሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ መኾኗን ያስረዳበትና ያወጀበት፤ በቤተ መቅደስ የንግድ ሥራ ማከናወን እንደማይገባ ያረጋገጠበት ዕለት ነው፡፡
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
ሦስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ‹ምኵራብ› ይባላል፡፡ ምኵራብ አምልኮተ እግዚአብሔር ሲፈጸምበት፣ ሕገ ኦሪት ሲነበብበት የነበረ በአይሁድ የሚሠራ መካነ ጸሎት ነው፡፡ ዘወትር ቅዳሜ ብዙ ሕዝብ ይሰበሰብበት ስለ ነበር ጌታችን ለማስተማር ብዙ ጊዜ በምኵራብ ተገኝቶአል፡፡ ስያሜው የተወሰደው በዮሐንስ ፪፥፲፬ ‹‹ወረከበ በምኵራብ እለ ይሠይጡ አልህምተ ወአባግዐ ወአርጋበ …፤ በመቅደስም በሬዎችን፣ ላሞችን፣ በጎችን፣ ርግቦችን፣ የሚሸጡትን አገኘ …›› ተብሎ ከተገለጸው ኃይለ ቃል ላይ ሲኾን፣ ‹ምኵራብ› የሚለው ቃልም በአማርኛ ‹መቅደስ› ተብሎ ተተርጕሟል፡፡ ምኵራብ የሚባለው ሳምንት ጌታችን ወደ ምኵራብ ገብቶ ማስተማሩ የሚነገርበት፤ ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፤ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅና የብር መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከነሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፤ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የስሙ መጠሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ መኾኗን ያስረዳበትና ያወጀበት፤ በቤተ መቅደስ የንግድ ሥራ ማከናወን እንደማይገባ ያረጋገጠበት ዕለት ነው፡፡
#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)