"ኑ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ"
(ብፁእ አቡነ ሺኖዳ)
ኑ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ኑ በፀሎት ወደአምላክ ቅረቡ ፤ በፀሎት ማለት እንዴት ነው? ይህስ የልባችሁን ምስጢር ሁሉ ሳትደብቁ እርሱ እግዚአብሄር እንደሚያስፈልጋችሁ መናገር ማለት ነው ፤ እንዲህም በሉ ፦ “ጌታ ሆይ ወደ አንተ መምጣት እፈልጋለሁ ፡ ጌታ ሆይ ካንተ ተለይቼ እኔ ምንም ነኝ ፡ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴን አጣሁ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ደስታየን ሁሉ አጣሁ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴ ትርጉም አልባ ሆነ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴ ጣእም አልባ ሆነ” በሉ ፤ ዳግምም ከእግዚአብሄር እግር ስር ተደፍታችሁ እንዲህ በሉት፦ “ አምላኬ ሆይ ፦ ወደ አንተ መመለስ እፈልጋለሁ ፤ ነገር ግን ጠላቶቼ ከእኔ በእጅጉ የሚበልጡ ናቸው ፤ ነፍሴንም አምላክሽ አያድኑሽም የሚሏት ብዙ ናቸው” ፡፡
ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ “ ጌታ ሆይ ታደገኝ ወደ አንተ የምመለስበትን መንገድ ምራኝ” በሉት ፤ ለአምላካችሁ ንገሩት ፦ “ካንተ ከተለየሁ ወዲህ አቅሜ ሁሉ ተዳክሟልና ጌታ ሆይ ልዩ ሃይልህን ላክልኝ ፡ ወዳንተ የምመለስበትን ልዩ ርዳታህን ስጠኝ ፤” በማለት፡፡ ብዙ ሰወች በመደጋገም “ወደ እግዚአብሄር የምመለሰው እንዴት ነው ?” ይላሉ፡፡ ከእግዚአብሄር እግር በታች ራሳችሁን ጣሉ ፡ እንዲህም በሉት ፦ “ ጌታ ሆይ ሳትባርከኝ አልለቅህም ፡ ወዳንተ አቅርበኝ ፡ ከልጆችህ እንደአንዱ አድርገኝ ፡ ሃጢአቴን ብቻ ይቅር እንድትልልኝ አልሻም ፡ ይልቁንም ከሃጢአት ፍቅር ትለየኝ ዘንድ ጭምር እንጂ ፡”በሉት ፦ ዳግምም “ ጌታ ሆይ የሃጢአት ፍቅር ልቤን ተቆጣጥሮታልና ይህን ካላስወገድኩ ወዳንተ መቅረብ አይቻለኝም ፡ ጌታ ሆይ የሃጢአትን ፍቅር ከልቤ ላይ ንቀል ፡” በሉት ዳግምም እንዲህ በሉት ፦ ”ጌታ ሆይ ከሃጢአቴ ነፅቼ ወዳንተ መምጣት እንደምን ይቻለኛል? ይልቁንስ መጀመሪያ አንተ ናልኝ ሃጢአቴንም ደምስስ እንጂ “ እንዲህም በሉት ፦ “ በራሴማ ሃጢአትን ማስወገድ ብችል ወዳንተ መቼ መመለስ ያቅተኝ ነበር? እኔ ግን አንተ ከሃጢአቴ እንድታርቀኝ እወዳለሁ ፡ ጌታ ሆይ ፦ ሃይልህን እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ” በሉት፡፡
እመኑኝ የምወዳችሁ ልጆቼ ፦ ትክክለኛዋን ፀሎት ያወቃት እርሱ ትክክለኛዋንም ንስሃን የሚያውቅ እርሱ ነው ፤ ማር ይስሃቅ እንደተናገረው ፦ “ንስሃ ከፀሎት ውጭ እንደሚገኝ የሚያስብ ሰው እርሱ በዲያቢሎስ የተታለለ ነው” ምክንያቱም በፀሎት ወደ እግዚአብሄር የምትመለሱበትን ሃይልን ታገኛላችሁና፡፡ ስለሆነም ከየትኛውም ስራ ይልቅ ራሳችሁን ለፀሎት አስገድዱ ፤ ምክንያቱም በፀሎት አማካኝነት በእናንተና በእግዚአብሄር መካከል ያለውን ግድግዳ አስወግዳችሁ እንደገና ወደእርሱ ትመለሱ ዘንድ ይቻላችኅልና ፤ በጣም ብዙ ሰወች ከፀሎት ይልቅ ለአገልግሎት መትጋታቸው የሚገርም ነው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በንባብ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በተመስጦ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በመንፈሳዊ ስብሰባወች ለመታደም የሚተጉትም እንደዚያው ፤ ለዚህ እኮ ነው ከእግዚአብሄር ጋር ባላቸው ግንኙነት የማይሳካላቸው ፤ ይፀልያሉ ያነባሉ ደግሞም ስብሰባወችን ይታደማሉ በዚህ ሁሉ ሰአት ከእግዚአብሄር ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም ፤ ምንም አይነት ግንኙነት ፡፡
ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ወደእግዚአብሄር ተመለሱና ከእርሱ ውሰዱ ፤ አንዳንድ ሰወች በመፀለይ ለእግዚአብሄር የሚሰጡት እንዳለ ያስባሉ ፡ ለእግዚአብሄር ቃላትን ይሰጡታል ፡ ጊዜን ፡ ምናልባትም ስሜታቸውን ፤ ነገር ግን ጥልቅ የሆነ ፀሎት ከእግዚአብሄር የመውሰድ ጉዳይ ነው ፤ እርሱ ሰጭ እንጂ ተቀባይ አይደለምና ፤ በፀሎቱ ስኬታማ ውጤትን የሚያመጣ ሰው እርሱ ከእግዚአብሄር ስለሚወስደው የፀለየና እንደዚያም የሚያምን ነው ፤ እርሱ ነው በፀሎቱ የተሳካለት፡፡ በምትፀልዩበት ጊዜ ከእግዚአብሄር ሃይልን እንደተቀበላችሁ ከተሰማችሁ ፡ ያን ጊዜ ውጤታማ ፀሎት ፀለያችሁ ፤ አንድ ሰው ፀልዮ ከእግዚአብሄር በረከት ከተቀበለ፡ እንግዲህ ይህ ሰው ነው ውጤታማ ፀሎት ያቀረበው ፤ ማንም በፀሎት በፀፀትና በንስሃ ወደእግዚአብሄር ቢቀርብ እርሱ ውጤታማ ፀሎትን አቀረበ ፤ አንድ ሰው ቢፀልይና ለቅድስና ቢታገል ፡ ይህ ሰው ፀሎቱ ውጤታማ ሆነ ፤ አንድ ሰው ቢፀልይና ከእግዚአብሄር ጋር ያለውን ግንኙነት ቢያጠናክር ይሄኔ ውጤታማ ፀሎትን አቀረበ፡፡
እግዚአብሄር እንድትመጡ ይናገራችኅል ፡ በፀሎት ኑ ና የሚያስፈልጋችሁን ልስጣችሁ እያለ ፤ ነገር ግን እናንተ ለሁለት ደቂቃ ብቻ ትፅልዩና ወዲያው ትሰለቻላችሁ ፡ ከእግዚአብሄርም አንዳች ሳትቀበሉ ትሄዳላችሁ ፤ እግዚአብሄር ወደእናንተ ያይና እንዲህ ይላል ፦ “ስለምን ከእኔ ሳትቀበሉ ተመለሳችሁ? የሚያስፈልጋችሁን ልሰጣችሁ ወድጄ ነበርና ፤ ስለምን ቶሎ ተመለሳችሁ ያዘጋጀሁላችሁን ሳትወስዱ?” እያለ ፤ ነገር ግን እናንተ ቶሎ ሰለቻችሁና ለመሄድ ወሰናችሁ ፤ እሺ ሂዱ ፡ ከዚያ ግን እግዚአብሄርን መፈለግ ትጀምራላችሁ አታገኙትም ፤ ጥላችሁ ስትሄዱ ያጣችሁት ምንም ሳትይዙ መሄዳችሁን ብቻ እንዳይመስላችሁ በልባችሁ ለእግዚአብሄር ጊዜ እንደሰጣችሁት ማሰባችሁም ጭምር እንጂ ፤ ወዲያውም ከመንፈሳዊ የስኬት ድርጊቶች ውስጥ መፀለያችሁን ትፅፋላችሁ፡፡
ይህ ግን ፀሎት አይደለም!!! ከእግዚአብሄር ከቶ ምን አገኛችሁ? እግዚአብሄርን አጥብቃችሁ ልትይዙት ይገባል አጥብቃችሁ መቼም ቢሆን ካንተ አልለይም መለየትም አልፈልግም ማለት አለባችሁ፡፡ ስለዚህ እኮ ነው ለፀሎት ትእግስት የሚያስፈልገው፤ ያለትእግስት ከእግዚአብሄር አንዳች እንኳን ልትቀበሉ አትችሉም፤ በፀሎታችሁ ትእግስተኞች ልትሆኑ ይገባችኅል፤ እግዚአብሄርን ንገሩት፦ ከእግርህ በታች እንደሆንኩ እቆያለሁ በረከትህንም ሳትሰጠኝ አልነቃነቅም ከእግዚአብሄር በረከትን ካልተቀበልኩ እርሱን መያዜን አልለቅም ካልባረከኝ አልለቅህም እይዘዋለሁ ወዴትም ይሄድ ዘንድ አልተወውም፤ እንግዲህ ይህ ነው በፀሎት ውስጥ ያለው ትግል፤ ሰወች ፀሎት እንዴት እንደሚፀለይ አልተማሩም እነርሱ የሚያስቡት ፀሎት ማለት ጥቂት ቃላትን መናገር ይመስላቸዋል አይደለም፡፡
ፀሎትን አዘውትሩ፡- ከእግዚአብሄርም አንዳች እስክትቀበሉ ድረስ ታገሉ ፤ አንዳች እንኳን ካልወሰዳችሁ ሳትቀበሉ የትም እንደማትሄዱ ንገሩት ፀሎቴን አልገታም በሉት እንደተፃፈ አንተ ሩህሩህ መሃሪ አምላክ ነህ የለመነውን ሁሉ የምትሰጥ ነህና እንግዲህ እኔም ለምኜሃለሁ እስከምትሰጠኝ ድረስ ወዴትም አልሄድም በሉት፤ በፀሎታችሁ ከእግዚአብሄር ጋር ታገሉ ያን ጊዜ ታርፋላችሁ በፍቅር ትሞላላችሁ በፀሎታችሁም ብርቱ ትሆናላችሁ ከንቱ ነገርንም መደጋገም ትተዋላችሁ እንዲያውም ልባችሁን በእግዚአብሄር ፊት ትዘረጋላችሁ፤ የሳሙኤል እናት ሃና በፀሎቷ ጊዜ ታለቅስ ነበር በልቧም ልጅ እንደምታገኝ ቃል ሳይገባላት ከቤተመቅደሱ ላለመውጣት ወስና ነበር ፤ ንጉስ ዳዊት ከእግዚአብሄር በረከትን እስኪቀበል ድረስ ፀሎቱን አላቋረጠም በመጀመሪያ “ጌታ ሆይ ፦ አስጨናቂወቼ ምንኛ በዙ” በማለት ፀለየ፤ ቀጥሎም እንዲህ አለ ፦ “ እናንተ ክፉ አድራጊወች ከእኔ ራቁ እግዚአብሄር ፀሎቴን ሰምቶልኛልና ፡ ጌታየ የልመናየን ድምፅ አድምጧልና ጌታየ ፀሎቴን ሰምቷልና“፡፡ ኑ ወደእግዚአብሄር ተመለሱ፡፡
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
(ብፁእ አቡነ ሺኖዳ)
ኑ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ኑ በፀሎት ወደአምላክ ቅረቡ ፤ በፀሎት ማለት እንዴት ነው? ይህስ የልባችሁን ምስጢር ሁሉ ሳትደብቁ እርሱ እግዚአብሄር እንደሚያስፈልጋችሁ መናገር ማለት ነው ፤ እንዲህም በሉ ፦ “ጌታ ሆይ ወደ አንተ መምጣት እፈልጋለሁ ፡ ጌታ ሆይ ካንተ ተለይቼ እኔ ምንም ነኝ ፡ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴን አጣሁ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ደስታየን ሁሉ አጣሁ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴ ትርጉም አልባ ሆነ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴ ጣእም አልባ ሆነ” በሉ ፤ ዳግምም ከእግዚአብሄር እግር ስር ተደፍታችሁ እንዲህ በሉት፦ “ አምላኬ ሆይ ፦ ወደ አንተ መመለስ እፈልጋለሁ ፤ ነገር ግን ጠላቶቼ ከእኔ በእጅጉ የሚበልጡ ናቸው ፤ ነፍሴንም አምላክሽ አያድኑሽም የሚሏት ብዙ ናቸው” ፡፡
ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ “ ጌታ ሆይ ታደገኝ ወደ አንተ የምመለስበትን መንገድ ምራኝ” በሉት ፤ ለአምላካችሁ ንገሩት ፦ “ካንተ ከተለየሁ ወዲህ አቅሜ ሁሉ ተዳክሟልና ጌታ ሆይ ልዩ ሃይልህን ላክልኝ ፡ ወዳንተ የምመለስበትን ልዩ ርዳታህን ስጠኝ ፤” በማለት፡፡ ብዙ ሰወች በመደጋገም “ወደ እግዚአብሄር የምመለሰው እንዴት ነው ?” ይላሉ፡፡ ከእግዚአብሄር እግር በታች ራሳችሁን ጣሉ ፡ እንዲህም በሉት ፦ “ ጌታ ሆይ ሳትባርከኝ አልለቅህም ፡ ወዳንተ አቅርበኝ ፡ ከልጆችህ እንደአንዱ አድርገኝ ፡ ሃጢአቴን ብቻ ይቅር እንድትልልኝ አልሻም ፡ ይልቁንም ከሃጢአት ፍቅር ትለየኝ ዘንድ ጭምር እንጂ ፡”በሉት ፦ ዳግምም “ ጌታ ሆይ የሃጢአት ፍቅር ልቤን ተቆጣጥሮታልና ይህን ካላስወገድኩ ወዳንተ መቅረብ አይቻለኝም ፡ ጌታ ሆይ የሃጢአትን ፍቅር ከልቤ ላይ ንቀል ፡” በሉት ዳግምም እንዲህ በሉት ፦ ”ጌታ ሆይ ከሃጢአቴ ነፅቼ ወዳንተ መምጣት እንደምን ይቻለኛል? ይልቁንስ መጀመሪያ አንተ ናልኝ ሃጢአቴንም ደምስስ እንጂ “ እንዲህም በሉት ፦ “ በራሴማ ሃጢአትን ማስወገድ ብችል ወዳንተ መቼ መመለስ ያቅተኝ ነበር? እኔ ግን አንተ ከሃጢአቴ እንድታርቀኝ እወዳለሁ ፡ ጌታ ሆይ ፦ ሃይልህን እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ” በሉት፡፡
እመኑኝ የምወዳችሁ ልጆቼ ፦ ትክክለኛዋን ፀሎት ያወቃት እርሱ ትክክለኛዋንም ንስሃን የሚያውቅ እርሱ ነው ፤ ማር ይስሃቅ እንደተናገረው ፦ “ንስሃ ከፀሎት ውጭ እንደሚገኝ የሚያስብ ሰው እርሱ በዲያቢሎስ የተታለለ ነው” ምክንያቱም በፀሎት ወደ እግዚአብሄር የምትመለሱበትን ሃይልን ታገኛላችሁና፡፡ ስለሆነም ከየትኛውም ስራ ይልቅ ራሳችሁን ለፀሎት አስገድዱ ፤ ምክንያቱም በፀሎት አማካኝነት በእናንተና በእግዚአብሄር መካከል ያለውን ግድግዳ አስወግዳችሁ እንደገና ወደእርሱ ትመለሱ ዘንድ ይቻላችኅልና ፤ በጣም ብዙ ሰወች ከፀሎት ይልቅ ለአገልግሎት መትጋታቸው የሚገርም ነው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በንባብ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በተመስጦ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በመንፈሳዊ ስብሰባወች ለመታደም የሚተጉትም እንደዚያው ፤ ለዚህ እኮ ነው ከእግዚአብሄር ጋር ባላቸው ግንኙነት የማይሳካላቸው ፤ ይፀልያሉ ያነባሉ ደግሞም ስብሰባወችን ይታደማሉ በዚህ ሁሉ ሰአት ከእግዚአብሄር ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም ፤ ምንም አይነት ግንኙነት ፡፡
ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ወደእግዚአብሄር ተመለሱና ከእርሱ ውሰዱ ፤ አንዳንድ ሰወች በመፀለይ ለእግዚአብሄር የሚሰጡት እንዳለ ያስባሉ ፡ ለእግዚአብሄር ቃላትን ይሰጡታል ፡ ጊዜን ፡ ምናልባትም ስሜታቸውን ፤ ነገር ግን ጥልቅ የሆነ ፀሎት ከእግዚአብሄር የመውሰድ ጉዳይ ነው ፤ እርሱ ሰጭ እንጂ ተቀባይ አይደለምና ፤ በፀሎቱ ስኬታማ ውጤትን የሚያመጣ ሰው እርሱ ከእግዚአብሄር ስለሚወስደው የፀለየና እንደዚያም የሚያምን ነው ፤ እርሱ ነው በፀሎቱ የተሳካለት፡፡ በምትፀልዩበት ጊዜ ከእግዚአብሄር ሃይልን እንደተቀበላችሁ ከተሰማችሁ ፡ ያን ጊዜ ውጤታማ ፀሎት ፀለያችሁ ፤ አንድ ሰው ፀልዮ ከእግዚአብሄር በረከት ከተቀበለ፡ እንግዲህ ይህ ሰው ነው ውጤታማ ፀሎት ያቀረበው ፤ ማንም በፀሎት በፀፀትና በንስሃ ወደእግዚአብሄር ቢቀርብ እርሱ ውጤታማ ፀሎትን አቀረበ ፤ አንድ ሰው ቢፀልይና ለቅድስና ቢታገል ፡ ይህ ሰው ፀሎቱ ውጤታማ ሆነ ፤ አንድ ሰው ቢፀልይና ከእግዚአብሄር ጋር ያለውን ግንኙነት ቢያጠናክር ይሄኔ ውጤታማ ፀሎትን አቀረበ፡፡
እግዚአብሄር እንድትመጡ ይናገራችኅል ፡ በፀሎት ኑ ና የሚያስፈልጋችሁን ልስጣችሁ እያለ ፤ ነገር ግን እናንተ ለሁለት ደቂቃ ብቻ ትፅልዩና ወዲያው ትሰለቻላችሁ ፡ ከእግዚአብሄርም አንዳች ሳትቀበሉ ትሄዳላችሁ ፤ እግዚአብሄር ወደእናንተ ያይና እንዲህ ይላል ፦ “ስለምን ከእኔ ሳትቀበሉ ተመለሳችሁ? የሚያስፈልጋችሁን ልሰጣችሁ ወድጄ ነበርና ፤ ስለምን ቶሎ ተመለሳችሁ ያዘጋጀሁላችሁን ሳትወስዱ?” እያለ ፤ ነገር ግን እናንተ ቶሎ ሰለቻችሁና ለመሄድ ወሰናችሁ ፤ እሺ ሂዱ ፡ ከዚያ ግን እግዚአብሄርን መፈለግ ትጀምራላችሁ አታገኙትም ፤ ጥላችሁ ስትሄዱ ያጣችሁት ምንም ሳትይዙ መሄዳችሁን ብቻ እንዳይመስላችሁ በልባችሁ ለእግዚአብሄር ጊዜ እንደሰጣችሁት ማሰባችሁም ጭምር እንጂ ፤ ወዲያውም ከመንፈሳዊ የስኬት ድርጊቶች ውስጥ መፀለያችሁን ትፅፋላችሁ፡፡
ይህ ግን ፀሎት አይደለም!!! ከእግዚአብሄር ከቶ ምን አገኛችሁ? እግዚአብሄርን አጥብቃችሁ ልትይዙት ይገባል አጥብቃችሁ መቼም ቢሆን ካንተ አልለይም መለየትም አልፈልግም ማለት አለባችሁ፡፡ ስለዚህ እኮ ነው ለፀሎት ትእግስት የሚያስፈልገው፤ ያለትእግስት ከእግዚአብሄር አንዳች እንኳን ልትቀበሉ አትችሉም፤ በፀሎታችሁ ትእግስተኞች ልትሆኑ ይገባችኅል፤ እግዚአብሄርን ንገሩት፦ ከእግርህ በታች እንደሆንኩ እቆያለሁ በረከትህንም ሳትሰጠኝ አልነቃነቅም ከእግዚአብሄር በረከትን ካልተቀበልኩ እርሱን መያዜን አልለቅም ካልባረከኝ አልለቅህም እይዘዋለሁ ወዴትም ይሄድ ዘንድ አልተወውም፤ እንግዲህ ይህ ነው በፀሎት ውስጥ ያለው ትግል፤ ሰወች ፀሎት እንዴት እንደሚፀለይ አልተማሩም እነርሱ የሚያስቡት ፀሎት ማለት ጥቂት ቃላትን መናገር ይመስላቸዋል አይደለም፡፡
ፀሎትን አዘውትሩ፡- ከእግዚአብሄርም አንዳች እስክትቀበሉ ድረስ ታገሉ ፤ አንዳች እንኳን ካልወሰዳችሁ ሳትቀበሉ የትም እንደማትሄዱ ንገሩት ፀሎቴን አልገታም በሉት እንደተፃፈ አንተ ሩህሩህ መሃሪ አምላክ ነህ የለመነውን ሁሉ የምትሰጥ ነህና እንግዲህ እኔም ለምኜሃለሁ እስከምትሰጠኝ ድረስ ወዴትም አልሄድም በሉት፤ በፀሎታችሁ ከእግዚአብሄር ጋር ታገሉ ያን ጊዜ ታርፋላችሁ በፍቅር ትሞላላችሁ በፀሎታችሁም ብርቱ ትሆናላችሁ ከንቱ ነገርንም መደጋገም ትተዋላችሁ እንዲያውም ልባችሁን በእግዚአብሄር ፊት ትዘረጋላችሁ፤ የሳሙኤል እናት ሃና በፀሎቷ ጊዜ ታለቅስ ነበር በልቧም ልጅ እንደምታገኝ ቃል ሳይገባላት ከቤተመቅደሱ ላለመውጣት ወስና ነበር ፤ ንጉስ ዳዊት ከእግዚአብሄር በረከትን እስኪቀበል ድረስ ፀሎቱን አላቋረጠም በመጀመሪያ “ጌታ ሆይ ፦ አስጨናቂወቼ ምንኛ በዙ” በማለት ፀለየ፤ ቀጥሎም እንዲህ አለ ፦ “ እናንተ ክፉ አድራጊወች ከእኔ ራቁ እግዚአብሄር ፀሎቴን ሰምቶልኛልና ፡ ጌታየ የልመናየን ድምፅ አድምጧልና ጌታየ ፀሎቴን ሰምቷልና“፡፡ ኑ ወደእግዚአብሄር ተመለሱ፡፡
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
🕯``ድንግልናን የምትፈልጉ ሴቶች በሙሉ የጌታችን እናት የኾነችውን የማርያምን ምሳሌ ተከተሉ``🕯
💡ጉባኤ፦ የድንግል ሕይወት💡
[ከ፫፻፸፮-፬፻፵፬ (376-444) ዓ.ም የነበረው እስክንድርያዊዉ
ቅዱስ ቄርሎስ]
“Come, O all ye women who desire
virginity…” (ድንግልናን የምትፈልጉ ሴቶች በሙሉ የጌታችን
እናት የኾነችውን የማርያምን ምሳሌ ተከተሉ፤ የርሷንም መንገድ
መናኛ ምግብ መብላቷንና መሬት ላይ መተኛቷን ዐስቡ፤ ለዚኽ
ዓለም ነገሮች ምንም ዐይነት ጉጉት የላትምና የርሷ ስምም
ኹልጊዜም በካህናት አፍ ውስጥ ነበር፤ ሰውነቷን በጭራሽ
በሕዝብ መታጠቢያ ውስጥ ታጥባ አታውቅም፤ ራሷን በፍጹም
በመዋቢያ የፊት ቀለም፣ በዐይን ኩልና በቅባት በጭራሽ አስውባ
አታውቅም፤ በጣም ያጌጠ ልብስ እንደሚወድዱ ኹሉም በዘመኗ
የነበሩ ሴቶች በደማቅ ባለቀለም ልብስ በጭራሽ አስጌጣ
አታውቅም፤ በጭራሽ የወይንን ጣዕም ቀምሳ አታውቅም፤
ኹልጊዜም ዓለማትን የፈጠረ ፈጣሪዋን ትጠብቅ ስለነበር ፊቷን
ወደ ምሥራቅ አዙራ ትቀመጥ ነበር፤ ከእናቷና ከአባቷ በስተቀር
ከማንም ጋር ተገናኝታና አውርታ አታውቅም
ነገረ ማርያም በሐዲስ ኪዳን
[መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ]
Join 👉 @linkortodoxe21💡
💡ጉባኤ፦ የድንግል ሕይወት💡
[ከ፫፻፸፮-፬፻፵፬ (376-444) ዓ.ም የነበረው እስክንድርያዊዉ
ቅዱስ ቄርሎስ]
“Come, O all ye women who desire
virginity…” (ድንግልናን የምትፈልጉ ሴቶች በሙሉ የጌታችን
እናት የኾነችውን የማርያምን ምሳሌ ተከተሉ፤ የርሷንም መንገድ
መናኛ ምግብ መብላቷንና መሬት ላይ መተኛቷን ዐስቡ፤ ለዚኽ
ዓለም ነገሮች ምንም ዐይነት ጉጉት የላትምና የርሷ ስምም
ኹልጊዜም በካህናት አፍ ውስጥ ነበር፤ ሰውነቷን በጭራሽ
በሕዝብ መታጠቢያ ውስጥ ታጥባ አታውቅም፤ ራሷን በፍጹም
በመዋቢያ የፊት ቀለም፣ በዐይን ኩልና በቅባት በጭራሽ አስውባ
አታውቅም፤ በጣም ያጌጠ ልብስ እንደሚወድዱ ኹሉም በዘመኗ
የነበሩ ሴቶች በደማቅ ባለቀለም ልብስ በጭራሽ አስጌጣ
አታውቅም፤ በጭራሽ የወይንን ጣዕም ቀምሳ አታውቅም፤
ኹልጊዜም ዓለማትን የፈጠረ ፈጣሪዋን ትጠብቅ ስለነበር ፊቷን
ወደ ምሥራቅ አዙራ ትቀመጥ ነበር፤ ከእናቷና ከአባቷ በስተቀር
ከማንም ጋር ተገናኝታና አውርታ አታውቅም
ነገረ ማርያም በሐዲስ ኪዳን
[መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ]
Join 👉 @linkortodoxe21💡
#ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤
¹⁴ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።
💎@linkortodoxe21
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤
¹⁴ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።
💎@linkortodoxe21
ኑ እንግዲህ ይህችን ንጽሕት በግ እናክብራት እናግናት የድኅነታችን መሥዋዕት የሚሆነውን በግ ወልዳልናለችና፡፡ ንጹሑን የዝናም ውሃ የተሸከመችልን የብርሃን ደመና እርሷን እናግናት እናትነት ከድንግልና አስተሳብራ የያዘች እርሷን ኑ እናመስግናት፡፡ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ ለአብርሃም ልጆች መመከያ የሆነች እርሷን ኑ ክብሯን ገናንነቷን እንናገር፡፡
ቅድስተ ቅዱሳን የተባለችውን ሁለተኛ ክፍል እርሷን ኑ እናመስግናት በዚች ሕግ በዚህችም ኪዳን አለባት፡፡ ሙሴም በኦሪት የተጻፈውን ለሕዝቡ ከነገረ ወዲያ ድንኳኑንም የሥራቸውንም ዕቃ ሁሉ ንዋየ ቅድሳቱን ይረጫል፡፡ (ዘፀአ ፳፬፥፰) እንዲሁም ልጅሽ ለደቀ መዛሙርቱም የወንጌልን ሕግ ካስተማራቸው በኋላ በዕንጨት መስቀል ላይ ራሱን ሠዋ፡፡ ባምላካዊ ደሙ ፈሳሽነትም መሃይማኑን የተቀቡ አደረጋቸው፡፡
መለኮት የተዋሐደው የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እውነት ነው፡፡ ይህ ደም ስላፈሰሰው ወንድሙን እንደሚከስ እንደ አቤል ደም አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ቃየልን እንደተናገረው እንዲህ ሲል የወንድምህ የደሙ ቃል ወደኔ ደረሰ፡፡ (ዘፍጥ ፬ ፥፲ ) የሕዝብና የአሕዛቡን ኃጢአት የሚያርቅ ነው እንጂ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ እንደነገራቸው እንዲህ ሲል ኃጢአት በሚሠረይ ገንዘብ ስለ እናንተ የሚፈስ ደሜ ይህ ነው ንሡ ጠጡ፡፡ (ማቴ ፳፮፣ ፳፯፣ ፳፰ )
ይህ ደም ስለ ወይኑ ቦታ እንደሞተ እንደ ኢይዝራኤላዊው እንደ ናቡቴ ደም አይደለም፡፡ (፩ ነገ ፳፩፥፲፫ ) ለበጎቹ ቤዛ የተሰቀለ የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላካዊ ደም ነው እንጂ፡፡ (ዮሐ ፲፥ ፲፩ ) ይህ ኃጢአትን ለማራቅ የማይችሉ የአሮን ልጆች እንዲሠዉት ላም ደም አይደለም፡፡ የዓለሙን ኃጢአት የሚሸከም የእግዚአብሔር በግ ንጹሕ ደም ነው እንጂ፡፡ (ዕብራውያን ፲፥ ፬-፭ )
ይህ ደም በቀራንዮ የፈሰሰው ነው፡፡ በአሥራ አንደ ሰዓት ጊዜ የአይሁድ ፋሲካ አለፈ ይህም ደም ዘወትር የሚቀዳው ፈሳሽነቱም እስከ ዘለዓለሙ የማይደርቅ ነው፡፡ ይህ ደም የኔ ዋጋ የዕዳዬም ከፋይ ነው፡፡ እኔ በዚህ ደም ተማጥኜአለሁ ዕድል ፈንታዬ ጽዋ ተርታዬ ፍሬ ከሌላቸው ጋራ እንዳይሆን፡፡ ይህም ካንቺ ሰው የሆነው አምላክ ደም የሚረባኝ የሚጠቅመኝ ይሁነኝ፡፡
ቅድስት ድንግል ሆይ በክርስቶስ እንድድን በክርስቶስም እንድኖር በክርስቶስም ነፍሳትን ከሚውጡ እባቦች እንድቤዥ አድርጊኝ፡፡
(አርጋኖን - አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ )
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቅድስተ ቅዱሳን የተባለችውን ሁለተኛ ክፍል እርሷን ኑ እናመስግናት በዚች ሕግ በዚህችም ኪዳን አለባት፡፡ ሙሴም በኦሪት የተጻፈውን ለሕዝቡ ከነገረ ወዲያ ድንኳኑንም የሥራቸውንም ዕቃ ሁሉ ንዋየ ቅድሳቱን ይረጫል፡፡ (ዘፀአ ፳፬፥፰) እንዲሁም ልጅሽ ለደቀ መዛሙርቱም የወንጌልን ሕግ ካስተማራቸው በኋላ በዕንጨት መስቀል ላይ ራሱን ሠዋ፡፡ ባምላካዊ ደሙ ፈሳሽነትም መሃይማኑን የተቀቡ አደረጋቸው፡፡
መለኮት የተዋሐደው የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እውነት ነው፡፡ ይህ ደም ስላፈሰሰው ወንድሙን እንደሚከስ እንደ አቤል ደም አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ቃየልን እንደተናገረው እንዲህ ሲል የወንድምህ የደሙ ቃል ወደኔ ደረሰ፡፡ (ዘፍጥ ፬ ፥፲ ) የሕዝብና የአሕዛቡን ኃጢአት የሚያርቅ ነው እንጂ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ እንደነገራቸው እንዲህ ሲል ኃጢአት በሚሠረይ ገንዘብ ስለ እናንተ የሚፈስ ደሜ ይህ ነው ንሡ ጠጡ፡፡ (ማቴ ፳፮፣ ፳፯፣ ፳፰ )
ይህ ደም ስለ ወይኑ ቦታ እንደሞተ እንደ ኢይዝራኤላዊው እንደ ናቡቴ ደም አይደለም፡፡ (፩ ነገ ፳፩፥፲፫ ) ለበጎቹ ቤዛ የተሰቀለ የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላካዊ ደም ነው እንጂ፡፡ (ዮሐ ፲፥ ፲፩ ) ይህ ኃጢአትን ለማራቅ የማይችሉ የአሮን ልጆች እንዲሠዉት ላም ደም አይደለም፡፡ የዓለሙን ኃጢአት የሚሸከም የእግዚአብሔር በግ ንጹሕ ደም ነው እንጂ፡፡ (ዕብራውያን ፲፥ ፬-፭ )
ይህ ደም በቀራንዮ የፈሰሰው ነው፡፡ በአሥራ አንደ ሰዓት ጊዜ የአይሁድ ፋሲካ አለፈ ይህም ደም ዘወትር የሚቀዳው ፈሳሽነቱም እስከ ዘለዓለሙ የማይደርቅ ነው፡፡ ይህ ደም የኔ ዋጋ የዕዳዬም ከፋይ ነው፡፡ እኔ በዚህ ደም ተማጥኜአለሁ ዕድል ፈንታዬ ጽዋ ተርታዬ ፍሬ ከሌላቸው ጋራ እንዳይሆን፡፡ ይህም ካንቺ ሰው የሆነው አምላክ ደም የሚረባኝ የሚጠቅመኝ ይሁነኝ፡፡
ቅድስት ድንግል ሆይ በክርስቶስ እንድድን በክርስቶስም እንድኖር በክርስቶስም ነፍሳትን ከሚውጡ እባቦች እንድቤዥ አድርጊኝ፡፡
(አርጋኖን - አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ )
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
+ ዝም ብለን የምንጠላው ሰው +
ከሩቅ የምናውቀው አንዳንድ ሰው የለም? ብዙም አናውቀውም:: ቀርበን አውርተነው አናውቅም:: ስናየው ግን እንዲሁ ደስ የማይለንና ያለ ምክንያት የምንጠላው ሰው የለም?
"እሱን ሰውዬ ጥሎብኝ አልወደውም"
"አይ እሱን ልጅ ቀልቤ ትከሻዬ አልወደደውም"
"እኔ እንጃ ለምን እንደሆነ ባላውቅም አልወዳትም:: ምክንያቴን አትጠይቀኝ ግን በቃ እንዲሁ አልወዳትም"
ምንም ምክንያት ሳይኖረን እንዲሁ የምንጠላው ሰው አለ::
እግዚአብሔር ግን
"አንድያ ልጁን እስኪሠጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአል" (ዮሐ 3:16)
ጠላቶቹ ሳለን በልጁ ሞት አዳነን እንደሚል እርሱ እኛን ለመጥላት ብዙ ምክንያት ነበረው:: እርሱ ግን እንዲሁ ወደደን:: ከእኛ ምንም ባያገኝም ስለ እኛ ያለው ፍቅር የእንዲሁ ፍቅር (unconditional love) ነበረ:: እርሱ እንዲሁ ወዶናል እኛ ግን እንዲሁ ሰው እንጠላለን::
ያለ ምክንያት መውደድ ቢያቅተን እንኳን ያለ ምክንያት መጥላታችን (unconditional hate) ቢቀር ምናለ?
የሚያሳዝነው ያለ ምክንያት የጠላናቸውን ሰዎች የበለጠ ለመጥላት በልባችን እስር ቤት ውስጥ በጥላቻ ሰንሰለት እናስራቸውና የበለጠ ለመጥላት ስለእነርሱ ክፉ ክፉ ማስረጃ ለመስማት እንተጋለን:: ጥሩ ነገራቸውን ለመስማት አንፈልግም:: ክፉ ስንሰማ ግን "እኮ እኔ እኮ ዝም ብሎ ትከሻዬ ይነግረኝ ነበር" ብለን በደስታ እንፈነድቃለን:: እንዲሁ የጠላነውን ሰው በምክንያት ለመጥላት በመቻላችን ደስ ይለናል::
እኛ ሰውን ለመጥላት ምክንያት የምንፈልገውን ያህል እንዲሁ የወደደን እግዚአብሔር ግን እኛን ለመማር ሰበብ ይፈልጋል:: ትንሽ በጎነት ቅንጣት ቅንነት ሲያገኝ እጅግ ይደሰታል:: ባለቅኔው "እግዚአብሔር መንግሥቱን በርካሽ ዋጋ ሸጠው:: በቀዝቃዛ ውኃ በዘለላ ዕንባ እና ማረኝ በሚል የወንበዴ ጩኸት!" እንዳሉት እሱ እኛን ይቅር ለማለት የሚታይ በጎነት ቢያጣ ልባችን ውስጥ ገብቶ ትንሽ መጸጸት ካለ ይፈልጋል:: እንዲሁ ወዶናልና እንዲሁ ሊተወን አይፈልግም::
"እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለሆነ
ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳን በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሠጠን"
ኤፌ 2:4
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ከሩቅ የምናውቀው አንዳንድ ሰው የለም? ብዙም አናውቀውም:: ቀርበን አውርተነው አናውቅም:: ስናየው ግን እንዲሁ ደስ የማይለንና ያለ ምክንያት የምንጠላው ሰው የለም?
"እሱን ሰውዬ ጥሎብኝ አልወደውም"
"አይ እሱን ልጅ ቀልቤ ትከሻዬ አልወደደውም"
"እኔ እንጃ ለምን እንደሆነ ባላውቅም አልወዳትም:: ምክንያቴን አትጠይቀኝ ግን በቃ እንዲሁ አልወዳትም"
ምንም ምክንያት ሳይኖረን እንዲሁ የምንጠላው ሰው አለ::
እግዚአብሔር ግን
"አንድያ ልጁን እስኪሠጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአል" (ዮሐ 3:16)
ጠላቶቹ ሳለን በልጁ ሞት አዳነን እንደሚል እርሱ እኛን ለመጥላት ብዙ ምክንያት ነበረው:: እርሱ ግን እንዲሁ ወደደን:: ከእኛ ምንም ባያገኝም ስለ እኛ ያለው ፍቅር የእንዲሁ ፍቅር (unconditional love) ነበረ:: እርሱ እንዲሁ ወዶናል እኛ ግን እንዲሁ ሰው እንጠላለን::
ያለ ምክንያት መውደድ ቢያቅተን እንኳን ያለ ምክንያት መጥላታችን (unconditional hate) ቢቀር ምናለ?
የሚያሳዝነው ያለ ምክንያት የጠላናቸውን ሰዎች የበለጠ ለመጥላት በልባችን እስር ቤት ውስጥ በጥላቻ ሰንሰለት እናስራቸውና የበለጠ ለመጥላት ስለእነርሱ ክፉ ክፉ ማስረጃ ለመስማት እንተጋለን:: ጥሩ ነገራቸውን ለመስማት አንፈልግም:: ክፉ ስንሰማ ግን "እኮ እኔ እኮ ዝም ብሎ ትከሻዬ ይነግረኝ ነበር" ብለን በደስታ እንፈነድቃለን:: እንዲሁ የጠላነውን ሰው በምክንያት ለመጥላት በመቻላችን ደስ ይለናል::
እኛ ሰውን ለመጥላት ምክንያት የምንፈልገውን ያህል እንዲሁ የወደደን እግዚአብሔር ግን እኛን ለመማር ሰበብ ይፈልጋል:: ትንሽ በጎነት ቅንጣት ቅንነት ሲያገኝ እጅግ ይደሰታል:: ባለቅኔው "እግዚአብሔር መንግሥቱን በርካሽ ዋጋ ሸጠው:: በቀዝቃዛ ውኃ በዘለላ ዕንባ እና ማረኝ በሚል የወንበዴ ጩኸት!" እንዳሉት እሱ እኛን ይቅር ለማለት የሚታይ በጎነት ቢያጣ ልባችን ውስጥ ገብቶ ትንሽ መጸጸት ካለ ይፈልጋል:: እንዲሁ ወዶናልና እንዲሁ ሊተወን አይፈልግም::
"እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለሆነ
ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳን በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሠጠን"
ኤፌ 2:4
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
+ ለምን ትቀናለህ? +
በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡
አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡
ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡
ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡
ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡
ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡
ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡
የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡
ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡
ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡
ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡
በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡
‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አለታ ወንዶ ኢትዮጵያ
ጥር 5 2013 ዓ.ም.
መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ቤተሰቦች ታሪክ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም share share share አርጉት
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡
አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡
ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::
ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡
ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡
ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡
ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡
የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡
ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡
የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡
ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡
ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡
ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡
በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡
‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አለታ ወንዶ ኢትዮጵያ
ጥር 5 2013 ዓ.ም.
መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ቤተሰቦች ታሪክ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም share share share አርጉት
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
"ድንግል ኾይ! 🙏✨🙏
በእውነቱ አንቺ ከታላላቆች ይልቅ ታላቅ ነሽ 🤲
ማኅደረ ቃለ አብ ኾይ! ከፍጡራን ወገን አንቺን ሊተካከል የሚችል ታላቅ ማን ነው?
ድንግል ኾይ! ከየትኛው ፍጥረት ጋር አወዳድርሻለኹ? አንቺ ቀድሞ በወርቅ ካጌጠችው የሕጉ ታቦት ይልቅ በንጽሕና ያጌጥሽ ታላቅ ነሽ! 💐💐💐
እውነተኛውን መና የተሸከምሽ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ መና የተባለውም ሥግው ቃል ነው፡፡" ✨✨✨
ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ
@linkortodoxe21
በእውነቱ አንቺ ከታላላቆች ይልቅ ታላቅ ነሽ 🤲
ማኅደረ ቃለ አብ ኾይ! ከፍጡራን ወገን አንቺን ሊተካከል የሚችል ታላቅ ማን ነው?
ድንግል ኾይ! ከየትኛው ፍጥረት ጋር አወዳድርሻለኹ? አንቺ ቀድሞ በወርቅ ካጌጠችው የሕጉ ታቦት ይልቅ በንጽሕና ያጌጥሽ ታላቅ ነሽ! 💐💐💐
እውነተኛውን መና የተሸከምሽ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ መና የተባለውም ሥግው ቃል ነው፡፡" ✨✨✨
ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ
@linkortodoxe21
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንኳን ለበዓለ ግዝረቱ ለክርስቶስ፣ ለቅዱስ ኤልያስ ነቢይ፣ ለቅዱስ ኖኅ ጻድቅ፣ ለታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፣ ለአባ ሙሴ ገዳማዊ እንዲኹም ለአባ ወርክያኖስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኹ 🙏
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
ዳግመኛም ዛሬ ጥር 6 ቀን ቅድስት ደብረ ቁስቋም፣ አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን፣ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ፣ ቅድስት ሰሎሜ፣ አባ አርከ ሥሉስ፣ አባ ጽጌ ድንግል እንዲኹም ቅድስት አርሴማ ድንግል ወርኃዊ መታሰቢያቸው ነው 🙏🙏🙏
አምላከ ቅዱሳን በቃልኪዳናቸው ይማረን 🤲 አሜን!
"የቅዱሳን መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. ፲፥፯
🌿🌿🌿🌼🌼🌼🌿🌿🌿🌼🌼🌼
@linkortodoxe21
እንኳን ለበዓለ ግዝረቱ ለክርስቶስ፣ ለቅዱስ ኤልያስ ነቢይ፣ ለቅዱስ ኖኅ ጻድቅ፣ ለታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፣ ለአባ ሙሴ ገዳማዊ እንዲኹም ለአባ ወርክያኖስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኹ 🙏
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
ዳግመኛም ዛሬ ጥር 6 ቀን ቅድስት ደብረ ቁስቋም፣ አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን፣ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ፣ ቅድስት ሰሎሜ፣ አባ አርከ ሥሉስ፣ አባ ጽጌ ድንግል እንዲኹም ቅድስት አርሴማ ድንግል ወርኃዊ መታሰቢያቸው ነው 🙏🙏🙏
አምላከ ቅዱሳን በቃልኪዳናቸው ይማረን 🤲 አሜን!
"የቅዱሳን መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. ፲፥፯
🌿🌿🌿🌼🌼🌼🌿🌿🌿🌼🌼🌼
@linkortodoxe21
+++እፈርድ ዘንድ እኔ ማነኝ?+++
በአንድ ወቅት አባ ፖርፎርዮስ እና ሦስት መንፈሳዊ ልጆቻቸው ወደ ገዳም ሲመለሱ መንገዱ በጣም ስላደከማቸው ታክሲ መያዝ ፈለጉ። በአጋጣሚ በርቀት ታክሲ ተመለከቱ። ሦስቱ የአባ አገልጋዮችም ታክሲውን ለማስቆም ገና ሲያስቡ ፤ አባ ፖርፎርዮስ "ተዉ አትጨነቁ ታክሲው በራሱ ይቆማል ፤ ነገር ግን ወደ ውስጥ ከገባን በኋላ ከእኔ በስተቀር ከታክሲ አሽከርካሪው ጋር ማንም እንዳይነጋገር" አሉ። አባ ፖርፎርዮስ እንደተናገሩት ለታክሲው ማንም ምልክት ሳይሰጠው ፤ ያሉበት ቦታ መጥቶ ቆመ። ኹሉም ወደ ታክሲው ገቡ ፤ አባ ፖርፎርዮስም የት መሔድ እንደሚፈልጉ ለሾፌሩ ተናገሩ።
አሽከርካሪው መኪናውን መንዳት እንደጀመረ ወዲያው ስለ ካህናት በደል እና ኃጢአት ማውራት ጀመረ። ስለ ካህናቱ በሚያቀርበው በእያንዳንዱ ክስና ዘለፋ ፤ ወደ ኋላ እየዞረ ሦስቱን ወጣት አገልጋዮች "እሺ ስለዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ ወጣቶች?" ይላቸዋል። ሦስቱ ወጣቶች ግን የአባን ቃል በማክበር አንዳች ምላሽ አይሠጡም ነበር። የታክሲ አሽከርካሪው ወጣቶቹ ምንም መልስ እንደማይሰጡት በተረዳ ጊዜ ወደ አባ ፖርፎርዮስ ዞር ብሎ "አባዬ!(በፌዝ መልክ) የተናገርኹት ኹሉ እውነታውን ነው ፤ አይደል እንዴ?" ሲል ጠየቃቸው። አባ ፖርፎርዮስም መልሰው "ልጄ አንድ አጭር ታሪክ እነግርሃለሁ ፤ የምነግርህ አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ኹለት ጊዜ ትሰማው ዘንድም አያሻም" አሉትና ቀጠሉ።
"በአንድ ወቅት አንድ ቦታ ላይ የሚኖር አንድ ሰው ነበር። የዚህ ሰው ጎረቤት በእድሜ ሸምገል ያለና በጣም ትልቅና ሰፊ መሬት ያለው ነበረ። ሆኖም በአንድ ምሽት ይኼ ሰው ባለሀብት የነበረ ጎረቤቱን ገድሎ መሬት ቆፍሮ ቀበረው። ይኼ ሳያንስ በሐሰተኛ መረጃዎች ንብረቱን ወደ ራሱ አዙሮ ፤ ያንን ትልቅ መሬት ሸጠው። ከዚያ መሬቱን በሸጠበት ገንዘብ ምን እንደገዛ ታውቃለህ? <ታክሲ ገዛበት>" አሉት። በዚህ ሰዓት ከሰማው ታሪክ የተነሣ ደንግጦ መንቀጥቀጥ ጀመረ። መኪናውን እንደምንም ወደ ዳር አስይዞ ካቆመ በኋላ እየጮኽ "አባ ዝም ይበሉ! ይህን ጉዳይ እርስዎ እና እኔ ብቻ ነን የምናውቀው ፤ እባክዎ ዝም ይበሉ!" አላቸው። አባም ቀጥለው "ይህን ሥራህን እግዚአብሔርም ያውቀዋል ፤ ይህን እንዳሳውቅህ የነገረኝ እግዚአብሔር ነው ፤ አሁንም ንስሓ ገብተህ ሕይወትህን አስተካክል" አሉት።
+++
+ ተወዳጆች ሆይ! "የምዋቹን ሞት አልፈቅድም" (ሕዝ. 18: 32) ያለው አምላክ እቅፍ ሥር መሆን እንዴት ያለ መታደል ነው? መድኃኔ ዓለም ስንተወው የማይተወን ፣ ስንገፋው የማይገፋን ፣ ስንርቀው በአባታዊ ፍቅር በምክንያት የሚጠራን ፣ ክፋታችንን በፍቅር ፣ መታበያችንን በትዕግሥት የሚያቸንፍ በእውነት ተናግረው የማይፈጽሙለት የነገሥታት ንጉሥ ፣ የኃያላን ኃያል በእውነት እርሱ ነው።
+ እግዚአብሔር ያከበራቸው ካህናትን ከሥጋ ድካም የተነሣ የማይባቸውን ጉድለት አይቼ ልፈርድ ቀርቶ አጠገቤ ስላለው ወንድሜ በደል እና ኃጢአት እገልጥ ዘንድ እኔ ማነኝ? አምላኬ ሆይ! ዛሬ የወደዱኝ ከፍ ከፍም ያደረጉኝ ፣ ቢያውቁት ኖሮ እንዲጠሉኝና እንዲሸሹኝ የሚያደርገውን በደሌን ተሸክመህ በቸርነትህ ሸፍነኽው ባይሆን ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር? ወዴትስ እሸሸግ ነበር?
+ በተስፋ መቁረጥ እንዳልጠፋ የታገሥኽኝን መታገሥ ፣ የምትጠራኝን የንስሓ ጥሪ ሳልረዳ አሁንም በበደል ለምኖር ልጅህ ማስተዋልን አድለኝ! ዛሬም ከእቅፍህ ሳትለየኝ ልጄ ብለህ ቀጥተህ ፤ ዘወትር በማትነጥፍ ቸርነትህ በምሕረትህ ጎብኘኝ!
Source : The Orthodox Life ተሻሽሎ የቀረበ!
ስብሐት ለእግዚአብሔር
✍ዲያቆን ደረጀ ድንቁ
ጥቅምት 11 2013 ዓ.ም
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
በአንድ ወቅት አባ ፖርፎርዮስ እና ሦስት መንፈሳዊ ልጆቻቸው ወደ ገዳም ሲመለሱ መንገዱ በጣም ስላደከማቸው ታክሲ መያዝ ፈለጉ። በአጋጣሚ በርቀት ታክሲ ተመለከቱ። ሦስቱ የአባ አገልጋዮችም ታክሲውን ለማስቆም ገና ሲያስቡ ፤ አባ ፖርፎርዮስ "ተዉ አትጨነቁ ታክሲው በራሱ ይቆማል ፤ ነገር ግን ወደ ውስጥ ከገባን በኋላ ከእኔ በስተቀር ከታክሲ አሽከርካሪው ጋር ማንም እንዳይነጋገር" አሉ። አባ ፖርፎርዮስ እንደተናገሩት ለታክሲው ማንም ምልክት ሳይሰጠው ፤ ያሉበት ቦታ መጥቶ ቆመ። ኹሉም ወደ ታክሲው ገቡ ፤ አባ ፖርፎርዮስም የት መሔድ እንደሚፈልጉ ለሾፌሩ ተናገሩ።
አሽከርካሪው መኪናውን መንዳት እንደጀመረ ወዲያው ስለ ካህናት በደል እና ኃጢአት ማውራት ጀመረ። ስለ ካህናቱ በሚያቀርበው በእያንዳንዱ ክስና ዘለፋ ፤ ወደ ኋላ እየዞረ ሦስቱን ወጣት አገልጋዮች "እሺ ስለዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ ወጣቶች?" ይላቸዋል። ሦስቱ ወጣቶች ግን የአባን ቃል በማክበር አንዳች ምላሽ አይሠጡም ነበር። የታክሲ አሽከርካሪው ወጣቶቹ ምንም መልስ እንደማይሰጡት በተረዳ ጊዜ ወደ አባ ፖርፎርዮስ ዞር ብሎ "አባዬ!(በፌዝ መልክ) የተናገርኹት ኹሉ እውነታውን ነው ፤ አይደል እንዴ?" ሲል ጠየቃቸው። አባ ፖርፎርዮስም መልሰው "ልጄ አንድ አጭር ታሪክ እነግርሃለሁ ፤ የምነግርህ አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ኹለት ጊዜ ትሰማው ዘንድም አያሻም" አሉትና ቀጠሉ።
"በአንድ ወቅት አንድ ቦታ ላይ የሚኖር አንድ ሰው ነበር። የዚህ ሰው ጎረቤት በእድሜ ሸምገል ያለና በጣም ትልቅና ሰፊ መሬት ያለው ነበረ። ሆኖም በአንድ ምሽት ይኼ ሰው ባለሀብት የነበረ ጎረቤቱን ገድሎ መሬት ቆፍሮ ቀበረው። ይኼ ሳያንስ በሐሰተኛ መረጃዎች ንብረቱን ወደ ራሱ አዙሮ ፤ ያንን ትልቅ መሬት ሸጠው። ከዚያ መሬቱን በሸጠበት ገንዘብ ምን እንደገዛ ታውቃለህ? <ታክሲ ገዛበት>" አሉት። በዚህ ሰዓት ከሰማው ታሪክ የተነሣ ደንግጦ መንቀጥቀጥ ጀመረ። መኪናውን እንደምንም ወደ ዳር አስይዞ ካቆመ በኋላ እየጮኽ "አባ ዝም ይበሉ! ይህን ጉዳይ እርስዎ እና እኔ ብቻ ነን የምናውቀው ፤ እባክዎ ዝም ይበሉ!" አላቸው። አባም ቀጥለው "ይህን ሥራህን እግዚአብሔርም ያውቀዋል ፤ ይህን እንዳሳውቅህ የነገረኝ እግዚአብሔር ነው ፤ አሁንም ንስሓ ገብተህ ሕይወትህን አስተካክል" አሉት።
+++
+ ተወዳጆች ሆይ! "የምዋቹን ሞት አልፈቅድም" (ሕዝ. 18: 32) ያለው አምላክ እቅፍ ሥር መሆን እንዴት ያለ መታደል ነው? መድኃኔ ዓለም ስንተወው የማይተወን ፣ ስንገፋው የማይገፋን ፣ ስንርቀው በአባታዊ ፍቅር በምክንያት የሚጠራን ፣ ክፋታችንን በፍቅር ፣ መታበያችንን በትዕግሥት የሚያቸንፍ በእውነት ተናግረው የማይፈጽሙለት የነገሥታት ንጉሥ ፣ የኃያላን ኃያል በእውነት እርሱ ነው።
+ እግዚአብሔር ያከበራቸው ካህናትን ከሥጋ ድካም የተነሣ የማይባቸውን ጉድለት አይቼ ልፈርድ ቀርቶ አጠገቤ ስላለው ወንድሜ በደል እና ኃጢአት እገልጥ ዘንድ እኔ ማነኝ? አምላኬ ሆይ! ዛሬ የወደዱኝ ከፍ ከፍም ያደረጉኝ ፣ ቢያውቁት ኖሮ እንዲጠሉኝና እንዲሸሹኝ የሚያደርገውን በደሌን ተሸክመህ በቸርነትህ ሸፍነኽው ባይሆን ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር? ወዴትስ እሸሸግ ነበር?
+ በተስፋ መቁረጥ እንዳልጠፋ የታገሥኽኝን መታገሥ ፣ የምትጠራኝን የንስሓ ጥሪ ሳልረዳ አሁንም በበደል ለምኖር ልጅህ ማስተዋልን አድለኝ! ዛሬም ከእቅፍህ ሳትለየኝ ልጄ ብለህ ቀጥተህ ፤ ዘወትር በማትነጥፍ ቸርነትህ በምሕረትህ ጎብኘኝ!
Source : The Orthodox Life ተሻሽሎ የቀረበ!
ስብሐት ለእግዚአብሔር
✍ዲያቆን ደረጀ ድንቁ
ጥቅምት 11 2013 ዓ.ም
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
መልካም በዓል !!!!!
"የእግዚአብሔር ሠራዊት ኪሩቤል ሱራፌል አፍኒን ዕውቀት ያላቸው መላእክትም ሁሉ ሥላሴ የፈጠሯቸው መላእክት ሁሉ ያመሰግናሉ ሌላ ዕውቀትም ይሰጣል።"
ሄኖክ 17:17
"ሁሉ በሥላሴ ፈቃድ ተፈጥሯልና ይህ ለምንድ ነው ያለ ለምንድነው የሚል የለም።"
ሲራክ 39:21
@linkortodoxe21
መልካም በዓል !!!!!
"የእግዚአብሔር ሠራዊት ኪሩቤል ሱራፌል አፍኒን ዕውቀት ያላቸው መላእክትም ሁሉ ሥላሴ የፈጠሯቸው መላእክት ሁሉ ያመሰግናሉ ሌላ ዕውቀትም ይሰጣል።"
ሄኖክ 17:17
"ሁሉ በሥላሴ ፈቃድ ተፈጥሯልና ይህ ለምንድ ነው ያለ ለምንድነው የሚል የለም።"
ሲራክ 39:21
@linkortodoxe21
🔺ቅዳሴ ማርያም
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመክራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይናገራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይፈፅማሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይሠራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስማማሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያከናውናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይልካሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያሰለጥናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ምስክር_ይሆናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ሰውን_ይስባሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያለምዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመክራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያነጻሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያጸራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያከብራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያጸናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስጨክናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስተምራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይጋርዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያለብሳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ባለምዋል_ያደርጋሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይቀመጣሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይፈርዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመረምራሉ።
እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን አንድነትን ሳንለይ የተለየ እንዳይሆን ። የተቀላቀለ እንዳይሆን እንለይ።
እንደ አብርሃምና እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብም ሦስት የምንል አይደለም በገጽ ሦስት ሲሆን አንድ
ነው እንጂ ። ከፍጥረት ሁሉ እንደሚቀድም እንደ አዳም አንድ የምንል አይደለም በባሕርዪው አንድ ሲሆን ሦስት ነው እንላለን እንጂ ።
ክፉዎች አይሁድ ባለማወቃቸው የእግዚአብሔርን ገጽና አካል አንድ ነው የሚሉ በደለኞችን የይስማኤል ወገኖችንም እነሆ እንሰማቸዋለን ልቦናቸውን ያሳወሩ ናቸው ።
አምላኮቻቸውም ብዙ አጋንንቶቻቸው ብዙ የሆኑ በጣዖት የሚያመልኩ አረማውያንን እነሆ እናያቸዋለን ። እኛ ግን በጎ ጐዳና የሚያስተምሩትን እንከተላለን ። ሐዋርያት እንዲህ እያሉ እንዳስተማሩን ።
አብ ፀሐይ ነው ወልድ ፀሐይ ነው መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው ። ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው ።
አብ እሳት ነው ወልድ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስም እሳት ነው ። በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ነው ። አብ ጎሕ ነው ወልድ ጎሕ ነው መንፈስ ቅዱስም ጎሕ ነው ። በብርሃኑ ፀዳል ጨለማ የራቀበት አንድ የጧት ጎሕ ነው ።
አብ ጒንደ ወይን ነው ወልድ ጒንደ ወይን ነው መንፈስ ቅዱስም ጒንደ ወይን ነው ። ዓለሙ ሁሉ የጣፈጠበት አንድ የሕይወት ወይን ነው ።
አብ ሐሊብ ነው ወልድ ሐሊብ ነው መንፈስ ቅዱስም ሐሊብ ነው ። ጭማሪ የሌለበት አንድ ሐሊብ እርሱ ነው ።
እንዲህም እናምናለን እንዲህም እንታመናለን ።
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመክራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይናገራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይፈፅማሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይሠራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስማማሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያከናውናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይልካሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያሰለጥናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ምስክር_ይሆናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ሰውን_ይስባሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያለምዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመክራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያነጻሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያጸራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያከብራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያጸናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስጨክናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያስተምራሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይጋርዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ያለብሳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ባለምዋል_ያደርጋሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይቀመጣሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይፈርዳሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ #ይመረምራሉ።
እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን አንድነትን ሳንለይ የተለየ እንዳይሆን ። የተቀላቀለ እንዳይሆን እንለይ።
እንደ አብርሃምና እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብም ሦስት የምንል አይደለም በገጽ ሦስት ሲሆን አንድ
ነው እንጂ ። ከፍጥረት ሁሉ እንደሚቀድም እንደ አዳም አንድ የምንል አይደለም በባሕርዪው አንድ ሲሆን ሦስት ነው እንላለን እንጂ ።
ክፉዎች አይሁድ ባለማወቃቸው የእግዚአብሔርን ገጽና አካል አንድ ነው የሚሉ በደለኞችን የይስማኤል ወገኖችንም እነሆ እንሰማቸዋለን ልቦናቸውን ያሳወሩ ናቸው ።
አምላኮቻቸውም ብዙ አጋንንቶቻቸው ብዙ የሆኑ በጣዖት የሚያመልኩ አረማውያንን እነሆ እናያቸዋለን ። እኛ ግን በጎ ጐዳና የሚያስተምሩትን እንከተላለን ። ሐዋርያት እንዲህ እያሉ እንዳስተማሩን ።
አብ ፀሐይ ነው ወልድ ፀሐይ ነው መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው ። ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው ።
አብ እሳት ነው ወልድ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስም እሳት ነው ። በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ነው ። አብ ጎሕ ነው ወልድ ጎሕ ነው መንፈስ ቅዱስም ጎሕ ነው ። በብርሃኑ ፀዳል ጨለማ የራቀበት አንድ የጧት ጎሕ ነው ።
አብ ጒንደ ወይን ነው ወልድ ጒንደ ወይን ነው መንፈስ ቅዱስም ጒንደ ወይን ነው ። ዓለሙ ሁሉ የጣፈጠበት አንድ የሕይወት ወይን ነው ።
አብ ሐሊብ ነው ወልድ ሐሊብ ነው መንፈስ ቅዱስም ሐሊብ ነው ። ጭማሪ የሌለበት አንድ ሐሊብ እርሱ ነው ።
እንዲህም እናምናለን እንዲህም እንታመናለን ።
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
አንተ ሰው! ልጅህ ይታዘዝልህ ዘንድ ትሻለህን? እንኪያስ ገና ከሕፃንነቱ አንሥተህ በጌታ ምክርና ተግሣጽ አሳድገው፡፡ “ልጅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማት አያስፈልገውም” ብለህ በፍጹም የምታስብ አትኹን፡፡ ልጅህ ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚማርበት ጊዜ ከኹሉም አስቀድሞ የሚማረው፡- “አባትህና እናትህን አክብር” የሚለውን ደገኛ ትእዛዝ ነውና፡፡ ይህ ቀድሞ የሚጠቅመው ደግሞ አንተን ነው፡፡ ስለዚህ “ቅዱሳት መጻሕፍትን ሊያነቡ የሚገባቸው መነኰሳት ናቸው፤ ታዲያ ልጄን የማሳድገው መነኵሴ እንዲኾን ነውን?” አትበለኝ፡፡ ልጅህ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ያለበት የግድ መነኵሴ ለመኾን አይደለም፡፡ መነኵሴ ባይኾንም እንኳን ጥሩ ክርስቲያን እንዲኾን አድርገው፡፡
እስኪ ንገረኝ! እንደዚህ ያለ በጎ ነገርን የምትፈራው ለምንድን ነው? ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ የምትፈራው ለምንድን ነው? እኔ ግን እነግርሃለሁ ለሰው ኹሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን መማር እጅግ አስፈላጊ ነው። በተለይም ለሕፃናት! “ለምን?” ብለህ ትጠይቀኝ ይኾናል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ፡- ሕፃናት በዚህ ዕድሜያቸው ለከንቱነት፣ ዓለማዊ ተረቶችን ለመስማት፣ በአሕዛብ ዘንድ ታዋቂ የኾኑ ሰዎችን ለራሳቸው ምሳሌ አድርገው ለመውሰድ፣ የእነዚህ ስመ ገናና ሰዎች ደገኛ ያልኾነ አመለካከትም ለራሳቸው ለመውሰድና ሞትን የሚፈሩ ለመኾን፣ ለምሳሌ አኪላስ ለዕቁባቱ ብሎ ሲሞት ሌላው ደግሞ ሰክሮ መሞቱንና እነዚህን የመሰሉ አሳፋሪ ተረቶችን ሰምተው የእነዚህን ተረቶች መልእክትም የራሳቸው ለማድረግ እጅግ የተጋለጡ ናቸውና፡፡ ስለዚህ ልጅህ ለእነዚህ ኹሉ ተግዳረቶች መፍትሔ ያሻዋል - ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ!
#በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ ከተተረጎመ "ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ" መጽሐፍ
❤️@linkortodoxe21
❤️@linkortodoxe21
❤️@linkortodoxe21
እስኪ ንገረኝ! እንደዚህ ያለ በጎ ነገርን የምትፈራው ለምንድን ነው? ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ የምትፈራው ለምንድን ነው? እኔ ግን እነግርሃለሁ ለሰው ኹሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን መማር እጅግ አስፈላጊ ነው። በተለይም ለሕፃናት! “ለምን?” ብለህ ትጠይቀኝ ይኾናል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ፡- ሕፃናት በዚህ ዕድሜያቸው ለከንቱነት፣ ዓለማዊ ተረቶችን ለመስማት፣ በአሕዛብ ዘንድ ታዋቂ የኾኑ ሰዎችን ለራሳቸው ምሳሌ አድርገው ለመውሰድ፣ የእነዚህ ስመ ገናና ሰዎች ደገኛ ያልኾነ አመለካከትም ለራሳቸው ለመውሰድና ሞትን የሚፈሩ ለመኾን፣ ለምሳሌ አኪላስ ለዕቁባቱ ብሎ ሲሞት ሌላው ደግሞ ሰክሮ መሞቱንና እነዚህን የመሰሉ አሳፋሪ ተረቶችን ሰምተው የእነዚህን ተረቶች መልእክትም የራሳቸው ለማድረግ እጅግ የተጋለጡ ናቸውና፡፡ ስለዚህ ልጅህ ለእነዚህ ኹሉ ተግዳረቶች መፍትሔ ያሻዋል - ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ!
#በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ ከተተረጎመ "ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ" መጽሐፍ
❤️@linkortodoxe21
❤️@linkortodoxe21
❤️@linkortodoxe21
ይህ ✝የህይወት መንገድ✝ የተሰኘ ቴሌግራም ቻናላችን
👉ምክሮችና የአባቶች ተግሳጾች
👉የተለያዩ የህይወት ትምህርቶች
👉የህይወት ችግሮችና መፍትሄዎች
👉መንፈሳዊ ግጥሞች
👉መንፈሳዊ ታሪኮች
👉የቮይስ ትምህርቶች
👉የቪድዮ ትምህርቶች
👉እለታዊ የብሩክ ንጋት ብሩህ ቀን መርሃግብሮች 👉መንፈሳዊ መዝሙሮችና የተለያዩ🔵መንፈሳዊ🔵 አገልግሎቶችን ያቀርባል።የአገልግሎቶቻችን ተካፋይ ለመሆን ይህንን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
@yehywetmenged
@yehywetmenged
@yehywetmenged
የዚህ ቻናል #እህት የሆነውን ✝ህይወት ቲዩብ✝የተሰኘውን ብዙ አገልግሎቶችን የምናቀርብበትን ቻናል ይመልከቱ።ከወደዱትም❤️ሰብስክራይብ❤️ በማድረግ ቤተሰባaችን ይሁኑ።
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
👉ምክሮችና የአባቶች ተግሳጾች
👉የተለያዩ የህይወት ትምህርቶች
👉የህይወት ችግሮችና መፍትሄዎች
👉መንፈሳዊ ግጥሞች
👉መንፈሳዊ ታሪኮች
👉የቮይስ ትምህርቶች
👉የቪድዮ ትምህርቶች
👉እለታዊ የብሩክ ንጋት ብሩህ ቀን መርሃግብሮች 👉መንፈሳዊ መዝሙሮችና የተለያዩ🔵መንፈሳዊ🔵 አገልግሎቶችን ያቀርባል።የአገልግሎቶቻችን ተካፋይ ለመሆን ይህንን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
@yehywetmenged
@yehywetmenged
@yehywetmenged
የዚህ ቻናል #እህት የሆነውን ✝ህይወት ቲዩብ✝የተሰኘውን ብዙ አገልግሎቶችን የምናቀርብበትን ቻናል ይመልከቱ።ከወደዱትም❤️ሰብስክራይብ❤️ በማድረግ ቤተሰባaችን ይሁኑ።
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
ፆመ ገሃድ ምንድነው?
ጾመ ገሃድ
ይህ ጾም የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጥምቀት በማሰብ
የጥምቀት ዋዜማ የሚፆም ፆም ነው፡፡ ይህም ማለት በጥምቀት ዋዜማ ከምግብ መከልከል ነው፡፡ የሚቆርብ ሰው አክፍሎ የሚያድር ስለሆነም የጥምቀትን ድራር መጾም ነው፡፡ ሐዋርያት
«ልደት ጥምቀት ዓርብ ረቡዕ ቢውል በሌሊት ቀድሰው ሥጋውን ደሙን ይቀበሉ፤ ከሌሊቱ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጹሙ ብለው አይፍረዱ» ብለዋል /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/፡፡ የልደትና
የጥምቀት በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ሃምሳ የሚበላውን የጥሉላት ምግብ በጠዋት በመብላት ምእመናን በዓሉን እንዲያከብሩ ታዟል፡፡
ይህም እነዚህ ሁለቱ ታላላቅ የእግዚአብሔር በዓላት
በመሆናቸው ነው፡፡ የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ በሚውልበት ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ ማክሰኞንና ሐሙስን
በመጾማችን ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል፡፡ በዚህም የጾምና የበዓል ማክበር ሥራ ይከናወናል፡፡ የጥምቀትን ዋዜማ ጥሉላት መባልዕትን መተው ነው፡፡ ይህንንም እንደ ዘይቤው ገሀድ ይለዋል፣ መገለጫ፣ ግልጥ፣ ይፋ መሆን ማለት ነው፡፡
እንዲሁም ጋድ ይለዋል፣ ለውጥ፣ ልዋጭ ማለት ነው፡፡ ጥምቀት ረቡዕ ዓርብ ሲውል በዚያ ለውጥ ማክሰኞ ሐሙስ ይጾማልና ጋድ አለው፡፡ እንዲሁም አንድ ጊዜ ሲጾም አንድ ጊዜ ሲቀር
እንዳይረሳና ቅዳሜ ወይም እሑድ በሰንበት ቀን ይጾሙ ዘንድ አይቻልም፣ ነገር ግን እህል ውኃ እንጂ ጥሉላት ከመብላት መጠበቅ ይገባል፡፡
ልደት የሚውልባቸው ረቡዕና ዓርብ ቢሆኑ የፍሥክ /
የሚበላባቸው/ ቀናት ሆነው እንዲከበሩ ሐዋርያት ያዘዙ ቢሆንም በዋዜማው የሚገኙት ማክሰኞና ሐሙስ ከጾመ ነቢያት ጋር የተያያዙ ስለሆኑ መጾማቸው ግድ ነው፡፡ ሆኖም የነቢያትን ጾም
የማይጾሙ ሰዎች በመላው የጾሙ ቀናት ሲበሉ ቆይተው
በዋዜማው ብቻ ገሀድ ነው ብለው ይጾማሉ፡፡ ነገር ግን ይሄ ትክክል አይደለም። ጾሙ የጥምቀት ብቻ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ አባቶቻችን በፆም በጸሎት በረከት እንዳገኙ እኛም ከእግዚአብሔር በረከት እናገኛለን እና መፆምን ቸል አንበል ለዚህም አምላካችን ይርዳን አሜን፡
(ምንጭ ከገድላት አንደበት)
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ጾመ ገሃድ
ይህ ጾም የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጥምቀት በማሰብ
የጥምቀት ዋዜማ የሚፆም ፆም ነው፡፡ ይህም ማለት በጥምቀት ዋዜማ ከምግብ መከልከል ነው፡፡ የሚቆርብ ሰው አክፍሎ የሚያድር ስለሆነም የጥምቀትን ድራር መጾም ነው፡፡ ሐዋርያት
«ልደት ጥምቀት ዓርብ ረቡዕ ቢውል በሌሊት ቀድሰው ሥጋውን ደሙን ይቀበሉ፤ ከሌሊቱ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጹሙ ብለው አይፍረዱ» ብለዋል /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/፡፡ የልደትና
የጥምቀት በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ሃምሳ የሚበላውን የጥሉላት ምግብ በጠዋት በመብላት ምእመናን በዓሉን እንዲያከብሩ ታዟል፡፡
ይህም እነዚህ ሁለቱ ታላላቅ የእግዚአብሔር በዓላት
በመሆናቸው ነው፡፡ የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ በሚውልበት ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ ማክሰኞንና ሐሙስን
በመጾማችን ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል፡፡ በዚህም የጾምና የበዓል ማክበር ሥራ ይከናወናል፡፡ የጥምቀትን ዋዜማ ጥሉላት መባልዕትን መተው ነው፡፡ ይህንንም እንደ ዘይቤው ገሀድ ይለዋል፣ መገለጫ፣ ግልጥ፣ ይፋ መሆን ማለት ነው፡፡
እንዲሁም ጋድ ይለዋል፣ ለውጥ፣ ልዋጭ ማለት ነው፡፡ ጥምቀት ረቡዕ ዓርብ ሲውል በዚያ ለውጥ ማክሰኞ ሐሙስ ይጾማልና ጋድ አለው፡፡ እንዲሁም አንድ ጊዜ ሲጾም አንድ ጊዜ ሲቀር
እንዳይረሳና ቅዳሜ ወይም እሑድ በሰንበት ቀን ይጾሙ ዘንድ አይቻልም፣ ነገር ግን እህል ውኃ እንጂ ጥሉላት ከመብላት መጠበቅ ይገባል፡፡
ልደት የሚውልባቸው ረቡዕና ዓርብ ቢሆኑ የፍሥክ /
የሚበላባቸው/ ቀናት ሆነው እንዲከበሩ ሐዋርያት ያዘዙ ቢሆንም በዋዜማው የሚገኙት ማክሰኞና ሐሙስ ከጾመ ነቢያት ጋር የተያያዙ ስለሆኑ መጾማቸው ግድ ነው፡፡ ሆኖም የነቢያትን ጾም
የማይጾሙ ሰዎች በመላው የጾሙ ቀናት ሲበሉ ቆይተው
በዋዜማው ብቻ ገሀድ ነው ብለው ይጾማሉ፡፡ ነገር ግን ይሄ ትክክል አይደለም። ጾሙ የጥምቀት ብቻ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ አባቶቻችን በፆም በጸሎት በረከት እንዳገኙ እኛም ከእግዚአብሔር በረከት እናገኛለን እና መፆምን ቸል አንበል ለዚህም አምላካችን ይርዳን አሜን፡
(ምንጭ ከገድላት አንደበት)
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
#ከተራ_ምንድን_ነው?
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
መልካም የከተራ በዓል
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
መልካም የከተራ በዓል
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ጌታችን ለምን በውሃ ተጠመቀ?
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)
አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)
አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቃና ዘገሊላ
ቃና' የሚለው ቃል በሃገራችን ልሳን (በአማርኛ)
የምግብን: የመጠጥን ጥፍጥና ወይም በጐ መዓዛን የሚያመለክት ነው:: ምንአልባትም ከዚህ በዓል ምሥጢር የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ግን ቃና ከገሊላ አውራጃዎች አንዷ ናት:: ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚህች ሥፍራ ተገኝቶ በድንግል እናቱ ምልጃ ታላቅ ተአምርን በዚህች ዕለት ሠርቷል
ተአምር የሚለውን ቃል በቁሙ 'ምልክት' ብሎ
መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ (በላይ):
ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ (ሲፈጸም) ተአምር ይባላል:: ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው
ስለዚህም ነው 'ኤልሻዳይ / ከሐሌ ኩሉ / ሁሉን
ቻይ' እያልን የምንጠራው:: እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ (ኦሪትን ተመልከት) እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ (1ነገሥትን ተመልከት) እንደ ነበር ይታወቃል
እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: (ማቴ. 10:8, 17:20, ማር. 16:17, ሉቃ. 10:17, ዮሐ. 14:12) እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: (ሐዋ. 3:6, 5:1, 5:12, 8:6, 9:33-43, 14:8, 19:11)
ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በወንጌሉ ምዕራፍ 2 ላይ
እንዳስቀመጠው የቃና ዘገሊላው ተአምር የመጀመሪያው ነው:: "ወዝንቱ ቀዳሜ ተአምር ዘገብረ . . ." እንዲል:: (ዮሐ. 2:11) ያ ማለት ግን ጌታ ከዚያ በፊት ተአምራትን አልሠራም ማለት አይደለም
ይልቁኑ ራሱን ከገለጠና ከተጠመቀ በኋላ የሠራው
የመጀመሪያው ተአምር ነው ሲል ነው እንጂ:: ምክንያቱም መድኃኒታችን እንደ ተጠመቀ ዕለቱኑ ገዳመ ቆረንቶስ ገብቷልና:: (ማቴ. 4:1) አንድም በቃና ሌሎች ተአምራትን የሚሠራ ነውና ይህ
ተአምር በቃና የመጀመሪያው ሆነ
+ትክክለኛው የቃና ዘገሊላ ቀን የካቲት 23 ነው:: ጥር 11 ተጠምቆ: የካቲት 21 ቀን ከጾም ተመልሷል:: ከዚያም የካቲት 23 ቀን ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ ሒዷል:: ነገር ግን አበው መንፈስ ቅዱስ እንደ መራቸው የውሃ በዓል
ከውሃ በዓል ጋር ይስማማል ብለው ጥር 12 ቀን አድርገውታል
በቃና ዘገሊላ ሙሽራው ዶኪማስ ሲሆን ባለ ሠርጉ
ደግሞ አባቱ ዮአኪን ነው:: ይህም ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል አጐቱ ነው:: የልጁ ጋብቻ የተቀደሰ ይሆን ዘንድም ጌታ ክርስቶስን: ድንግል እናቱንና ባለሟሎቹ ሐዋርያትን ወደ ሠርጉ ጠራ
ምንም እንኳ መድኃኒታችንና እመቤታችን ከድግሱ
የማይበሉ ቢሆኑም (በትሕርምት ኗሪዎች ነበሩና)
ጠሪውን ደስ ለማሰኘት ሠርጉን (ብቻውን) ለመቀደስና የጋብቻን ክቡርነት ለማሳየት አብረው ታደሙ
የሠርጉ ሥነ ሥርዓት ሲጀመር በድንኳኑ ውስጥ ጌታ ከመካከል ተቀመጠ:: ድንግል በቀኙ: ዮሐንስ በግራው
ሲቀመጡ: ሌሎች
ሐዋርያት ግራና ቀኝ ከበው ተቀመጡ:: ሲበላና ሲጠጣ
ድንገት የተደገሰው ምግብና መጠጥ አለቀ::
ደጋሾቹ በጭንቅ ላይ ሳሉም አይጠና ሆዷ ድንግል እመ ብርሃን የሆነውን አወቀች:: እንዴት አወቀች ቢሉ:- በጸጋ: አንድም 'ከልጅሽ አማልጂን' ብለው ቢለምኗት ነው ይሏል:: እመቤታችን በዚያ ጊዜ ወደ ልጇ ቀርባ ቸር ልጇን "ወይንኬ አልቦሙ-ወይኑኮ አልቆባቸዋል" አለችው
+ለጊዜው ወይኑም: ምግቡም ስላለቀባቸው እንዲህ አለች:: በምሥጢሩ ግን ወይን ያለችው ፍቅርን: ቅዱስ ቃሉንና ክቡር ደሙን ነው:: ጌታም ይመልሳል:- "ምንት ብየ ምስሌኪ ኦ ብእሲቶ: ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ-አንቺ ሆይ! (እናቴ ሆይ!)
ያልሺኚን አላደርግ ዘንድ ካንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ? ነገር
ግን ጊዜው ገና አልደረሰም ብየ ነው እንጂ" አላት::
ምክንያቱም ጌታ:-
የወይን ጋኖቹ እስኪያልቁ ይጠብቅ ነበር:: (አበረከተ ይሉታልና) አንድም ይሁዳ ወጥቶ ነበርና እርሱ እስኪመለስ ነው:: (እኔ ስወጣ ጠብቆ ተአምር ሠራ ብሎ ለክፋቱ ምክንያት እንዳያቀርብ) አንድም "ወይን (ቅዱስ ደሜን) የምሰጠው በቀራንዮ አንባ ነው" ሲል "ጊዜየ ገና ነው" ብሏታል:: አንዳንድ ልቡናቸው የጠፋ ወገኖቻችን ጌታ እመቤታችንን እንዳቃለላት (ሎቱ ስብሐት! ወላቲ ስብሐት!) አስመስለው ይናገራሉ:: ይህንን ስእንኅን ጌታ ባለጌዎቹ እነሱም አያደርጉት:: "አባትህንና እናትህን አክብር" (ዘጸ. 20) ያለ ጌታ እንዴት ለእናቱ ክብርን ይነፍጋል?ልቡና ይስጠን!
ወደ ጉዳያችን ስንመለስ መድኃኒታችን እንዲህ ሲል መለስላት:: ተግባብተዋልና እመ ብርሃን አሳላፊዎቹን "ኩሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ-የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው:: (ዮሐ. 2:5) ጌታም በ6ቱ ጋኖች ውሃ አስሞልቶ በተአምራት ወይን አደረጋቸው
+እንጀራውን ወጡን በየሥፍራው ሞላው:: ታላቅ ደስታም ሆነ:: የአሳላፊዎቹ አለቃም (ለአባታችን አብርሃም ምሳሌ ነው) ከወይኑ ጥፍጥና የተነሳ አደነቀ:: በዚህም የድንግል ማርያም አማላጅነት: የመድኃኒታችን ከሃሊነት ታወቀ: ተገለጠ
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ቃና' የሚለው ቃል በሃገራችን ልሳን (በአማርኛ)
የምግብን: የመጠጥን ጥፍጥና ወይም በጐ መዓዛን የሚያመለክት ነው:: ምንአልባትም ከዚህ በዓል ምሥጢር የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ግን ቃና ከገሊላ አውራጃዎች አንዷ ናት:: ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚህች ሥፍራ ተገኝቶ በድንግል እናቱ ምልጃ ታላቅ ተአምርን በዚህች ዕለት ሠርቷል
ተአምር የሚለውን ቃል በቁሙ 'ምልክት' ብሎ
መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ (በላይ):
ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ (ሲፈጸም) ተአምር ይባላል:: ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው
ስለዚህም ነው 'ኤልሻዳይ / ከሐሌ ኩሉ / ሁሉን
ቻይ' እያልን የምንጠራው:: እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ (ኦሪትን ተመልከት) እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ (1ነገሥትን ተመልከት) እንደ ነበር ይታወቃል
እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: (ማቴ. 10:8, 17:20, ማር. 16:17, ሉቃ. 10:17, ዮሐ. 14:12) እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: (ሐዋ. 3:6, 5:1, 5:12, 8:6, 9:33-43, 14:8, 19:11)
ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በወንጌሉ ምዕራፍ 2 ላይ
እንዳስቀመጠው የቃና ዘገሊላው ተአምር የመጀመሪያው ነው:: "ወዝንቱ ቀዳሜ ተአምር ዘገብረ . . ." እንዲል:: (ዮሐ. 2:11) ያ ማለት ግን ጌታ ከዚያ በፊት ተአምራትን አልሠራም ማለት አይደለም
ይልቁኑ ራሱን ከገለጠና ከተጠመቀ በኋላ የሠራው
የመጀመሪያው ተአምር ነው ሲል ነው እንጂ:: ምክንያቱም መድኃኒታችን እንደ ተጠመቀ ዕለቱኑ ገዳመ ቆረንቶስ ገብቷልና:: (ማቴ. 4:1) አንድም በቃና ሌሎች ተአምራትን የሚሠራ ነውና ይህ
ተአምር በቃና የመጀመሪያው ሆነ
+ትክክለኛው የቃና ዘገሊላ ቀን የካቲት 23 ነው:: ጥር 11 ተጠምቆ: የካቲት 21 ቀን ከጾም ተመልሷል:: ከዚያም የካቲት 23 ቀን ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ ሒዷል:: ነገር ግን አበው መንፈስ ቅዱስ እንደ መራቸው የውሃ በዓል
ከውሃ በዓል ጋር ይስማማል ብለው ጥር 12 ቀን አድርገውታል
በቃና ዘገሊላ ሙሽራው ዶኪማስ ሲሆን ባለ ሠርጉ
ደግሞ አባቱ ዮአኪን ነው:: ይህም ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል አጐቱ ነው:: የልጁ ጋብቻ የተቀደሰ ይሆን ዘንድም ጌታ ክርስቶስን: ድንግል እናቱንና ባለሟሎቹ ሐዋርያትን ወደ ሠርጉ ጠራ
ምንም እንኳ መድኃኒታችንና እመቤታችን ከድግሱ
የማይበሉ ቢሆኑም (በትሕርምት ኗሪዎች ነበሩና)
ጠሪውን ደስ ለማሰኘት ሠርጉን (ብቻውን) ለመቀደስና የጋብቻን ክቡርነት ለማሳየት አብረው ታደሙ
የሠርጉ ሥነ ሥርዓት ሲጀመር በድንኳኑ ውስጥ ጌታ ከመካከል ተቀመጠ:: ድንግል በቀኙ: ዮሐንስ በግራው
ሲቀመጡ: ሌሎች
ሐዋርያት ግራና ቀኝ ከበው ተቀመጡ:: ሲበላና ሲጠጣ
ድንገት የተደገሰው ምግብና መጠጥ አለቀ::
ደጋሾቹ በጭንቅ ላይ ሳሉም አይጠና ሆዷ ድንግል እመ ብርሃን የሆነውን አወቀች:: እንዴት አወቀች ቢሉ:- በጸጋ: አንድም 'ከልጅሽ አማልጂን' ብለው ቢለምኗት ነው ይሏል:: እመቤታችን በዚያ ጊዜ ወደ ልጇ ቀርባ ቸር ልጇን "ወይንኬ አልቦሙ-ወይኑኮ አልቆባቸዋል" አለችው
+ለጊዜው ወይኑም: ምግቡም ስላለቀባቸው እንዲህ አለች:: በምሥጢሩ ግን ወይን ያለችው ፍቅርን: ቅዱስ ቃሉንና ክቡር ደሙን ነው:: ጌታም ይመልሳል:- "ምንት ብየ ምስሌኪ ኦ ብእሲቶ: ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ-አንቺ ሆይ! (እናቴ ሆይ!)
ያልሺኚን አላደርግ ዘንድ ካንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ? ነገር
ግን ጊዜው ገና አልደረሰም ብየ ነው እንጂ" አላት::
ምክንያቱም ጌታ:-
የወይን ጋኖቹ እስኪያልቁ ይጠብቅ ነበር:: (አበረከተ ይሉታልና) አንድም ይሁዳ ወጥቶ ነበርና እርሱ እስኪመለስ ነው:: (እኔ ስወጣ ጠብቆ ተአምር ሠራ ብሎ ለክፋቱ ምክንያት እንዳያቀርብ) አንድም "ወይን (ቅዱስ ደሜን) የምሰጠው በቀራንዮ አንባ ነው" ሲል "ጊዜየ ገና ነው" ብሏታል:: አንዳንድ ልቡናቸው የጠፋ ወገኖቻችን ጌታ እመቤታችንን እንዳቃለላት (ሎቱ ስብሐት! ወላቲ ስብሐት!) አስመስለው ይናገራሉ:: ይህንን ስእንኅን ጌታ ባለጌዎቹ እነሱም አያደርጉት:: "አባትህንና እናትህን አክብር" (ዘጸ. 20) ያለ ጌታ እንዴት ለእናቱ ክብርን ይነፍጋል?ልቡና ይስጠን!
ወደ ጉዳያችን ስንመለስ መድኃኒታችን እንዲህ ሲል መለስላት:: ተግባብተዋልና እመ ብርሃን አሳላፊዎቹን "ኩሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ-የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው:: (ዮሐ. 2:5) ጌታም በ6ቱ ጋኖች ውሃ አስሞልቶ በተአምራት ወይን አደረጋቸው
+እንጀራውን ወጡን በየሥፍራው ሞላው:: ታላቅ ደስታም ሆነ:: የአሳላፊዎቹ አለቃም (ለአባታችን አብርሃም ምሳሌ ነው) ከወይኑ ጥፍጥና የተነሳ አደነቀ:: በዚህም የድንግል ማርያም አማላጅነት: የመድኃኒታችን ከሃሊነት ታወቀ: ተገለጠ
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ይህ ✝የህይወት መንገድ✝ የተሰኘ ቴሌግራም ቻናላችን
👉ምክሮችና የአባቶች ተግሳጾች
👉የተለያዩ የህይወት ትምህርቶች
👉የህይወት ችግሮችና መፍትሄዎች
👉መንፈሳዊ ግጥሞች
👉መንፈሳዊ ታሪኮች
👉የቮይስ ትምህርቶች
👉የቪድዮ ትምህርቶች
👉እለታዊ የብሩክ ንጋት ብሩህ ቀን መርሃግብሮች 👉መንፈሳዊ መዝሙሮችና የተለያዩ🔵መንፈሳዊ🔵 አገልግሎቶችን ያቀርባል።የአገልግሎቶቻችን ተካፋይ ለመሆን ይህንን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
@yehywetmenged
@yehywetmenged
@yehywetmenged
የዚህ ቻናል #እህት የሆነውን ✝ህይወት ቲዩብ✝የተሰኘውን ብዙ አገልግሎቶችን የምናቀርብበትን ቻናል ይመልከቱ።ከወደዱትም❤️ሰብስክራይብ❤️ በማድረግ ቤተሰባaችን ይሁኑ።
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
👉ምክሮችና የአባቶች ተግሳጾች
👉የተለያዩ የህይወት ትምህርቶች
👉የህይወት ችግሮችና መፍትሄዎች
👉መንፈሳዊ ግጥሞች
👉መንፈሳዊ ታሪኮች
👉የቮይስ ትምህርቶች
👉የቪድዮ ትምህርቶች
👉እለታዊ የብሩክ ንጋት ብሩህ ቀን መርሃግብሮች 👉መንፈሳዊ መዝሙሮችና የተለያዩ🔵መንፈሳዊ🔵 አገልግሎቶችን ያቀርባል።የአገልግሎቶቻችን ተካፋይ ለመሆን ይህንን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
@yehywetmenged
@yehywetmenged
@yehywetmenged
የዚህ ቻናል #እህት የሆነውን ✝ህይወት ቲዩብ✝የተሰኘውን ብዙ አገልግሎቶችን የምናቀርብበትን ቻናል ይመልከቱ።ከወደዱትም❤️ሰብስክራይብ❤️ በማድረግ ቤተሰባaችን ይሁኑ።
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
youtube.com/c/hiwottube
+ሜልኮል ግን በልቧ ናቀችው+
ሜልኮል ዳዊትን በልቧ ለምን ናቀችው? ለምንስ ዕርቃኑን ሆኖ በመዝለሉ ተገረመች? ለዚህ መልስ በሜልኮል ልብ የተናቀው ዳዊት መልስ አለው።
እግዚአብሔር የሚገለጥበት ታቦት በከተማው ሲገባ የተመለከተ ዳዊት በእስራኤላውያን ዘንድ ያለው ክብር አላሳሰበውም የንግስናውም ካባ አልያዘውም በደስታና በተመስጦ እየዘመረ ይዘል ነበር። መጎናጸፊያው ከመሬት ወድቆ እርቃኑን እስኪሆን ድረስ ዓለምን ለጥቂት ሰዓታት በተመስጦ ዘንግቶ ነበር።
ዳዊት ምን አይነት ተመስጦ ውስጥ ነበር? ደስታውስ ምን ያህል ቢሆን ነው የምድር ሹማምንተ መተው የማይፈልጉትን ክብር እስኪንቅ ድረስ ያዘለለው? የዳዊት ዝማሬና ዝላይ በፍጹም ከስጋዊ ስሜት የመነጨ ሳይሆን ነፍስ ስትደሰት የሚፈጠረ ተመስጦ ነው። ይደንቃል? ለታቦት ሊሰጥ የሚገባውን ክብር ዳዊት እየወደቀና እየተነሳ አስተማረን። የእግዚአብሔርን ታቦት ስትመለከቱ ዓለማዊ ክብራቹ ሊይዛቹ አይገባም የልባሳቹ ማማር እና መድመቅ ወደኋላ ይመልሳቹ ዘንድ የተገባ አይደለም የሚል ምክር ለገሰን።
በኤልሳቤጥ ማኅፀን የዘለለው ፅንስ ታቦት የተሰኘች የእመቤታችንን ድምፅ በሰማ ጊዜ ነበር። ፅንሱ ሰምቶ በስውር ሲዘል ዳዊት ደግሞ አይቶ በግልጥ ዘለለ። የሁለቱም መዝለል ምክንያት ግን ደስታ ነው። የእግዚአብሔር ታቦት በአደባባይ ሲወጣ ሐዘን የለም ለቅሶና ጸብ አይኖርም የሚኖረው "ደስታ" ብቻ ነው። ደስታችን ፍጹም ሲሆን ከጥግ ቆመው የሚስቁ ሜልኮሎች ትዝ እይሉንም።
ሜልኮል ከመስኮት ላይ ቆማ የታቦቱን መምጣት ሳይሆን ስትከታተል የቆየችው የዳዊትን መዝለልና መዘመር ነበር። ይህን በማድረጉ ከክብሩ የተዋረድ መስሎ ታያት። በዚህም ምክንያት በልቧ ናቀችው። ታቦቱ ተነስቶ ሕዝቡን ባርኮ ወደ ክብር ቦታው እስኪመለስ ድረስ ዳር ቆመው የልብስ ዓይነት ሚያማርጡ የሰዎችን እንቅስቃሴ የሚገመግሙ ከሚከብረው ታቦት ይልቅ ሰዎችን ለማመስገንም ይሁን ለመናቅ ልቦናቸውን ያዘጋጁ ሜልኮሎች አይጠፉም።
ምስጢር ሲሰወርብን እንዲ እንሆናለን። ለታቦት ከሚሰጠው ክብር በተጨማሪ በደስታ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ይፈለጋል። በፍጹም ደስታ ውስጥ ሆኖ ያከበረንን እግዚአብሔርን ከማመስገን ፈንታ ለጸብ የሚጋብዝ ንቀትና ስላቅ ስናበዛ በተመስጦ ያሉ ዳዊቶችን እንረብሻቸዋለን። ወይ አንደስት ወይ ደግሞ በታቦቱ መመጣት ለሚደሰቱት ሰዎች ምክንያት ላለመሆን አንታቀብም።
ዳዊት በፍጹም ተመስጦ እና ደስታ የተቀበለውን ታቦት ይዞ መሰዋዕትን አቅርቦ ሲመለስ ቀድሞውንም የዳዊት ምስጋና ከልቧ ያልገባው ሜልኮል"የእስራኤል ንጉስ በአገልጋዮቹ ሚስቶች ፊት በመገለጡ ምነኛ የተከበረ ነው" በማለት በነገር የሚወጋ ንግግር ተናገረች። ዳዊት ግን እንደዛ በማድረጉ አንድም ነገር የማፈር ስሜት አልተሰማውም በልበ ሙሉነት ድንቅ ቃላቶችን አወጣ እንዲህ አላት "በእግዚአብሔር ፊት ዘምሬአለሁ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ አለቃ እሆን ዘንድ ከአባትሽና ከቤቱ ሁሉ ይልቅ የመረጠኝ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት እጫወታለሁ እዘምራለሁም አሁንም እገለጣለሁ በዕይንሽ ፊትና እንዴት ከብረሕ ባልሽባቸው ሴቶች ልጆች ፊት የተናቅሁ እሆናለው" አላት
አሸማቀው እና ተሳልቀው ደስታህን ለሚቀሙ ሜልኮሎች ተብሎ የሚቀር ዝማሬ የለም። ለታቦት ክብር መስጠት ያልገባቸው በመስኮት ለሚያጮልቁ ሰዎች ሲባል የሚተው ምሰጋና የለም። መቋሚያና ጸናጽል ይዘን ከበሮ አንግበን ማመስገን ቢሳነን እንኳን በተፈጥሮ የተሰጠን የድምጽ መሳርያ ጭብጨባና በእልልታን ተጠቅመን የእግዚአብሔርን ታቦት እናከብራለን።
ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
4-5-2013
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ሜልኮል ዳዊትን በልቧ ለምን ናቀችው? ለምንስ ዕርቃኑን ሆኖ በመዝለሉ ተገረመች? ለዚህ መልስ በሜልኮል ልብ የተናቀው ዳዊት መልስ አለው።
እግዚአብሔር የሚገለጥበት ታቦት በከተማው ሲገባ የተመለከተ ዳዊት በእስራኤላውያን ዘንድ ያለው ክብር አላሳሰበውም የንግስናውም ካባ አልያዘውም በደስታና በተመስጦ እየዘመረ ይዘል ነበር። መጎናጸፊያው ከመሬት ወድቆ እርቃኑን እስኪሆን ድረስ ዓለምን ለጥቂት ሰዓታት በተመስጦ ዘንግቶ ነበር።
ዳዊት ምን አይነት ተመስጦ ውስጥ ነበር? ደስታውስ ምን ያህል ቢሆን ነው የምድር ሹማምንተ መተው የማይፈልጉትን ክብር እስኪንቅ ድረስ ያዘለለው? የዳዊት ዝማሬና ዝላይ በፍጹም ከስጋዊ ስሜት የመነጨ ሳይሆን ነፍስ ስትደሰት የሚፈጠረ ተመስጦ ነው። ይደንቃል? ለታቦት ሊሰጥ የሚገባውን ክብር ዳዊት እየወደቀና እየተነሳ አስተማረን። የእግዚአብሔርን ታቦት ስትመለከቱ ዓለማዊ ክብራቹ ሊይዛቹ አይገባም የልባሳቹ ማማር እና መድመቅ ወደኋላ ይመልሳቹ ዘንድ የተገባ አይደለም የሚል ምክር ለገሰን።
በኤልሳቤጥ ማኅፀን የዘለለው ፅንስ ታቦት የተሰኘች የእመቤታችንን ድምፅ በሰማ ጊዜ ነበር። ፅንሱ ሰምቶ በስውር ሲዘል ዳዊት ደግሞ አይቶ በግልጥ ዘለለ። የሁለቱም መዝለል ምክንያት ግን ደስታ ነው። የእግዚአብሔር ታቦት በአደባባይ ሲወጣ ሐዘን የለም ለቅሶና ጸብ አይኖርም የሚኖረው "ደስታ" ብቻ ነው። ደስታችን ፍጹም ሲሆን ከጥግ ቆመው የሚስቁ ሜልኮሎች ትዝ እይሉንም።
ሜልኮል ከመስኮት ላይ ቆማ የታቦቱን መምጣት ሳይሆን ስትከታተል የቆየችው የዳዊትን መዝለልና መዘመር ነበር። ይህን በማድረጉ ከክብሩ የተዋረድ መስሎ ታያት። በዚህም ምክንያት በልቧ ናቀችው። ታቦቱ ተነስቶ ሕዝቡን ባርኮ ወደ ክብር ቦታው እስኪመለስ ድረስ ዳር ቆመው የልብስ ዓይነት ሚያማርጡ የሰዎችን እንቅስቃሴ የሚገመግሙ ከሚከብረው ታቦት ይልቅ ሰዎችን ለማመስገንም ይሁን ለመናቅ ልቦናቸውን ያዘጋጁ ሜልኮሎች አይጠፉም።
ምስጢር ሲሰወርብን እንዲ እንሆናለን። ለታቦት ከሚሰጠው ክብር በተጨማሪ በደስታ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ይፈለጋል። በፍጹም ደስታ ውስጥ ሆኖ ያከበረንን እግዚአብሔርን ከማመስገን ፈንታ ለጸብ የሚጋብዝ ንቀትና ስላቅ ስናበዛ በተመስጦ ያሉ ዳዊቶችን እንረብሻቸዋለን። ወይ አንደስት ወይ ደግሞ በታቦቱ መመጣት ለሚደሰቱት ሰዎች ምክንያት ላለመሆን አንታቀብም።
ዳዊት በፍጹም ተመስጦ እና ደስታ የተቀበለውን ታቦት ይዞ መሰዋዕትን አቅርቦ ሲመለስ ቀድሞውንም የዳዊት ምስጋና ከልቧ ያልገባው ሜልኮል"የእስራኤል ንጉስ በአገልጋዮቹ ሚስቶች ፊት በመገለጡ ምነኛ የተከበረ ነው" በማለት በነገር የሚወጋ ንግግር ተናገረች። ዳዊት ግን እንደዛ በማድረጉ አንድም ነገር የማፈር ስሜት አልተሰማውም በልበ ሙሉነት ድንቅ ቃላቶችን አወጣ እንዲህ አላት "በእግዚአብሔር ፊት ዘምሬአለሁ በእግዚአብሔር ሕዝብ በእስራኤል ላይ አለቃ እሆን ዘንድ ከአባትሽና ከቤቱ ሁሉ ይልቅ የመረጠኝ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት እጫወታለሁ እዘምራለሁም አሁንም እገለጣለሁ በዕይንሽ ፊትና እንዴት ከብረሕ ባልሽባቸው ሴቶች ልጆች ፊት የተናቅሁ እሆናለው" አላት
አሸማቀው እና ተሳልቀው ደስታህን ለሚቀሙ ሜልኮሎች ተብሎ የሚቀር ዝማሬ የለም። ለታቦት ክብር መስጠት ያልገባቸው በመስኮት ለሚያጮልቁ ሰዎች ሲባል የሚተው ምሰጋና የለም። መቋሚያና ጸናጽል ይዘን ከበሮ አንግበን ማመስገን ቢሳነን እንኳን በተፈጥሮ የተሰጠን የድምጽ መሳርያ ጭብጨባና በእልልታን ተጠቅመን የእግዚአብሔርን ታቦት እናከብራለን።
ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
4-5-2013
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21