የእግዚአብሔር ጸጋ
የእግዚአብሔር ጸጋ ማንንም ሳያስቀር ሰዎችን ሁሉ ስለሚጎበኝ ኃጢአተኞች እንኳ ከዚህ የእግዚአብሔር ጸጋ ጉብኝት ተቋዳሾች ናቸው። ስለ ጌታችን እንዲህ ተብሎ ትጽፏል “እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስ የተገዙትንም እየፈወሰ ዞረ” ሐዋ. 10፥38። እርሱ የጠፉት ነፍሳት ባለመታመናቸው በልበ ደንዳናነት ከእርሱ ርቀው ቢጠፉም እርሱ ግን መፈለጉን አላቋረጠም። የነበሩበት እጅግ ተስፋ የሚያስቆርጥ ቢሆንም እንኳ መልሶ እስከሚያመጣቸው ድረስ ፍለጋው አልተቋረጠም።
ሰዎች ስለ ድኅነታቸው ተስፋ የሚቆርጡ ቢሆኑም እንኳ እግዚአብሔር ግን በሰዎች ላይ ተስፋ ማሳደሩን አያቋርጥም። እግዚአብሔር በመንፈሳቸው የደከሙትን ቀርቶ ሞቶ ሥጋው በመሽተት ላይ ያለውን ሰው እንኳ ሳያስቀር ለሁሉም ሁሉ ጊዜ በጎ ነገርን ይሰራል። (ዮሐ. 11፥39) ከዚህ በተጨማሪ እርሱ በሕይወቱ የመጨረሻ ህቅታ ለነበረው ወንበዴ፣ ለቀረጥ ሰብሳቢው ዘኪዎስና አምስት ባሎች ለነበርዋት ሳምራዊት ሴት ይሰራ ነበር። (ሉቃስ. 23፥43፣ ሉቃስ. 19፥9፣ ዮሐ. 4፥18)። እርሱ ያቺ ጠፍታ የነበረችው ሳምራዊት ሴት ወደ ንስሐ ሊመራት ያለችበት ድረስ ሄዶ ፈልጓታል።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የእግዚእብሔርን ፍቅር በማስመልከት “እግዚአብሔር ለድኅነታችን ምክንያት ይሆን ዘንድ አንዲት ዘለላ እንባ እንኳ ትበቃዋለች። ይህች ዘለላ እንባ የከንቱ ደስታ ባለቤት በሆነው በዲያብሎስ ከመነጠቅዋ በፊት ለእኛ ለድኅነታችን ምክንያት እንድትሆን እግዚአብሔር ይቀበላታል” ብሎ ነበር።
በእርግጥ ከእኛ ልቦናዎች ይበልጥ እጅግ ርኅሩኅ ከሆነው ከአምላካችን ልብ የሚበልጥ የለም። ይህንን በማስመልከትም አምላካችን እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል “ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደ ሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ” (ሮሜ. 10፥21፣ ኢሳ. 65፥2)።
አምላካችን እግዚአብሔር ኃጢአት እንጂ ኃጥእ አይጸየፍምና ያለ አድልዎ ለሁሉም በእኩል ዓይን ይጎበኘዋል።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
የእግዚአብሔር ጸጋ ማንንም ሳያስቀር ሰዎችን ሁሉ ስለሚጎበኝ ኃጢአተኞች እንኳ ከዚህ የእግዚአብሔር ጸጋ ጉብኝት ተቋዳሾች ናቸው። ስለ ጌታችን እንዲህ ተብሎ ትጽፏል “እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስ የተገዙትንም እየፈወሰ ዞረ” ሐዋ. 10፥38። እርሱ የጠፉት ነፍሳት ባለመታመናቸው በልበ ደንዳናነት ከእርሱ ርቀው ቢጠፉም እርሱ ግን መፈለጉን አላቋረጠም። የነበሩበት እጅግ ተስፋ የሚያስቆርጥ ቢሆንም እንኳ መልሶ እስከሚያመጣቸው ድረስ ፍለጋው አልተቋረጠም።
ሰዎች ስለ ድኅነታቸው ተስፋ የሚቆርጡ ቢሆኑም እንኳ እግዚአብሔር ግን በሰዎች ላይ ተስፋ ማሳደሩን አያቋርጥም። እግዚአብሔር በመንፈሳቸው የደከሙትን ቀርቶ ሞቶ ሥጋው በመሽተት ላይ ያለውን ሰው እንኳ ሳያስቀር ለሁሉም ሁሉ ጊዜ በጎ ነገርን ይሰራል። (ዮሐ. 11፥39) ከዚህ በተጨማሪ እርሱ በሕይወቱ የመጨረሻ ህቅታ ለነበረው ወንበዴ፣ ለቀረጥ ሰብሳቢው ዘኪዎስና አምስት ባሎች ለነበርዋት ሳምራዊት ሴት ይሰራ ነበር። (ሉቃስ. 23፥43፣ ሉቃስ. 19፥9፣ ዮሐ. 4፥18)። እርሱ ያቺ ጠፍታ የነበረችው ሳምራዊት ሴት ወደ ንስሐ ሊመራት ያለችበት ድረስ ሄዶ ፈልጓታል።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የእግዚእብሔርን ፍቅር በማስመልከት “እግዚአብሔር ለድኅነታችን ምክንያት ይሆን ዘንድ አንዲት ዘለላ እንባ እንኳ ትበቃዋለች። ይህች ዘለላ እንባ የከንቱ ደስታ ባለቤት በሆነው በዲያብሎስ ከመነጠቅዋ በፊት ለእኛ ለድኅነታችን ምክንያት እንድትሆን እግዚአብሔር ይቀበላታል” ብሎ ነበር።
በእርግጥ ከእኛ ልቦናዎች ይበልጥ እጅግ ርኅሩኅ ከሆነው ከአምላካችን ልብ የሚበልጥ የለም። ይህንን በማስመልከትም አምላካችን እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል “ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደ ሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ” (ሮሜ. 10፥21፣ ኢሳ. 65፥2)።
አምላካችን እግዚአብሔር ኃጢአት እንጂ ኃጥእ አይጸየፍምና ያለ አድልዎ ለሁሉም በእኩል ዓይን ይጎበኘዋል።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
✝ኑሮየን ንገረኝ✝
ታላቁ ቅዱስ አርሳንዮስ ቤተ መንግሥትን ለቆ ወደ በረሃ ለምናኔ ሲገባ ጌታን የለመነበት ትልቅ ጸሎት ነበር። ጌታሆይ አለው። ጌታም አርሳኒ ምን ትሻለህ አለው። ቅዱስ አርሳንዮስም ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ ሲል ጠየቀ። ዳግመኛም ጌታ ሆይ ሲል ጮኸ። ጌታም አርሳኒ ምን ትሻለህ አለው። እርሱም ጌታይ ሆይ ኑሮዬን ንገረኝ አለው። ሦስተኛም አለ ጌታ ሆይ? አርሳኒ ምን ትሻለህ? ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ? ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦
ጌታም መለሰ።
፩. ቦታ ምረጥ
፪.ከሰው ተለይ
፫.ዝም በል
ይህን ነግሮ ሲፈጽም ቃሉ ዝም አለ። አርሳኒም ገዳም ገብቶ ለፍጹምነት በቃ።
ሰው መንገድ ሲሄድ በሁለት መንገድ ሊወድቅ ይችላል።አንደኛ በጠማማ መንገድ በመሄድ። ሁለተኛ በቅን መንገድ ሳያስተውሉ በመሄድ ነው። በጠማማ መንገድ በመሄድ መውደቅ ማለት በጠማማ ሃይማኖት መኖር ነው ። በቅን መንገድ ሳያስተውሉ መጓዝ ማለት ደግሞ በቀናች ሃይማኖት እየኖሩ አካሄድን አለማወቅ ነው። መንገዱ የቀና ቢሆንም አረማመዱ ባለማየት ከሆነ እግሮቹ ተጣልፈውም ቢሆን ይወድቃል። አካሄዱ ካላማረ በክርስቶስ ማመንም ያስኮንናል።የምናውቀው ክርስትና በማናውቀው መንገድ ከኖርነው ያጠፋል።
አውቀን ለምናደርጋቸው እንኳ ቢሆን እንዴት ላድርገው እያልን መጠየቅ በየዕለቱ እናደርገው ዘንድ ይገባል። በየጊዜውና በየሰዓቱ ወደ ክርስቶስ የምንጓዝ ነንና ጥያቄያችን የዘወትር ነው። ጸሎት አይቋረጥም መባሉ ስለዚህ ነው።ቅዱስ አርሳንዮስ ኑሮው ምንኩስና እንዲሆን ወስኖ ነበር። ግን መነኩሴ መሆን እንዳለበት እያወቀ ኑሮየን ንገረኝ ይል ነበር። ለምን ቢሉ ኑሮውን ብናውቀውም አኗኗሩን ግን ካልጠየቅን የሚጠቅመውን በማይጠቅም መንገድ ልንኖረው እንችላለን።፡
ለምሳሌ ከቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስ ጳውሎስን እንይ። ቅዲስ ጳውሎስ ምሑረ ኦሪት ነበር። ፵፮ቱን የኦሪት መጻሕፍት ተምሯል። መጻሕፍቱ ግን የሚተረጎሙት በክርስቶስ መገለጥ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ግን ጌታን ያሳድድ ነበር። የሚያሳደደውም ለሕግ የተቆረቆርሁ መስሎት ነበር። ጌታም ቅንነቱን አይቷልና ጌታን እያገለገለ መስሎት ጌታን ያሳድድ የነበረውን አልተወውም። መንገዱን ያቀናለት ዘንድ መንገገድ ላይ በመብረቅ ተገለጠለት። ሊያሳድድበት የሄደውን መንገድ ወደ ክርስቶስ እንዲደርስበት መራው። እውቀትን ቅንነት ይመራዋል፤ ቅንነትን እውቀት ያበራዋል። ስለዚህ ስለምናደርገው ነገር በቂ እውቀት ቢኖረንም ያንን ግን እንደመርከብ የሚመራው ረድኤተ እግዚአብሔር ነውና አዘውትረን ኑሮየን ንገረኝ እንበል!
Join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
ታላቁ ቅዱስ አርሳንዮስ ቤተ መንግሥትን ለቆ ወደ በረሃ ለምናኔ ሲገባ ጌታን የለመነበት ትልቅ ጸሎት ነበር። ጌታሆይ አለው። ጌታም አርሳኒ ምን ትሻለህ አለው። ቅዱስ አርሳንዮስም ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ ሲል ጠየቀ። ዳግመኛም ጌታ ሆይ ሲል ጮኸ። ጌታም አርሳኒ ምን ትሻለህ አለው። እርሱም ጌታይ ሆይ ኑሮዬን ንገረኝ አለው። ሦስተኛም አለ ጌታ ሆይ? አርሳኒ ምን ትሻለህ? ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ? ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦
ጌታም መለሰ።
፩. ቦታ ምረጥ
፪.ከሰው ተለይ
፫.ዝም በል
ይህን ነግሮ ሲፈጽም ቃሉ ዝም አለ። አርሳኒም ገዳም ገብቶ ለፍጹምነት በቃ።
ሰው መንገድ ሲሄድ በሁለት መንገድ ሊወድቅ ይችላል።አንደኛ በጠማማ መንገድ በመሄድ። ሁለተኛ በቅን መንገድ ሳያስተውሉ በመሄድ ነው። በጠማማ መንገድ በመሄድ መውደቅ ማለት በጠማማ ሃይማኖት መኖር ነው ። በቅን መንገድ ሳያስተውሉ መጓዝ ማለት ደግሞ በቀናች ሃይማኖት እየኖሩ አካሄድን አለማወቅ ነው። መንገዱ የቀና ቢሆንም አረማመዱ ባለማየት ከሆነ እግሮቹ ተጣልፈውም ቢሆን ይወድቃል። አካሄዱ ካላማረ በክርስቶስ ማመንም ያስኮንናል።የምናውቀው ክርስትና በማናውቀው መንገድ ከኖርነው ያጠፋል።
አውቀን ለምናደርጋቸው እንኳ ቢሆን እንዴት ላድርገው እያልን መጠየቅ በየዕለቱ እናደርገው ዘንድ ይገባል። በየጊዜውና በየሰዓቱ ወደ ክርስቶስ የምንጓዝ ነንና ጥያቄያችን የዘወትር ነው። ጸሎት አይቋረጥም መባሉ ስለዚህ ነው።ቅዱስ አርሳንዮስ ኑሮው ምንኩስና እንዲሆን ወስኖ ነበር። ግን መነኩሴ መሆን እንዳለበት እያወቀ ኑሮየን ንገረኝ ይል ነበር። ለምን ቢሉ ኑሮውን ብናውቀውም አኗኗሩን ግን ካልጠየቅን የሚጠቅመውን በማይጠቅም መንገድ ልንኖረው እንችላለን።፡
ለምሳሌ ከቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስ ጳውሎስን እንይ። ቅዲስ ጳውሎስ ምሑረ ኦሪት ነበር። ፵፮ቱን የኦሪት መጻሕፍት ተምሯል። መጻሕፍቱ ግን የሚተረጎሙት በክርስቶስ መገለጥ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ግን ጌታን ያሳድድ ነበር። የሚያሳደደውም ለሕግ የተቆረቆርሁ መስሎት ነበር። ጌታም ቅንነቱን አይቷልና ጌታን እያገለገለ መስሎት ጌታን ያሳድድ የነበረውን አልተወውም። መንገዱን ያቀናለት ዘንድ መንገገድ ላይ በመብረቅ ተገለጠለት። ሊያሳድድበት የሄደውን መንገድ ወደ ክርስቶስ እንዲደርስበት መራው። እውቀትን ቅንነት ይመራዋል፤ ቅንነትን እውቀት ያበራዋል። ስለዚህ ስለምናደርገው ነገር በቂ እውቀት ቢኖረንም ያንን ግን እንደመርከብ የሚመራው ረድኤተ እግዚአብሔር ነውና አዘውትረን ኑሮየን ንገረኝ እንበል!
Join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።
ብጽዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
ብጽዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
ጻዲቁ ዮሴፍ እጅግ ከባድ የሆነ ውጪያዊ ውጊያ ከጲጥፋራ ሚስት ቢገጥመውም አልወደቀም። እርሱ ኃጢአትን በልቡ ውስጥ ስላልተቀበለው ፈተናውንም አልተቀበለውም። ስለሆነም ጥቃቱን ሊቋቋም ችሏል። ዲያብሎስ አሳቦችን ያቀርብልሃል እንጅ ተቀብለህ ተግባራዊ እንድታደርጋቸው አያስገድድህም።
ብጽዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
ብጽዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
join or share
@linkortodoxe21
👳ይፍቱኝ👳
አንድ በእድሜ ጠና ያሉ ካህን የከተማ አውቶብስ ውስጥ ናቸው አውቶብሱ ሞልቷል እንኳንስ መቀመጫ የእግር መቆሚያ ቦታ የለውም መቼስ መሳፈሩ ግድ ነውና ሰው በሰው ላይ ተዛዝሎ በሩም በግድ ተዘግቶ ጉዞው ቀጥሏል ካህኑ መቀመጫ በማጣታቸው የአውቶብሱን ብረት ይዘው ከወዲያ ወዲህ እየተወዛወዙ ሳለ አንድ የኪስ ቀበኛ በኪሳቸው እጁን ጥልቅ ሲያረግ ካህኑም የሌባውን እጅ ከኪሳቸው ጋር ጨምድደው ይይዙታል ይሄኔ ሌባው ኮስተር ብሎ ከካህን መስቀል እንደሚሳለም ምእመን ራሱን ወደ ምድር ዝቅ አድርጎ "ይፍቱኝ" ይላል የሌባው ድፍረትና ዓይን አውጣነት የገረማቸው ካህንም "ወቸው ጉድ እንኳን ተፈተህ ታስረህስ መች ተቻልክ" አሉት ይባላል "
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
የንስሐ መጀመርያው እየሠሩ ካለው ኃጥያት መለየት ነው ማቴ ፳፮ ፣ ፸፭
ሰው ከእግዚአብሔር ምህረት መጠየቅ ያለበት የበደለውን ክሶ የቀማውን መልሶ ሊሆን ይገባል
join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
አንድ በእድሜ ጠና ያሉ ካህን የከተማ አውቶብስ ውስጥ ናቸው አውቶብሱ ሞልቷል እንኳንስ መቀመጫ የእግር መቆሚያ ቦታ የለውም መቼስ መሳፈሩ ግድ ነውና ሰው በሰው ላይ ተዛዝሎ በሩም በግድ ተዘግቶ ጉዞው ቀጥሏል ካህኑ መቀመጫ በማጣታቸው የአውቶብሱን ብረት ይዘው ከወዲያ ወዲህ እየተወዛወዙ ሳለ አንድ የኪስ ቀበኛ በኪሳቸው እጁን ጥልቅ ሲያረግ ካህኑም የሌባውን እጅ ከኪሳቸው ጋር ጨምድደው ይይዙታል ይሄኔ ሌባው ኮስተር ብሎ ከካህን መስቀል እንደሚሳለም ምእመን ራሱን ወደ ምድር ዝቅ አድርጎ "ይፍቱኝ" ይላል የሌባው ድፍረትና ዓይን አውጣነት የገረማቸው ካህንም "ወቸው ጉድ እንኳን ተፈተህ ታስረህስ መች ተቻልክ" አሉት ይባላል "
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
የንስሐ መጀመርያው እየሠሩ ካለው ኃጥያት መለየት ነው ማቴ ፳፮ ፣ ፸፭
ሰው ከእግዚአብሔር ምህረት መጠየቅ ያለበት የበደለውን ክሶ የቀማውን መልሶ ሊሆን ይገባል
join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
=> #የምኒልክ_አዋጅ
________________
" እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፣ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ። እንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉ ነውና ስለኔ ሞት አላዝንም።
ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም ። አሁንም አገር የሚያጠፋ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባሕር አልፎ መጥቷል። እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፍል መሬት ይቆፍር ጀመር ።
አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም። ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም ጉልበት ያለህ
በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበትም የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በኀዘንህ እርዳኝ ። ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም #ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም። ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ "
ይህን አዋጅ ሰምቶ ህዝብ ከጫፍ እስከ ጫፍ ንጉሡን ተከትሎ ህይወቱን ሰጥቶ ሀገሩን እና ክብሩን ታደገ።
Join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
________________
" እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፣ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ። እንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉ ነውና ስለኔ ሞት አላዝንም።
ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም ። አሁንም አገር የሚያጠፋ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባሕር አልፎ መጥቷል። እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፍል መሬት ይቆፍር ጀመር ።
አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም። ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም ጉልበት ያለህ
በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበትም የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በኀዘንህ እርዳኝ ። ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም #ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም። ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ "
ይህን አዋጅ ሰምቶ ህዝብ ከጫፍ እስከ ጫፍ ንጉሡን ተከትሎ ህይወቱን ሰጥቶ ሀገሩን እና ክብሩን ታደገ።
Join or share
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
❤️ተዋህዶ ነሽ ውብ እምነት
ተዋሕዶ ነሽ ውብ እምነት❤️
🎙መምህር ምህረተአብ አሰፋ
join or share
💚@linkortodoxe21💚
💛@linkortodoxe21💛
❤️@linkortodoxe21❤️
ተዋሕዶ ነሽ ውብ እምነት❤️
🎙መምህር ምህረተአብ አሰፋ
join or share
💚@linkortodoxe21💚
💛@linkortodoxe21💛
❤️@linkortodoxe21❤️