መንፈሳዊ ህይወት
4.02K subscribers
437 photos
5 videos
8 files
62 links
✟✟✟በስመአብ ወወልድ በመንፈስ ቅድስ አሀድ አምላክ አሜን ✞✞✞
በዚህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ ስርአት የጠበቁ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ይጠቅሙናል ያስተምሩናል የምንላቸውን መንፈሳዊ
ትምህርቶች ብሒሎች ምክሮች እናስተላልፋለን።
ለሌሎች ሼር በማድረግ ቻናሉን ያጋሩ ✟✟✟

መንፈሳዊ ህይወት (ሰው)
✍️✍️ ሀሳብ ወይም አስተያየት ;👇👇

https://t.me/Ortodoxe21 በዚ ይላኩልን
Download Telegram
መልካም ዕለተ ሰንበት 🙏🙏🙏


ወዳጄ ኾይ!

የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ። አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትኽ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልኽ ጠላት አለኽና ነገር ግን ወድቀኽ አትቅር፡፡

አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ኼዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትኽ ዲያብሎስ ቢያቆስልኽ ማንም አይወቅስኽም መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡

የምትወቀሰው ለቁስልኽ መድኃኒት ማድረግኽን ችላ ያልክ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይኽ ከላይ የነገርኩኽ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይኼዳል ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡

አንተም ከወደቅኽበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትኽ ዲያብሎስን ድል አድርገኽ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡

ስለዚኽ በርታና ተነሥ ዘግይቻለኹ ብለኽ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አኹንም መጀመር ትችላለኽና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

መልካም ዕለተ ሰንበት🙏

💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
1
እንካን ለደስታ አብሳሪው ገናናው መልአክ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳቹ 🙏🙏🙏
ቅዱስ ገብርኤል

ታህሳስ 19 ቀን በዚህ ቀን ሰለስቱ ደቂቅ "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል" ያሉበት ዕለትና ቅዱስ ገብርኤል ከእሣት ያዳቸው ዕለት መታሰቢያ በዓል ነው። ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ነገሩ እንዲህ ነው። ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር ሰዎች የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የነበሩት ወጣቶች ሥም አናንያ (ሲድራቅ) ፤ አዛርያ (ሚሣቅ) ፤ ሚሣኤል (አብድናጎ) ነበሩ። ት/ዳንኤል 3፡1-30 ታሪኩ እንደሚግረን ንጉስ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሣት ውስጥ ይጣላል ብሎ አወጀ። በዚህ መካከል ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻል?" ባላቸው ጊዜ የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም እንኳን አንተ ለመታመልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት ። በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሣት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሣቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠልስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው ። በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል እንዲያውም የአማልክትን ልጆች ይመስላል " አለ። የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ተብሎ የነበረው "ጉልበት ሁሉ ለሰልስቱ ደቂቅ አምላክ ይስገድ ይንበርከክ" ተባለ ይህን ሁሉ ታህሳስ 19 ቀን ሆነ በዚህም ምክንያት በታላቅ ደስታ እናከብረዋለን።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃው ረድየት በረከቱ አይለየን ።
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ጾም ስጦታ ነው:- የጾምን ጥቅሞች እያወቅን ስንመጣ ጾም የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን እንረዳለን፡፡ አዎን፤ጾም እንዲሁ ከአሥሩ ትእዛዛት እንደአንድ ትእዛዝ የሚቆጠር ብቻ ሳይሆን መለኮታዊ ስጦታ፣ጸጋ እና በረከት ነው፡፡ እኛን ሥጋና ነፍስ አድርጎ የፈጠረን ለመንፈሳዊ ሕይወታችን የሚጠቅመው ጾም እንደሚያስፈልገን የሚያውቀው ለመንፈሳዊ ዕድገታችንና ለዘላለማዊነታችን የሚያስብልን እግዚአብሔር ጾምን ተግባራዊ የምናደርግበትን እውቀት አድሎናል፡፡ እሱም እንደ ቸር አባትና እንደ ጠቢብ መምህር ጾምን ለእኛ አዞልናል፡፡ በራሱ ኃይልና እውቀት የሚተማመን ሰው በራሱ ይመካል፤ ድካሙን የተገነዘበ ሰው ግን ችግር ሲገጥመው ልመናውን ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርበው በጾም ውስጥ ሆኖ ነው፡፡እግዚአብሔረ ለችግሮቻችን ሁሉ የደርስ ዘንድ ጾም ትክክለኛው ጊዜያችን ነው፡፡ ይህ ጊዜ የተሰበረ ልብ ወደ እግዚአብሔር የሚጣራበት እግዚአብሔር ደግሞ የሚሰማበት ጊዜ ነው፡፡ በእውነተኛ ጾም ውሰጥ ሰው የእግዚአብሔርን ልብ ማራራት ይችላል፡፡ አንድ ቅዱስ መነኩሴ "ፀሐይ ምግብ ስበላ ከተመለከተችኝ እንሆ ሠላሳ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡" በማለት ተናግረዋል፡፡ እስክንድርያዊው ቅድስ መርቆርዮስ ምግብ ይበላ የነበረው በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነበር፡፡ሰው በተራበ ጊዜ የሚያቀርበው ልመና(ጸሎት) ይበልጥ ተሰሚነት አለው፡፡ሆድህ በምግብ ተሞልቶ ከምትጸልየው ሰዓታት ከሚወስድ ፀሎት ይልቅ በረሀብ ውስጥ ሆነህ የምታቀርበው የሁለት ደቂቃ ጸሎት ጥልቀት፣ ተሰሚነትና ተቀባይነት አለው፡፡

አቡ ሺኖዳ ሣልሳዊ

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
1
ልብህ ሞልቷል

አንድ ወጣት ወደ አንድ መነኩሴ ዘንድ ይሄድና ክርስትናን ማወቅ እፈልጋለው ስለ ክርስትና ንገሩኝ አላቸው ። ና ልጄ ውስጥ ሻይ እየጠጣን እናውራ ብለው ወደ ባዕታቸው ይዘውት ገቡ ።ከዛ ማንቆርቆሪያቸውን ጥደው ሻዩ እስኪፈላ መጠበቅ ጀመሩ ። ልጁም በሚገርም የወሬ ፍጥነት አባ ክርስትና እንዲ ነው አይደል ፡አባ ክርስትና እንደዛ ነው አይደል ? ሰዎች እኮ ነግረውኛል እያለ ከሰዎች የሰማውን ይቀባጥራል

መነኩሴውም ዝም ብለው ሲሰሙት ቆዩና ሻዩ ሲፈላ ብርጭቆ አምጥተው ይቀዱለት ጀመረ ። ብርጭቆው ሞልቶ እየፈሰሰም ዝም ብለው ይቀዳሉ ። ከዛ ልጁም አንተ መነኩሴ ያምሀል እንዴ ? ብርጭቆውኮ ሞልቷል ። አንተ ለምትጨምርበት ሻይ ቦታ የለውም አላቸው ። መነኩሴውም አየህ ልጄ አንተም እንደዚ ብርጭቆ ነህ ። ስለ ክርስትና ማወቅ ትፈልጋለህ ነገር ግን ልብህ ሌሎች በነገሩህ አሉባልታ ተሞልቷል እኔ የምነግርህን ነገር የምትቀበልበት ቦታ በልብህ ውስጥ የለም

ብነግርህም ታፈሰዋለህ ። ስለዚህ አሁን ሂድ ልብህ ባዶ ሲሆን ተመልሰህ ና ያኔ እነግርሃለው አሉት። እኛስ ዛሬ ልባችንን የሞላው ምንድነው ? ፍቅር ? ሰላም ? መቻቻል ? ታምኝነት ፣ ህብረት አንድነት ነው ወይስ አስቀድሞ ልባችን በተንኮል ፣ በሟርት ፣ በቅናት፣በሴሰኝነት ፣ በዘረኝነትና በጎጠኝነት ስለተሞላ ለመልካም ነገሮች ቦታ የለውም ? እስቲ እራሳችንን እንፈትሽ ልባችንን ሞልቶት እየፈሰሰ ያለው ምንድነው ?

💚 @linkortodoxe21 💚
💛 @linkortodoxe21💛
❤️ @linkortodoxe21❤️
"ነገ ለአንተ የተሻለ ነው"
ያለህበት ዛሬ ለአንተ እጅግ አሰልቺ ከሆነ ለነገህ ኑር። በዚህ ነገህ ዉስጥ አንተን ለማረጋጋት የእግዚአብሔር እጅ ወደ አንተ መዘርጋቱን ተመልከት፡፡ ይህንን ካደረግህ በዚህ ነገህ ዉስጥ ለችግሮችህ ብዙ መፍትሔዎችን መመልከት ትችላለህ። የአንተ ዛሬ ጨለማ ከሆነ ነገህ በፊትህ የብርሃን መስኮቶችን ይከፈትልሀል ፡፡
ቅዱሳን ነገ ለሚያገኙት የዘለዓለም ህይወት ስለ ኖሩ ተስፋቸዉን ሁሉ በዚህ ነገ ላይ ጥለዉት ነበር። ሳዖል ባሳደደዉ ጊዜ ነብዩ ዳዊት የኖረዉ ለነገዉ ነዉ። ነብዩ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ዉስጥ ሳለ የኖረዉም ለነገዉ ነዉ። ቅዱስ ዮሴፍ በወኅኒ ሳለ አባቱ ቅዱስ ያዕቆብ ደግሞ በወንድሙ በዔሳዉ በተሳደደ ጊዜ የኖሩት ለነጋቸዉ ነበር፤ ያዕቆብም ከመሰደድ ዮሴፍም ከግዞት ህይወት እንደሚወጡ በእግዚአብሔር ታምነዋልና።
ነገሮች ለአንተ አስቸጋሪ ከሆኑ ለራስህ ነገ መፍትሔ ይገኝላቸዋል ብለህ ንገረዉ። ከዚህም በኋላ ለዚህ ነገህ በፈገግታና በደስታ ኑር!!
(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ)

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
ኤፌሶን 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤
⁵ አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤
👉@linkortodoxe21
እንካን ለጻድቁ ተክለ ሀይማኖት አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳቹ 🌿🌿🌿🌱🌱🌱🍀🍀🍀🌿🌿🌿🌱🌱🌱🍀🌿🌱🍀🍀🌿🌿🌿🌱🌱🌱🌿🌿
እሱ ማነው???


ሀይማኖቱን ከከሀዲ ዮዲት ጉዲት መሳይ
የሚከላከለው መንጋን ተመለስ ባይ
ማርያን- ጠንቋዩን ለአምላክ ያስገዛ
የወንጌል ገበሬ የኢትዮጵያ መዓዛ
እኮ እርሱ ማነው??
የትሩፋት መምህር የእግዚአርያ በረከት
የክርስቶስ ወታደር የብዙዎች አባት
ኢትዮጵያን ያበራት በወንጌል አዝመራ
ባለ ብዙ ሰብል በመኸር ጎተራ
በሰባኬ ክረምት በተዓምራት ፀደይ
የበረከት አባት በፍሬው የሚለይ
እኮ እርሱ ማነው??
ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ
ለምስጋና ሚቆም ከመንበረ ስሉስ
እንደ መላእክቱ ክንፍ የተሸለመ
እርሱስ ባህታዊው ተክለ ሃይማኖት ነው፡፡
"" እንኳን ለአባታችን ለፃዲቁ ለአቡነ ተክለሀይማኖት በዓል በሠላም አደረሳችሁ፡፡""
✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤

✤✤✤✤✤✤✞✤✤✤✤✤✤
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
አምላክ ለምን ሰው ሆነ ????
* ለአዳም የገባለት ቃል ኪዳን ይፈፀም ዘንድ
* የዓለምን ሕዝብ ከኃጢአት ለማንፃት
* የዓለምን ሕዝብ ከጽኑ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት
* ከእኛ በላይ ማንም የለም ይሉ ለነበሩ ሁሉ የሁሉም የበላይ አምላክና ጌታ
መኖሩን ያውቁ ዘንድ ኢየሱስ ሰው ሆኖ ተገለጠ።
* አምላክ አካል የለውም ይሉ ለነበሩ አካላዊነቱን ይገልጽ ዘንድ ወልድ
በተዋህዶ ሰው በመሆን ተገለጠ።
* ምድር ለመልካም ተፈጥራ ሳለ ስለ ሰው ኃጢአት በመረገሟ ምክንያት
ምድርን ሊቀድሳት፣ሊባርካት እርግማኗን በንጹህ ደሙ ያጠፋላት ዘንድ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆነ። ኢሳ. 45፥18 ዘፍ. 3፥17
* እውነተኛ ሠላምና እርቅን ለመስጠት
* ከዘላለም ሞት ለማዳን 1ኛ. ዮሐ.5፥20
* የአለም ብርሃን ለመሆን ዮሐ 8፥12
* እውነት የሆነው የሕይወት መንገድ ለጠፋባቸው ሰዎች ኢየሱስ
እውነትም፣መንገድም፣ሕይወትም ሆኖ ተገለጠ።ዮሐ 14፥6
* የሰው ልጅ በትዕዛዝ የተሰጠውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ባለመቻሉ ምክንያት
ሕግን ሠርቶ ፈጽሞ ያሳየው የለምና እግዚአብሔር በተዋህዶ ተገልጦ ህግን
ፈጽሞ ያሳየን ዘንድ ሰው ሆነ። ማቴ. 5፥17

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
በጥንት ዘመን አንድ ንጉሥ በሁለት ሰዎች ላይ ሞት ፈርዶ ሲያበቃ ለመጨረሻ ጊዜ የምትናገሩት ሐሳብ ካለ ይዛችሁት ከምትሞቱ ሐሳባችሁን ግለጹ አላቸው። አንደኛው የሞት ፍርዱ ላይነሳልኝ ምን አደከመኝ ብሎ ያስብና ምንም የምናገረው ነገር የለኝም የለኝም ይላል።

ሌላኛው ግን ዝም ብዬ ከምሞት ብሎ ያስብና አንድ መላ ያመጣል። ንጉሱ አንድ በጣም የሚወዳት ምርጥ ፈረስ እንዳላቸው ስለሚያውቅ "ንጉስ ሆይ ሺ ዓመት ይንገሡ! እኔ የሚወዱትን ፈረስዎ ለአንድ ዓመት መብረር ላለማምውደ እችላለሁ" ይህ የሚሆነው ግን የአንድ ዓመት ዕድሜ ከተሰጠኝ ብቻ ነው ይላል።

ንጉሡም አባባሉ ቢያስገርመውም "የሚበር ፈረስ ያለው በዓለም ላይ ብቸኛ ንጉሥ" መባሉን ውስጡ ስለወደደው በነገሩ ተስማምቶ የአንድ ዓመት ዕድሜ እንዲሰጠው ፈቀደ ።

ከችሎቱ መልስ ያ ዝም ያለው ባልንጀራው በዚህኛው ላይ ስላቅ ተናገረበት "ወፈፍ ያረግሃል ልበል? አሁን በየት ሀገር ነው ፈረስ የሚበረው? አንድ ዓመት ረዥም መስሎህ ነው ይህን የማይሆን ነገር የምትናገረው? ምናለ ጣርህን ባታበዛው" አለው።

ብልሁ ሰው ግን ተኩራርቶ እኔ እንዳንተ ዝም ብዬ አልሞትም ይህን ሃሳብ ሳቀርብ ነጻ ለመውጣት አራት አማራጮች አሉኝ እነርሱም፡-
፩ኛ. #በዚህ #አንድ #ዓመት #ንጉስ #ሊሞቱ #ይችላሉ

፪ኛ. #እኔ #እራሴ #ልሞት #እችላለሁ

፫ኛ. #ፈረሱ #ሊሞት #ይችላል

፬ኛ. #ማን #ያውቃል #ምንአልባት #ፈረሱን #መብረር #አስተምረው #ይሆናል። አለው ይባላል።
እኛም ዝም ብለን ከነኃጥያታችን ልንሞት አይገባም ንስሐ ገብተን ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ነጻ ወጥተን ብንሞት ይሻለናል

@linkortodoxe21
@linkortodoxe21
@linkortodoxe21