መንፈሳዊ ህይወት
4.03K subscribers
437 photos
5 videos
8 files
62 links
✟✟✟በስመአብ ወወልድ በመንፈስ ቅድስ አሀድ አምላክ አሜን ✞✞✞
በዚህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ ስርአት የጠበቁ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ይጠቅሙናል ያስተምሩናል የምንላቸውን መንፈሳዊ
ትምህርቶች ብሒሎች ምክሮች እናስተላልፋለን።
ለሌሎች ሼር በማድረግ ቻናሉን ያጋሩ ✟✟✟

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
✍️✍️ ሀሳብ ወይም አስተያየት ;👇👇

https://t.me/Ortodoxe21 በዚ ይላኩልን
Download Telegram
ክፉ ሰው ክፋትን ለመስራት ደፍሮ ሲሄድ መልካም ሰው በጎ ነገር ለማድረግ ፈሪ ሆነ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ

#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ሞት እንዳለ አስታውስ፦ እንዲሁ በዓለም ያለ ፈተናም እንደሚያልፍ። “ከፀሐይ በታች የተሠራውን ሥራ ሁሉ አየሁ፤ እነሆም፥ ሁሉ ከንቱ ነው፥ ነፋስንም እንደ መከተል ነው።” መክብብ 1፡14 ማለትን ትረዳለህ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
አንተ ሐሳብህን ልትመራዉ እንጂ፤ ሐሳብህ አንተን ሊመራ ቦታ አትስጠዉ፥ እዉነተኛ ክርስቲያን ስሜቱ የሚመራዉ ሳይሆን ስሜቱን የሚወመራ ነዉ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ጨዋ ሰው በሌሎች ሰዎች መጎሳቆል ላይ የራሱን ምቾት አይገነባም እርሱ የሌሎችን ሰዎች ምቾት ለማደላደል የራሱን ምቾት ይረሳልና።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ሥጋችን ምግብ ሲያጣ እንደሚደክም ሁሉ ነፍስም ምግቧን የእግዚአብሔርን ቃል ስታጣ ትደክማለች።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#join
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ዓብይ ጾም››

ጾም የቃሉ መሠረታዊ ትርጉም መታቀብ መከልከል ማለት ነው በቤተክርስቲያናችን እምነትና ትምህርት ጾም ማለት የሰው ልጅ ሕይወቱን ለሰጠው የሕይወትን መመሪያ ላዘጋጅለት ፈጣሪ እየታዘዘ ኃጢዓትን ለማስተሰረይ የምኞት ፍትወትን ኃይል አድክሞ ሥጋ ለነባቢት ነፍስ ትገዛለት ዘንድ በሕግ በታወቁ ጊዜያት ከመብል መጠጥ በመከልከልና የመንፈስ ብርታት ማግኛ የጥበብ መንገድ ነው::

ጾም ጸሎት ምጽዋት የተያያዙ የሥነ ምግባር ሰንሰለቶች ስለሆኑ በተግባር ተጠብቀው ሲተረጎሙ የእኛንም ሕይወት ከእግዚአብሔር ጋር ያገናኛሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ እንደምናነበው አበው ማንኛውንም ሥራ ለመሥራት ሲያስቡና ሲያቅዱ፣ ሲጀምሩና ሲፈጽሙ በጾም በጸሎት ነው፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ›› እንዲል (ኤፌ 6፡10) የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር የተባሉ መሣሪያዎች ጾም፣ ጸሎት ፣ ምጽዋት አጠንክሮ የሚጠቀምባቸው ክርስቲያን የችግርን ጊዜ የማለፍ ኃይል ይኖረዋል፡፡

ጸሎት እምነት እንዲለመልም እንዲፋፋ እንዲያፈራ ይረዳል፣ ጾም ደግሞ እምነትን ጸሎትን እያጠናከረ ብዙ ድንቅ ሥራዎች እንዲሰሩ ያደርጋል፡፡

ጾም ነፍስን በእግዚአብሔር ፊት ትሑት ያደርጋል የሥጋን ፈቃድ አስገዝቶ ነፍስ እንድትነፃ እንድትቀደስ አቋሟን እንድታስተካክል ይረዳታል ጾም ለነፍስ ብቻ ሳይሆን በሥጋ ሕይወትም ለሆድ ዕቃዎች (ለሰውነታችን) የውስጥ የምግብ ማዘጋጃ ክፍሎች ዕረፍትን ይሰጣል ጾም ትሑትና ቅን ያደርጋል በሥጋዊ ፍላጎቶቻችን ፈቃዶቻችን ላይ አዛዦች መሆናችንን ያረጋግጥልናል፡፡

ጾም ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ተቃራኒ በሆኑ ርኩሳን መናፍስትና በአጋንንት ላይ ኃይል እንድናገኝ ከፈተናዎች እንድንድን ይረዳል ክህደትን ጥርጥርን ያጠፋል እምነትንና በእምነት የምንሰራቸውን ሥራዎች ያጠናክራል የጥበብን መንገድ የሕይወትን ጎዳና ይገልፃል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትና ድንጋጌ (የሕግ ምንጭ) በሆነው ፍትሐ ነገሥት ስለጾም በተመለከተው አንቀጽ እንደተገለጸው ጾም

_ ጾመ ሕግ

_  ጾመ ፈቃድ ተብሎ በሁለት ይከፈላል

ጾመ ሕግ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ የኒቂያ ጉባኤ ሊቃውንት አበው በወሰኑት መሠረት ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 ላይ የተመለከቱትና ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾሟቸው የታዘዙት አፅዋማት ሰባት ሲሆኑ

ዐብይ ጾም

ጾመ ድህንት (ረቡዕና ዓርብ)

ጾመ ነነዌ

የልደትና ጥምቀት (ጋድ/ገሐድ ጾም)

የሐዋርያት (የሰኔ) ጾም

የነቢያት (የገና) ጾም

የፍልሰታ ጾም ናቸው

እነዚህ አጽዋማት የየራሳቸው የሆነ ታሪክና ትንታኔ ያላቸው ሲሆኑ ሁሉም ያለ ልዩነት በሁሉም ክርስቲያኖች በይፋ በማህበር እንዲጾሙ የተወሰኑ ናቸው፡፡

ጾመ ፈቃድ በግል ውሳኔ በኀጢዓት ስሜት የሻከረ ኅሊናን ለማጥራት ወይም ቅድስናን ጸጋና የበለጠ መንፈሳዊ ክብር ለማግኘት በመምህረ ንስሐ አማካኝነት አለዚያም ብቻ ለብቻ በሥውር አይቶ በግልፅ የሻቱትን ለሚሰጥ አምላክ የሚቀርብ ነው፡፡

ከሕግ አጽዋማት መካከል በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አቢያተ ክርስቲያናት እምነትና ሥርዓት በየአመቱ ከሚመላለሱት አጽዋማት ዋናውና ትልቁ ጾመ ሁዳዴ (አብይ ጾም) ነው፡፡

ይህንን ጾም የምንጾመው ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን  አብነትና አርአያ አድርገን ነው:: አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ከመጀመሩ በፊት በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ በመሄድ ከቆመ ሳይቀመጥ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ እህል ውሃ ሳይቀምስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ የዚህ ዓለም ተፈታታኝ የሆነ ዲያብሎስን ከነፈተናው ድል ነስቶታል፡፡ በስስት ፣ በትዕቢት፣ በፍቅረ ንዋይ የመጣውን ፈተና አጥፍቶ የኃጢዓትን እሾህ አቃጥሏል፡፡

–    ስስት ያልተሰጡትን መሻት የሌሎችን ድርሻ በይበልጥ ለመሻማት መሞከር

–    ትዕቢት አምላክ እሆናለሁ ማለት በሌሎች ላይ ታላቅነትን፣ የበላይነትን መመኘት

–    ፍቅረ ንዋይ ያለኝ ይበቃኛል አለማለት በተሰጡት አለማመስገን ነው
እነዚህ ሦስቱ አርዕስተ ኃጣውዕ ይባላሉ፡፡ እያንዳንዳችን የልቡናችን በር ከፍተን እንደገና ካላስገባናቸው በቀር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ተወግዷል

ሀ/ ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾመ

እርሱ ሠራዔ ህግ (ህግን የሠራ) ነውና፣ ሕግንና ነቢያትን ያጸና ዘንድ አንድም ሕግን ይሠራ ዘንድ ጾምን የሥራው መጀመሪያ አደረገ

አንድም ለሐዋርያት ለሊቃውንት እንዲሁም ከዚያ በኋላ ለሚነሱት ክርስቲያኖች ሁሉ አርአያና ምሣሌ አብነትም ለመሆን 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሞ ጸልዮ ሥራ ጀምሯል፡፡ ከዚያ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ከእርሱ በተማሩት መሠረት የሥራቸው መጀመሪያ ያደረጉት ጾምን ነው፡፡ (ሐዋ 13፡1)

መብል ለኃጢዓት (ለጥንተ አብሶ) መሠረት በመሆኗ በመብል ምክንያት ኃጢዓት ወደ ዓለም መጥቷልና፣ በመብል ምክንያት ወደ ዓለም የገባው ኃጢዓትና ኃጢዓት ያስከተለው ሞት ከሥራቸው ተነቅለው ተደምስሰው፣ የጠፋው የሰው ሕይወት የታደሰው በጌታችን ጾም ነው:: ሰው በሥጋዊ መብልና መጠጥ ብቻ ሰውነቱ የሚያምር በጾም የሚጠወልግ የሚጎዳ እየመሰላቸው ጾምን የሚፈሩት የሚሸሹት ጥቅም እንደማይሰጥ ሰው ሰራሽ ሥርዓት አድርገው የሚመለከቱትም ብዙ ናቸው፡፡ አስተዋዮች ግን ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃለ እግዚአብሔር ጭምር እንጂ በእህል ውሃ ብቻ ሊኖር እንደማይችል ጠንቅቀው አውቀው እየጾሙ ይጠቀሙበታል አስፈላጊም በሆነ ቦታና ጊዜ ከማይፈለግ ጮማና ወይን ይልቅ ጥራጥሬ ተመግቦ መውዛት ማማር እንደሚኖር ከሶስቱ ወጣቶች (አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤል) ታሪክ መማር ይቻላል፡፡ (ዳን 1፡8-16)

ምሳሌው ይደርስ ዘንድ (ለጊዜው)

ቀድሞ አባቶቹ ነቢያት አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመዋል ከዚያ ቢያተርፍ አተረፈ ብለው ቢያጎድል አጎደለ ብለው አይሁድ ደገኛይቱን ሕግ ሕገ-ወንጌል ከመቀበል ይከላከሉ ነበር፡፡

‹‹እኔ ሕግና ነቢያትን ልፈጽም እንጂ ልሽር አልመጣሁም›› ብሏልና (ማቴ 5፡17) ሕግና ሥርዓትን እየፈጸመ ከሕግ በታች ሆኖ ተመላለሰ

ሀ/ ሙሴ በአርባ ዘመኑ ለዕብራዊው ወገኑ አግዞ ግብጻዊውን ገድሎ በአሸዋ ቀብሮታል (ዘጸ 2፡11) ሙሴ የወልድ እግዚአብሔር፣ ዕብራዊው ወገኑ የአዳም ፣ ግብጻዊው የዲያብሎስ፣ አሸዋው የመስቀል ምሳሌ ነው፡፡

ሙሴ ግብጻዊውን ገድሎ በአሸዋ እንደቀበረ ጌታችንም ጾሞ ጸልዮ ዲያብሎስንና ፈተናዎቹን ድል ነስቷል፡፡

ለ/ ሙሴ 40 ዘመን በምድያም ኖሮ እስራኤልን ከግብፅ የባርነት ቀንበር ነፃ አውጥቷል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም እንጂ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሞ ጸልዮ ነፍሳትን ከሲኦል ነጻ ያወጣልና

ሐ/ ሕዝበ እስራኤል የገዳም ምሳሌ በሆነው በቃዴስ በረሃ 40 ዘመን ኖረው ምድረ ርሥት ኢየሩሳሌም ገብተዋል፣ (ዘጸ 14፡19 ፣ 32፡34) እናንተም 40 ቀንና 40 ሌሊት ብትጾሙ ርስት መንግስተ ሰማያትን ትወርሳላችሁ (ዘጸ 16፡4-17)

መ/ ሙሴ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሞ ጸልዮ ለሕይወታችን መመሪያ በእግዚአብሔር ጣት የተጻፉ አስርቱ ቃላት ያለባቸው ጽላቶች ተቀብሏል፡፡ ሕገ – ኦሪትን ሠርቷል (ዘጸ 34፡28)

ኢየሱስ ክርስቶስም እንጂ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሞ ጸሊዮ ሕገ-ኦሪትን አጽንቶ ደገኛይቱን ሕግ ህገ-ወንጌልን (ስድስቱን ቃላተ ወንጌል) ሠርቷል፡፡

#join #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21

#መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
መንፈሳዊ ህይወት pinned «ዓብይ ጾም›› ጾም የቃሉ መሠረታዊ ትርጉም መታቀብ መከልከል ማለት ነው በቤተክርስቲያናችን እምነትና ትምህርት ጾም ማለት የሰው ልጅ ሕይወቱን ለሰጠው የሕይወትን መመሪያ ላዘጋጅለት ፈጣሪ እየታዘዘ ኃጢዓትን ለማስተሰረይ የምኞት ፍትወትን ኃይል አድክሞ ሥጋ ለነባቢት ነፍስ ትገዛለት ዘንድ በሕግ በታወቁ ጊዜያት ከመብል መጠጥ በመከልከልና የመንፈስ ብርታት ማግኛ የጥበብ መንገድ ነው:: ጾም ጸሎት ምጽዋት የተያያዙ…»
ሠ/ ነቢዩ ኤልያስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሞ በእሳት ሠረገላ በአውሎ ንፋስ ተነጥቆ ወደ ገነት (ብሔረ ሕያዋን) አርጓል፣ ገብቷል እናንተም 40 ቀንና 40 ሌሊት ብትጾሙ ገነት መንግስተ ሰማያት ትገባላችሁ፡፡ (1ኛ ነገ 19፡8 ፣ 2ኛ ነገ 2፡11)

ረ/ ነቢዩ ሕዝቅኤል በግራ ጎኑ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ተኝቶ ስድስት መቶ ሙታን አስነስቷል እናንተም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ብትጾሙ ትንሣኤ ዘለ ክብር ትነሣላችሁ ለማለት ፣

ሰ/ ዕዝራ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከምግብ ተከልክሎ የጥበብ ሕይወት መመሪያ መጻሕፍትን ጽፏል (ዕዝ 7፡6) እነዚያ ቀን ሲጽፉ እየዋሉ ማታ ይመገባሉ እርሱ ግን ቀን ሲያጽፈው የሚውለውን ማታ ሲያስበው ያድር ነበር፡፡

እናንተም 40 ቀንና 40 ሌሊት ብትጾሙ ምሥጢር ይገለጥላችኋል ለማለት፡፡

ሰ/ ነቢዩ ዳንኤል ከሀገሩ ከኢየሩሳሌም በምርኮ በተወሰደበት ሀገር በአንድ አምላክ ላይ ከነበረው ጽኑ እምነት ሳያወላውል በጾም በጸሎት ተወስኖ በመገኘቱ ከአንበሶች አፍ እንደ ዳነ ፣ ሕልምን የመተርጎም ዕውቀት ጥበብ እንደተሰጠው ሀገሩ ኢየሩሳሌም ነጻ የምትሆንበትን ወገኖች እስራኤል ከስደት የሚመለሱበት ከዚህም በላይ ረቂቅና ጠለቅ ያለ የክርስቶስ ሰው የመሆን ምስጢር እንደተገለጸለት በሱባዔው ፍጻሜ መላዕክት ተልከው እንዳረጋጉት የምስራች ዜና እንዳሰሙት ፈተናውን ሁሉ ድል እንዳደረገ (ዳን 9፡2-4 ፣ ዳን 10፡2-14)

እኛም ጥበብ እውቀት እንዲገለጽልን በሀገርና በወገን ላይ የመጣው መዓትና መከራ እንዲወገድ ነውራችን እንዲከባለል ለኃጢዓታችን ስርየት እንድናገኝ፣ ከነፍሳችን ቁስል እንድንፈወስ ጾምን እንጹም፡፡

 

ጌታችንና አምለካችን ኢየሱስ ክርስቶስ 40 ቀንና 40 ሌሊት የጾመበት ፍጻሜው ግን፡-

ሀ/ አዳም ልጅነት የተሰጠው በ40 ቀኑ ነበር በተፈጠረበት ምድር ኤልዳ በምትባል ቦታ ቆይቶ ገነት ገብቷል፡፡

በ40 ቀን ተሰጥቶት የነበረውን ልጅነት በመብል ምክንያት አጥቶት ስለነበረ

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ ልጅነቱን (ለአዳም) ሊመልስ ፍጹም ካሣ እንደ ካሰ ለማጠየቅ (ኩፋ 4፡9)

ለ/ አንድም ፅንስ ሁሉ በእናቱ ማህፀን በ40ኛው ቀን ተሰዕሎተ መልክዕ ይይዛል (ይፈጸምለታል)

በመሆኑም በ40ኛው ቀን ተስዕሎተ መልክዕ ለተፈጸመለት ክቡር የሰው ዘር ሁሉ ፍጹም ካሳን ሊክስ እንደመጣ ለማጠየቅ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾመ፡፡

ሐ/ በሌላው ሰው የተሰራው ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከአምስተኛ ባሕርያተ ነፍስ በመሆኑ ለአራቱ አስር አስሩን ለመካስ ወይም አራቱ ባሕርያተ ሥጋና አምስተኛ ባሕርያተ ነፍስን አድርጎ ለአምስቱ ስምንት ስምንት ለመካስ እንደመጣ ለማጠየቅ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾመ

4×10 = 40 ወይም 5×8= 40
ለምን 55 ቀን እንጾማለን ???

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው 40 ቀንና 40 ሌሊት ብቻ ነው፤ በቤተክርስቲያናችን ግን አበው ቀኖና ሰርተው እንድንጾም የወሰኑት 55 ቀን ነው፡፡ ይህ እንደምን ነው ቢሉ ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡

1.  አንድም ክርስቶስ 40 ቀናት የጾመው ከቆመ ሳይቀመጥ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፣ እህል ውሃ ሳይቀምስ በመሆኑ እኛም እህል ውሃ የሚበላባቸውን በ55ቱ ቀን ያሉትን ቅዳሜና እሁድን ብንቀንሳቸው 40 ቀናት ከእህል ከውሃ፣ ከጥሉላት የሚጾምባቸው ፍጹም ሱባዔ ይሆናልና ነው፡፡

2.  በሌላው ከ40ኛው ቀናት ፊትና ኋላ ያሉትን ሁለቱን ሳምንታት ከፍ ሲል አበው ሐዋርያት ዝቅ ሲል ሃይማኖታቸው የቀና፣ ርቱዓነ ሃይማኖት 318ቱ ሊቃውንት ከዚያም በኋላ የተነሱ አበው ሊቃውንት ከ40ው ጾም ጋር አብሮ እንዲጾም ሕግ ስለሰሩ ነው፡፡

ሀ/ የመጀመሪያው ሳምንት (ከ40ው ቀን በፊት) ያለው እንዲጾም የተወሰነበት ወይም የሚጾምበት ምክንያት ‹‹ፎቃ የተባለ ንጉሥ አገዛዝ አጽንቶባቸው በኢየሩሳሌም የሚኖሩ ምዕመናን ህርቃል እንዲረዳቸው በጠየቁት ጊዜ ለመርዳት ፈቃደኛ ቢሆንም ሐዋርያት ሰው የገደለ ሰው ዕድሜውን ሙሉ እንዲጾም ስለወሰኑ በጉዳዩ የሚቸገርበት መሆኑን ገለጸላቸው ሕዝቡም የአንድ ሰው ዕድሜ ሰባ፣ ሰማንያ ነው እኛ እንጾምልሀለን ዘምተህ ጠላቶቻችንን አስወግድልን ስላሉት ቃላቸውን ተቀብሎ ችግራቸውን አስወግዶላቸዋል እነርሱም አምስት አምስቱን ቀን ተካፍለው ጾመውለታል›› ያላወቁት ምዕመናኑ ወይም ሕዝበ ክርስቲያኑ አንድ ጊዜ፣ ያወቁት የተረዱት ከምስጢር ባለጸጋ የሆኑት አበው ሐዋርያት ጹሙ ብለው ሥርዓት አድርገው በየዓመቱ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ አበው ሐዋርያት ከትምህርተ ወንጌል ሥምሪት አስቀድሞ አምስት አምስት ቀን የመጾም ልማድ እንደነበራቸውም ታውቋል፡፡

ለ/ ሌላው ከ40ው ቀን በኋላ ከሆሣእና እስከ ትንሣኤ ያለው ሳምንት ሰሞነ ሕማማት ነው፡፡ በሕማማት ሰሞን የዓለም መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ደኅንነት ሕማም መከራ የተቀበለበት በመስቀልም የሞትን ጽዋ ተቀብሎ ለሞት ኃጢዓት ከመገዛት ነጻ ያደረገን ስለሆነ ህማሙን፣ ምክረ ሞቱን ለኛ ሲል የተቀበለውን ፀዋትወ መከራ በጾም በፀሎት በሰጊድ በኀዘን ለማሰብ በቤተክርስቲያን አበው የተወሰነ በመሆኑ ማንኛውም ክርስቲያን ‹‹ጾም በእናንተ ዘንድ የከበረ ይሁን›› ብለው የዓለም ብርሃናት ብፁዓን ሐዋርያት በዲድስቅልያቸው (አንቀጽ 29) በወሰኑት መሠረት ከጥሉላት መባልዕት ሥጋ፣ ቅቤ፣ ወተት፣ ዓሣ ተከልክሎ ከ40ው ቀን ጋር አንድ ላይ ይህን ጾምም ሆነ ሌሎች አጽዋማትን እንዲከታተል ግዴታ አለበት።

#join #share
💚 @linkortodoxe21 💚
💛 @linkortodoxe21 💛
❤️ @linkortodoxe21 ❤️
ጾም ምንድነው???

ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገር ሁሉ መከልከል ማለት ነው፡፡ ወይም ለሥጋ የሚመቸውን ነገር መተው ማለት ነው፡፡ 

ጌታችን መጾም ሳያስፈልገዉ የጾመዉ በጾም መሳሪያነት ዲያብሎስን ድል ታደርጋላችሁ ሲለን ነዉ፡፡እርሱ ድል አድርጎለታልና ካልጾሙ ካልጸለዩ ሰይጣንን ድል ማድረግ እንደማይቻል ጌታ አስተምሮናል፡፡

ጾም ፊትን ወደ እግዚአብሔር ማቅናት እንደሆነ በሰብአ ነነዌ ታዉቋል እነዚህ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር የተመለሱት በጾም ነዉና፡፡ኃጢአታቸዉ እጅጉን ገዝፎ ቅድመ እግዚአብሔር ስለደረሰ የጌትነቱ ጨንገር ከመምጣቱ አስቀድሞ ንስሓ እንዲገቡ መሐሪ እግዚአብሔር ነብዩ ዮናስን ላከላቸዉ፡፡ሕዝቡም የነቢዩ ስብከትን ሰምተዉ በክፉ ስራቸዉ ተጸጽተዉ ከሊሒቅ እስከ ደቂቅ ማቅ ለበሱ አመድንም በራሳቸዉ ነሰነሱ፡፡ንጉሱም ከዙፋኑ ወርዶ መጎናጸፊዉን አዉልቆ ማቅ ለብሶ በአመድ ላይ ተቀመጠ፡፡አዕምሮ ጠባይዕ ያላደፈባቸዉ ሕጻናትና እንስሳትንም የንስሓቸዉ ተካፋዮች እንዲሆኑ አደረጉ፡፡በዚህ ጊዜ የፍጥረቱን መዳን እንጂ ጥፋቱን የማይወድ እግዚአብሔር ቁጣዉን በትዕግስት መዓቱን በምህረት መልሶ በይቅርታ ጎበኛቸዉ ከጠቀጣዉ መቅሠፍት አዳናቸዉ፡፡ዮና 3-5-10

ወደ እግዚአብሔር በጾም በጸሎት የተመለሱ ድኅነትን እንዳገኙ ሁሉ ያልተመለሱት ደግሞ ጠፍተዋል፡፡ለምሳሌ ሰብአ ሰዶም ገሞራ እንደ ነነዌ ሰዎች በጾም ወደ እግዚአብሔር ባለመመለሳቸዉ እሳት ከሰማይ ወርዶ አቃጥሎ አጥፍቷቸዋል፡፡ዘፍ 19-23


አብይ ፆም መባሉ ትልቅና ታላቅ ፆም መሆኑን ለማሳወቅ ነው። ይህ ፆም ታላቅ

መባሉም ለ55 ቀናት ያህል መፆሙና ከሌሎቹ አፅዋማት ጋር ሲነፃፀር በቁጥር መብለጡ ብቻ ሳይሆን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ

ቆሮንቶስ መፆም ሳይገባው ለእኛ አርአያና ትልቅ ምሳሌ ለመሆን የፆመው ጾምም በመሆኑ ነው

#Join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
ዘወረደ

ትርጕሙ ‹ከሰማየ ሰማያት የወረደ› ማለት ነው፡፡ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን፣ ከድንግል ማርያም የተወለደውን በጥንት ስሙ ወልድ፣ ቃል በኋላ ስሙ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አማኑኤል የተባለውን ሰው የኾነውን አምላክ ለማመስገን ርደቱን (ከሰማየ ሰማያት መውረዱን) ለመዘከር የሚጾም ጾም ነው፡፡ ጌታችን ጾመ ከማለት አስቀድሞ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን መናገር አስፈላጊ ነውና የመጀመሪያው ሳምንት ‹ዘወረደ› ተብሏል፡፡ ‹‹አንተ በሰማይ ወአንተ በምድር ወአንተ በባሕር ወአንተ በየብስ፤ አንተ በሰማይ አለህ፤ በምድር በባሕርም በየብስም አለህ፤›› የተባለውን በሰማይ በምድር ምሉዕ የኾነውን አምላክ ‹ወረደ፤ መጣ› ብሎ መናገር ‹ሰው ኾነ› ማለት ነው፡፡ ሰው ኾኖ መገለጡን ለማስረዳት ነው እንጂ መውረድ መውጣት የሚባሉ ቃላት በዅሉ ምሉዕ ለኾነው መለኮት አይስማሙትም፡፡ ቃላቱ ሰውኛ አነጋገርን የሚያመለክቱ ናቸውና፡፡ መተርጕማን አበው ‹‹‹ዘወረደ› ማለት ‹ሰው የኾነ› ማለት ነው›› ብለው ይተረጕማሉ፡፡ አምላካችን ሰው ከኾነ በኋላ ‹መጣ፤ ሔደ፤ ወረደ፤ ዐረገ› የሚሉ ቃላት ይስማሙታል፡፡ ምልዓቱን ሳይለቅ በሰው አካል ተወስኖ ታይቷልና፡፡ ስለዚህ ‹ወረደ› እግዚአብሔር ሰው ኾኖ መገለጡን፤ ‹ዐረገ› ደግሞ የሰውነቱን ሥራ መፈጸሙን ያሳያል፡፡ ዐረገ ስንልም ቀድሞ በሰማይ የለም ለማለት አይደለም፤ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመለኮቱ በዓለሙ ዅሉ ምሉዕ ነውና፡፡

ጾሙን ሐዋርያት፣ ስያሜውንና የምስጋናውን ሥርዓት ቅዱስ ያሬድ አዘጋጅተዋል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ነቢያትን በንባብ፤ ሐዋርያትን በስብከት፤ ሊቃውንትን በትርጓሜ፤ መላእክትን በዜማ ይመስላቸዋል፡፡ ቅዱስ ያሬድ የመላእክትን የምስጋና ሥርዓት ወደ ምድር አምጥቷል፡፡ የነቢያትን ትንቢት፣ የሐዋርያትን ትምህርት በሚገባ ተርጒሞ፣ አብራርቶ፣ አመሥጥሮ አዘጋጅቶታል፡፡ ሐዋርያት ጾሙን ጾመው የጾም ሕግ ደንግገዋል፤ ቅዱስ ያሬድም ለጾሙ ስያሜ ሰጥቶ ምስጋና ከነሥርዓቱ አዘጋጅቶ አቅርቧል፡፡ቤተ ክርስቲያናችንም የመጀመሪያው የዐቢይ ጾም ሳምንትን (ዘወረደን) ስያሜ እንደ ቅዱስ ያሬድ ከሐዋርያት ተቀብላ ታስተምራለች፡፡ ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ‹ጾመ ሕርቃል› እየተባለም ይጠራል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊዮስ) በ፮፻፲፬ ዓ.ም የነበረ የቤዛንታይን ንጉሥ ነው፡፡ ለክርስቲያኖች ባደረገው ርዳታ ምክንያት አንድ ሳምንት ጾመውለት ነበር፡፡ ያላወቁ ‹ጾመ ሕርቃል› ብለው አንድ ጊዜ ጾመው ትተውታል፡፡ ጥንቱን የቅዱሳን ሐዋርያት መኾኑን ያወቁ ምእመናን ግን ዅልጊዜ በየዓመቱ ይጾሙት ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ ጾመ ሕርቃል እየተባለ ይጠራል፡፡ ሙሉ ታሪኩ በፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ አንቀጽ ፲፭ ላይ ይገኛል፡፡

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት pinned «ዘወረደ ትርጕሙ ‹ከሰማየ ሰማያት የወረደ› ማለት ነው፡፡ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን፣ ከድንግል ማርያም የተወለደውን በጥንት ስሙ ወልድ፣ ቃል በኋላ ስሙ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አማኑኤል የተባለውን ሰው የኾነውን አምላክ ለማመስገን ርደቱን (ከሰማየ ሰማያት መውረዱን) ለመዘከር የሚጾም ጾም ነው፡፡ ጌታችን ጾመ ከማለት አስቀድሞ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን መናገር አስፈላጊ ነውና የመጀመሪያው…»
የምትጠላው ሰው ካለህ እንዳትጾም !! መጽሐፉ

" ወንድሙን የሚጠላ ነብሰ ገዳይ ነው"
ይላልና አትድከም 1ኛ ዮሐ 3÷15

👉ፍቅር ከሌለህ እንዳትጾም !! መጽሐፉ
" ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም "
ይላልና አትድከም 1ኛ ዮሐ 4÷8

👉 ዘረኛ ከሆንክ እንዳትጾም !!
ክርስቶስ ከዘር ከቋንቋና ከነገድ እንደዋጀህ
አላመንክምና አትድከም ራእይ 5÷9

👉ይቅርታ ማድረግ ካልቻልክ እንዳትጾም !! መጽሐፉ ወንድምህን ይቅር ካላልክ እግዚአብሔር ይቅር
አይልህም ይላልና አትድከም ማቴ 18÷35

👉በእጅህ ያለውን ደም ካልታጠብክ እንዳትጾም!! መጽሐፉ " የሰውን ደም የሚያፈስ ሁሉ ደሙ ይፈሳል "
ይላልና አትድከም ዘፍ 9÷6

👉ወዳጆጄ ሆይ! ...
ጾም አምልኮ ነው እንጂ ተራ የምግብ ለውጥ ብቻ የምናደርግበት ወግ አይደለምና አስቀድመን ንስሃ እንግባ !!

join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጾምንእንዴትመቀበልእንደሚገባን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል፦
ሙሽሪቱን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች አስቀድመው ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይጠርጉታል፡፡ የቆሸሸ ልብስን የለበሰ ሰው ወደ ሰርጉ አዳራሽ እንዳይገባ ያደርጉታል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚችለው የሰርግ ልብስ የለበሰ ሰው ብቻ ነው፡፡
እናንተም እንዲህ ልታደርጉ ይገባችኋል፡- ልቡናችሁን በማንጻት፣ አብዝቶ ከመብላትና ራስን ካለመግዛት በመራቅ የምግባር እናት፣ የማስተዋልና የሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ደጀ ልቡናችሁን በመክፈት ልትቀበሏት ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደ ኾነ ታላቅ ሐሴት ታደርጋላችሁ፤ እርስዋም ቁስለ ነፍሳችሁን ትፈውስላችኋለች፡፡


join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
👍1
1የጾም ሥርዓት

መጽሐፍ ‹‹ተሰአሎ ለአቡከ ወይነግረከ፤ አባትህን ጠይቅ፤ ይነግርህማል፤›› /ዘዳ.፴፪፥፯/ እንዳለ ጾም እንዴት እንደሚጾም አባቶችን መጠየቅ እና የአባቶችን ፈለግ መከተል ያስፈልጋል፡፡ ቅዱስ  ኤጲፋንዮስ ‹‹ቤተ ክርስቲያን እናቱ ያልኾነች ሰው እግዚአብሔር አባቱ አይኾነውም›› በማለት እንደ ተናገረው ያለ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔርን፤ ያለ እግዚአብሔር ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን ማወቅ አይቻልም፡፡ ስለዚህ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን እየሔዱ ቃለ እግዚአብሔር መማር፣ መጸለይ፣ ሥጋውን ደሙን መቀበል መገስገስ ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው፡፡ ‹‹ቤተ ክርስቲያን ለክርስቲያን›› እንዲሉ አበው፡፡ በጾም ወቅት ደግሞ ይህንን ተግባር ይበልጥ ማሳደግ ይገባል፡፡

በጾም ወቅት የሥጋ አለቃ ነፍስ ናት፡፡ ነፍስ ፈላጭ፣ ቆራጭ፣ አዛዥ ናት፡፡ ሰው መልካም ሥራ ከሠራ በነፍስ በሥጋው ይቀደሳል፤ ገነት (መንግሥተ ሰማያትን) ይወርሳል፡፡ ክፉ ከሠራ ደግሞ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን ያጣል፤ ወደ ሲኦል (ገሃነመ እሳት) ይወርዳል፡፡ ሰው ኀጢአተኛ ነው ሲባል ፈቃደ ሥጋው ሠልጥኖበታል ማለት ነው፡፡ ጻድቅ  ነው ሲባል  ደግሞ ፈቃደ ሥጋውን አሸንፏል (ለፈቃደ ነፍሱ እንዲገዛ አድርጓል) ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰው ሲቀደስም፣ ሲረክስም የሚኖረው በፈቃደ ሥጋ እና ፈቃደ ነፍስ መካከል ባለው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ትግል ነው፡፡

ጾም ራስን ዝቅ የማድረግ፣ የጸሎት እና የንስሐ ጊዜ እንደኾነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይነግሩናል፡፡ /ዕዝ. ፰፥፳፩፤ ነህ. ፩፥፬፤ ዳን.፱፥፫/፡፡ ስለዚህም ራሳችንን ዝቅ በማድረግ (በትሕትና) መጾም ይገባናል፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በምዕራፍ ፶፰ ቍጥር ፭ ላይ ‹‹እኔ የመረጥኩት ጾም ይህ ነውን? ሰውስ ነፍሱን የሚያዋርደው እንደዚህ ባለ ቀን ነውን? በውኑ ራሱን እንደ እንግጫ ዝቅ ያደርግ ዘንድ ማቅንና አመድንም በበታቹ ያነጥፍ ዘንድ ነውን?›› ይላል፡፡ እንግጫ ማለት ባሕር ውስጥ የሚበቅል ሣር ነው፡፡ በቀዳም ሥዑር ካህናት ‹‹ጌታ ተመረመረ፤ ዲያብሎስ ታሰረ፤›› እያሉ ለደስታ መግለጫ የሚሰጡት እና ራስ ላይ የሚታሰር ለምለም ሣር ነው፡፡ እንግጫ (ግጫ – በአንዳንድ አካባቢዎች) ሲያድግ ራሱን ዝቅ ያደርጋል፤ እያደገ ሲሔድ ራሱን ይደፋል (ዝቅ ያደርጋል)፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ ራሳችሁን እንደ እንግጫ (ግጫ) ዝቅ አድርጉ ማለቱ  በጾም ወቅት ‹‹እንደዚህ ነው የምጾመው፤ እስከዚህ ሰዓት ድረስ ነው የምጾመው›› እያልን ውዳሴ ከንቱን መሻት የለብንም ሲል ነው፡፡ ሰው እያወቀ ሲሔድ ራሱን ይደብቃል እንጅ ራሱን ከፍ ከፍ አያደርግም፡፡ የጾም ወቅት ትሕትናን ገንዘብ የምናደርግበትና ይበልጥ የምናሳድግበት ወቅት ነው፡፡ አንድ ክርስቲያን ፈተናን ችሎ በትዕግሥት የሚያሳልፍ፣ እየሰማ የሚተው መኾን አለበት፡፡ ነቢዩ ዕዝራም በመጽሐፈ ዕዝራ ፰፥፳፩ ላይ ‹‹በአምላካችን ፊት ራሳችንን እናዋርድ ዘንድ ከእርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛ እና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ በዚያ በአኅዋ ወንዝ አጠገብ ጾም አወጅሁ›› በማለት ራስን ዝቅ በማድረግ ለአምላክ ፈቃድ መገዛት እንደሚገባ ያስተምረናል፡፡

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
👍1
"የሚጠብቀኝ_አይተኛም"_|_"Yemitebekegn_Aytegnam"_ሊቀ_መዘምራን_ይልማ_ኃይሉ(480p)_16
<unknown>
🌱🌱🌿🌿🍀🍀የሚጠብቀኝ አይተኛም (2×)
አያንቀላፋም
የሚጠብቀኝ አይተኛም(2×) አያንቀላፋም 🌿🌿🍀🍀🍀🌱🌱🌱

join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
2 .የጾም ሰዓት

ስለ ጾም ሲነገር የጾም ሰዓትም አብሮ ይነሣል፡፡ በዘፈቀደ ሳይኾን በሰዓት የተወሰነ ጾም መጾም እንደሚገባን መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል፡፡ ‹‹የእስራኤልም ልጆች ዅሉ ሕዝቡም ዅሉ ወጥተው ወደ ቤቴል መጡ፤ አለቀሱም፡፡ በዚያም በእግዚአብሔር ፊት ተቀመጡ፡፡ በዚያም ቀን እስከ ማታ ድረስ ጾሙ፤›› ተብሎ እንደ ተጻፈ /መሳ.፳፥፳፮/፡፡ የጾም ሰዓትም በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፲፭ ተዘረዝሯል፡፡ ሠለስቱ ምዕት ‹‹ቢቻላችሁ ከዚህ አብዝታችሁ ጹሙ›› እንደዚሁም ‹‹በጾም ምክንያት ጠብ ክርክር ቢኾን መጾም ይገባል፤ ከመብላት መጾም ይሻላልና፤›› በማለት ከተወሰነው ሰዓት በላይ አብልጦ መጾም እንደሚቻልና ከመብል ይልቅ ለጾም ማድላት እንደሚገባ ነግረውናል /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፲፭ ቍጥር ፭፻፹፬/፡፡

ሰው ይረባኛል ይጠቅመኛል ብሎ አብዝቶ ከመጾሙ የተነሣ መላእክትን፣ አባ እንጦንስና አባ መቃርስን እንደሚመስል ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያስተምራሉ፡፡ አምላካችን ‹‹እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል›› የሚል ቃል ኪዳን የሰጣቸው አባቶቻችን መምህራን የምንጾማቸውን አጽዋማት እና የምንጾምበትን የሰዓት ጊዜ ወስነውልናል፡፡ በቅዱሳን አባቶቻችን ላይ አድሮ ሥርዓቱን የሠራልን ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ምክንያቱም ካለ እርሱ ፈቃድ እጽፍ፣ እተረጕም ቢሉ አይቻልምና፡፡ ጌታችን በወንጌሉ ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ዅሉ ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፤ ትእዛዜን የሚያከብር እንጅ፤›› እንዳለ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ተመርተው አባቶች  የደነገጉትን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ማክበር እና መጠበቅ አለብን፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹በየጥቂቱ ማደግ ይገባል›› እንዳለው ዅሉንም ነገር በአቅም ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ጾምን ስንጾምም አቅምን ማወቅም ተገቢ ነው፡፡ ብዙ ለመጾም ስንወስን ጽናታችንና ልምዳችንን ግምት ውስጥ በማስገባት መኾን ይኖርበታል፡፡ ካለበለዚያ ጥብዓት ጎድሎን፣ ትዕግሥት አንሶን እግዚአብሔርን ልናማርር እንችላለን፡፡ ጾመን የማናውቅ ሰዎች በስሜት ተነሣሥተን በአንድ ጊዜ ቀኑን ሙሉ መጾም አለብን ማለት የለብንም፡፡ ክርስትና የስሜት ጉዞ አይደለምና፡፡ እስከ ሰባት ሰዓት ጹሞ የማያውቅ ክርስቲያን እስከ ዐሥራ ሦስት ሊጾም አይችልም፡፡ በስሜት የሚደረግ ማንኛውም ነገር ፍጻሜ አይኖረውምና ስንጾም አቅማችንን ማወቅ ተገቢ ነው፤ ለዚህ ደግሞ ከንስሐ አባት ጋር መመካከር ይጠቅማል፡፡

ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹እጅግም ድሀ አታድርገኝ፤ እጅግም ሀብት አትስጠኝ›› ይላል፡፡ እኛም ስንጾምም ስንለምንም በአቅማችን መኾን አለበት፡፡ ስለጾምና የሰዓት ገደብ ሲነገር ማስተዋል የሚገባን ቁም ነገር ከእኽል ውኃ ከመከልከል አኳያ ጾም በቍጥርና በጊዜ የተወሰነ ይኹን እንጂ ከክፉ ተግባር ከመራቅ አንጻር ክርስቲያን እስኪሞት ድረስ ጾመኛ ነው፡፡ ምንጊዜም ቢኾን ከክፉ ነገር፣ ከኀጢአት ዅሉ መጾም (መከልከል) ይጠበቅበታልና፡፡ ዅላችንም ይህን ክርስቲያናዊ ሓላፊነት መዘንጋት የለብንም፡፡ ከዚህ ላይ ግን አንድ ሰው በመጾሙ ብቻ አምላክን ያስደስተዋል ማለት አይደለም፡፡ መጾም ያለበትም ለሥራው ኀጢአት ማካካሻ አይደለም፡፡ የኀጢአት ስርየት የሚገኘው ንስሐ በመግባት እንጅ በመጾም ብቻ አይደለምና፡፡ ሌሎችንም የትሩፋት ምግባራት መሥራት ስንችል ነው ኀጢአታችን የሚሰርይልን፡፡ ስለዚህ ራሳችንን ዝቅ በማድረግ፣ ንስሐ በመግባት፣ በመጸለይ፣ በመመጽወት ከጾምን ኀጢአታችን ይሰረይልናል ማለት ነው ‹‹በጾም ወበጸሎት ይሰረይ ኵሉ ኃጢአት፤ በጾም በጸሎት ኀጢአት ዅሉ ይደመሰሳል፤›› እንዲሉ ሊቃውንት

#join or #share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
👍1