ቅንጭብጭብ
7.25K subscribers
410 photos
9 videos
3 files
498 links
ካየሁት 👀 አስገራሚ
ከሠማሁት 👂 መሣጭ
ካነበብኩት 📖 አስተማሪ
ካሠብኩት ♀🅱 ልዩ ልዩ

እነሆ #ቅንጫቢ

ፅሁፎቻችሁን በ @bcrAzykid አካፍሉን።

ለማንኛውም አስተያየት ጥያቄ እና ጥቆማ @bcrAzykid ይጠቀሙ።
Download Telegram
ከ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰው...
@kinchebchabi
ቅንጭብጭብ
ከ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰው... @kinchebchabi
ከፈረንጆቹ 1962 ጀምሮ እንቅልፍ ያልተኛው ሰውዬ በቬትናም ትንሽዬ ከተማ ውስጥ:
በሰላም
በጤና
ከሰዎችም ሳይጣላ
ኡ ኡ ኡ ኡ እያለ ሳይጮህ
ሳያብድ
ሳይደባደብ
ስቅስቅ ብሎ ሳያለቅስ
ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ሳያስቸግር
ሳያቅለሸልሸው
ሳያጥወለውለው
ነገር አለሙ ሳይጠፋበት
ኧረ ወየው እያለ ሳይጮህ

ጭራሽ ትዳር ኖሮት ልጆች ወልዶ ፤ ከአንድም ሦስት ቤት በእጁ ገንብቶ ፤ በቀን ሁለት ስራ እየሰራ አለ ይኖራል።

እንዴት እንደሆነ እንጃ የሆነ ቀን ለታ ነቃ ነቃ ነቃ! በቃ እንቅልፉ ብን ብሎ ጠፋ!

ጥቂት እየተመገበ፤ ሲጃራውን እየጠጣ፤ ቤቱ የሚጠምቀውን የሩዝ አረቄ እየጠጣ ... አለ በሰላም በጤና

መቼ እንደተኛህ ትዝ ይልሃል ሲሉት: ድሮ ነው ሩቅ ጊዜ እያለ
ሚስቱን: ሲተኛ አይተሽው ታውቂያለሽ ስትባል Never እያለች
ልጁን: አንተስ ትተኛለህ ሲሉት "በሚገባ" እያለ

በዙሪያው ያሉ መንደርተኞች በሙሉ መሸ ደና ደሩ ሲሉ እሱግን ይኸው ለ 62 አመታት ቁልጭ እንዳለ አለ🧐

እናንተስ እንቅልፍ ሳትተኙ ኑሩ ብትባሉ የሚሆን ይመሥላችኋልን?

እንቅልፍ ህይወት ነው

🎶 ኦሆኦኦ መለስ አርገው ጋሜ
አይዞህ ወንድሜ🎶 ማለት ይሄኔ ነው 🧐

ሰውየው ግን የሚፈልገው ነገር ... መተኛት ነው አለ።
እውነቱን ነው .... በዚች አለም ላይ ከእንቅልፍ በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ?

ብቻ: በእውነት! ታሪኩ ውስብስብ ነው።

join us
@kinchebchabi
ይግረማችሁ - የምትተኙበት ፍራሽ ምን ይመስላል?

ይመቻል? ይቆረቁራል? ወገቤን አንገቴን አስብሏችኋል? በሉ ስለዚህ ፍራሽ አንብቡ...
ቅንጭብጭብ
ይግረማችሁ - የምትተኙበት ፍራሽ ምን ይመስላል? ይመቻል? ይቆረቁራል? ወገቤን አንገቴን አስብሏችኋል? በሉ ስለዚህ ፍራሽ አንብቡ...
የምናወራው ስለ ፍራሽ ነው ለማለት ያስቸግራል ።

DeRUCCI Smart ' T 11 - Pro  ይባላል  ።  ይህ በ 8,250. ዶላር ለገበያ የቀረበው ስማርት ፍራሽ ከተገጠሙለት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ   ቴክኖሎጂዎች መሀል . ...

በዚህ ፍራሽ ላይ የተኛ ሰው እንቅልፍ እንደተኛና እንዳልተኛ ፡ ፍራሹ በደንብ ያውቃል ። እና እንቅልፍ ካልወሰደው ፡ የመኝታ ቤቱን ብርሀን ቀስ እያለ ይቀንስና ለተኛው ሰው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ቅርፁን ለዋውጦ ይበልጥ ምቹ ሆኖ እንቅልፍን ለመጋበዝ ይሞክራል ።

ሰውየው በእንቅልፍ ሰአት ሙዚቃዎችን የመስማት ልምድ እንዳለው ፡ ተደርጎ ፕሮግራም ከተደረገ ፡ ከስለስ ያለ በመሳሪያ የተቀነባበረ ሙዚቃ በትንሹ ይከፍትለታል ።
እና ቀስ እያለ ፡ ማሳጅ እንደማድረግ አይነት በመጠኑ እየተንቀሳቀሰ ሰውየውን ለማስተኛት ይሞክራል ።
ከዚህ ሁሉ በኋላ ሰውየው እንቅልፍ ከተኛ ፡ የተከፈተውን ለስላሳ ክላሲካል ሙዚቃ ይዘጋና  የመኝታ ቤቱን መብራት ያጠፋል ።
.......
የዚህ ፍራሽ ስራ  ይህ ብቻ አይደለም ፡ ሰውየው እንቅልፍ ከተኛ በኋላም ፡ የልብ ምቱን ፡ የደም ዝውውሩን ፡ የሰውነቱን ሙቀት እና አጠቃላይ የጤናውን  ሁኔታ እየተከታተለ ይመዘግባል ።
.......
በዚህ አልጋ ላይ የተኛው ሰው ፡ ሰውነቱ ላይ ያልተለመደ አይነት ትኩሳት እንዳለው ፍራሹ  ካስተዋለ ፡ በተገጠመለት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አማካኝነት ፡ የትኩሳቱን ሁኔታ መዝግቦ .........
ማታ ስትተኛ ሙቀትህ ልክ አልነበረም ፡ ትኩሳት አለህ ፡  ሀኪም ቼክ ማድረግ ይኖርብሃል የሚል ቴክስት ጠዋት ወደሰውየው ስልክ ይልካል ።

......

ይህ የሚሆነው የሰውየው የጤና ሁኔታ  ለክፉ የማይሰጥ ከሆነ ነው ። ነገር ግን ሰውየው በተኛበት ወቅት የአተነፋፈስና የሰውነቱ ሙቀት ወይም የልብ ምቱ  ኖርማል ካልሆነና ሰውየው በድንገት ከታመመ ፡ ይህ ስማርት ፍራሽ ፡ ከሰውየው ስልክ ጋር ባለው የኢንተርኔት ግንኙነት አማካኝነት ፡ ወዲያውኑ ለድንገተኛ ህመም ተብሎ ወደተመዘገበው የህክምና ተቋም ወይም ሀኪም ጋር ስልክ ደውሎ ፡ Mr.. እንትና. .  በድንገተኛ ህመም ላይ ስለሆነ ቶሎ ድረሱለት ሲል ይደውላል ። ቴክስት ያደርጋል ።
....
ሰላም ከሆነና ሆኖም ሰውየው እያንኮራፋ ከሆነ ፡ በሚያንኮራፋው ሰው በኩል ብቻ ያለውን  የፍራሽ ክፍል ቅርፁን በመቀየር፡ ሰውየው  አስተኛኘቱን እንዲቀይርና ትራሱን በማስተካከል  አተነፋፈሱ ኖርማል እንዲሆን  ያደርጋል ።
.....
ለሊት ላይ የአየር ንብረቱ ተለውጦ ብርድ ከመጣ ፡ ይህ ፍራሽ ወደ AC ው መልእክት በመላክ ክፍሉ እንዲሞቅ ያደርጋል ። በተቃራኒው ሙቀት ከሆነም ክፍሉ እንዲቀዘቅዝ ያደርጋል ።

... ለሊቱ በዚህ መልኩ አልፎ ሲነጋ ፡ ሰውየው ከእንቅልፍ መንቃት ያለበት ሰአት ላይ ፡ እንደተለመዱት አላርሞች ድምፅ በመልቀቅ አይረብሽም ። ይህ ፍራሽ ጨዋ ነው ።
ከዛ ይልቅ ሰውየውን የሚቀሰቅሰው ፡ የክፍሉን ብርሀን በመጨመር እና በተወሰነ መልኩ ቀስ እያለ በመንቀሳቀስ እያባበለ ነው  ።
ይህን ከማድረጉ በፊት ግን ፡ ወደቡና ማፍያው ማሽን መልእክት በመላክ ፡ ቡና እንዲፈላ ያዛል ።
......
ማታ ሰውየው ጥሩ እንቅልፍ እንዳልተኛ ካስተዋለ ፡ ሲነጋ በሰውየው ስልክ ላይ ፡ ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት የሚያስችሉ ጠቃሚ ምክሮችን ይልካል ።
.............
ሆኖም  የሰላማዊ እንቅልፍ ጉዳይ  በምቹ ፍራሽ ላይ ከመተኛት ጋራ የተያያዘ  ባለመሆኑ እዚህ ላይ ተኝተውም  ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሊቸግር ይችላልና , ይህን መሰል መኝታ ሳያስፈልገን ስለምንተኛው  ስለ ጥሩው እንቅልፋችን እናመስግን ። ቴክኖሎጂው ግን እዚህ ደርሷል ።
© ዋስይሁን

በአብሮነት እንቆይ
t.me/kinchebchabi
''.....ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው... ሰው ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው ... ...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ...ነው ። በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው ። መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ።እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ናየምንኮራበት?......'''''

አለማየሁ ገላጋይ

በአብሮነት እንቆይ
t.me/kinchebchabi
ሳንዲ ፒርስ...
ቅንጭብጭብ
ሳንዲ ፒርስ...
ህይወት ለሳንዲ ፒርስ ፡ ደስ ትላለች. .. ሳንዲ በችካጎ ከተማ ከሚገኝ አንድ ባንክ ውስጥ ትሰራለች. .እናም እንደተለመደው በከተማዋ ዳርቻ ወደሚገኘው ቤቷ በማምራት ላይ ሳለች. .. ኩርቲስ ጃክሰንን ከርቀት ተመለከተችው. ..
..................
በዚህ ጎዳና ላይ አዘውትሮ የሚመላለስ ሰው ፡ ኩርቲስ ጃክሰንን ያውቀዋል ።
ይህ ሰው ለአመታት በዚህ ጎዳና ላይ አዘውትሮ በሚቀመጥበት ቦታ ላይ ሆኖ ፡ የሰወችን ደግነት ይጠባበቃል ። ኑሮው በሰወች ልግስና ላይ የተመሰረተ ነው ። እናም ዛሬም እንደተለመደው " ቤት አልባ ነኝ እርዱኝ " የሚል ፅሁፍ ደረቱ ላይ አድርጎ መብራት ይዟቸው የቆሙ ሰወችን እየለመነ ነው ።
.............
ሳንዲ ፒርስ ይሄ ጥቁር አሜሪካዊ ያሳዝናታል ፡ እናም አቅሟ በፈቀደ መጠን ሁሌም ትረዳዋለች ፡ ጥቂት ደቂቃ ወስዳም ታወራዋለች ፡ ይህ ለአንድ የጎዳና ተዳዳሪ ሰው ትልቅ ነገር ነበር ። እናም ዛሬ ፡ መብራት የያዛቸውን ሰወች ለምኖ ፡ ወደዘወትር ቦታው ሲመለስ ፡ ያችን ደግ ሴት ቆማ ስትጠብቀው ተመለከተ. . ሃይ ሳንዲ እንዴት ነሽ ፡ ልጅሽ ደህና ነው አላት ፡ የአስር አመት ልጅ እንዳላት ነግራዋለች እናም ሁሌ እሷን ሲያገኝ ይህንን ይጠይቃታል ።
.........
ሳንዲ ፒርስ ሁሉም ሰላም እንደሆነ ነግራው ፡ ህይወት አንድ ቀን መልካም ይሆናልና ተስፋ እንዳይቆርጥ አፅናንታው ፡ ጥቂት ብሮች ሰጥታው ሄደች ።
............
ኩርቲስ ጃክሰን በዚህች ሴት ደግነት ሁሌ ይገረማል ፡ ለሱ ይህች ሴት ዝም ብሎ ሳንቲም ሰጥተውት እንደሚያልፉት አይነት አይደለችም ፡ ፈጣሪ እንድታፅናናው የላከለት እህቱ ትመስለዋለች. . እናም በሳምንት የተወሰነ ጊዜ መጥታ ሰላም ብላው ስትሄድ በህይወት ላይ ተስፋ ያደርጋል ።
................
ሰሞኑን ግን ይህች መልካም ሴት ወደሱ መጥታ አታውቅም ፡ ቢያንስ በሳምንት አንዴ እንኳን ትመጣ የነበረችው ሳንዲ ፒርስ በዛ ጎዳና ማለፍ ከተወች ፡ አንድ ወር ሆናት. ..,በዚህ ጊዜ ኩርቲስ ጃክሰን አንድ ነገር አሰበና ፡ ወደምትሰራበት ባንክ ሄዶ ጠየቀ ። ለአንድ ወር ያህል ገብታ ስራ ገብታ እንደማታውቅ ነገሩት ።
.............
የጎዳና ተዳዳሪው ጃክሰን ይህን ሲሰማ በጣም አዘነ ፡ አዝኖ ብቻ አልተወም ፡ እኖርበታለሁ ወዳለችው ወደከተማዋ ዳርቻ ያሉ መንደሮች ሄዶ ለመፈለግ ወደዚያው ተጓዘ ።

..............
ኩርቲስ ጃክሰን ከብዙ ፍለጋ በኋላ ፡ የሳንዲ ፒርስን መኖሪያ ቤት አገኘ ፡ ነገር ግን በውስጡ ማንም አልነበረም ። ቤቱ በራፍ ላይ የሚከራይ የሚል ፅሁፍ ተለጥፎ ጭር ብሏል ። ያቺ ደግነቷን ሳትነፍግ ትረዳው የነበረችው ሴት ከነልጇ ቤቱን ለቀው ሄደዋል ።

............
ምን እንደተፈጠረ ማወቅ ፈልጎ አንድ ጎረቤቷን ጠየቀ
ሳንዲ ፒርስ ከአንድ ወር በፊት በማታውቀው ሁኔታ ከስራዋ እንደተባረረች ፡ ለተወሰነ ጊዜም ፡ በአቅራቢያ በሚገኝ ሆቴል ክፍል እየተከራየች መቆየቷንና ፡ ያላትን ጥቂት ገንዘብ ጨርሳ የሆቴል መክፈል ሲያቅታት ፡ ከአስር አመት ልጇ ጋር መኪናዋ ውስጥ መኖር እንደጀመረች ነገሩት ።
.........
የጎዳና ተዳዳሪው ኩርቲስ ጃክሰን ይህን ነገር እንደሰማ ፡ መኪናዋን አቁማ ወደምትኖርበት ቦታ ሄደ ፡ እንዳሰበው ፡ የ39 አመቷ ፡የቀድሞ የባንክ ሰራተኛ ከነልጇ መኪና ውስጥ ሆና ፡ ከሰወች ጋር ስትነጋገር ደረሰ ፡ ሰወቹ ከማህበራዊ አገልግሎት የመጡ ደንብ አስከባሪዎች ነበሩ ። እናም ከ10 አመት ልጇ ጋር መኪና ውስጥ መኖር እንደማትችል በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ቢሰጧትም ፡ መተው ስላልቻለች ፡ መንግስት ልጇን በሃይል ነጥቆ ፡ ወደህጻናት ማሳደጊያ ወስዶ እንደሚያሳድገው ለመጨረሻ ጊዜ እያስጠነቀቋት ነበር ።

..............
ኩርቲስ ጃክሰን ይህን ሲሰማ አዘነ ፡ ሰወቹ ጥለዋት እንደሄዱም ቀርቦ ሰላም አላት ፡ ሳንዲ ፒርስ ፡ ይህ ሰው እሷን ፍለጋ መምጣቱን ስትሰማ አለቀሰች ፡ ህይወት እንደጨለመባት ዳግም እዚህ ብትገኝ መንግስት ልጇን እንደሚነጥቃት ነገረችው ። ኩርቲስ ይህችን ህይወት ፊቷን ያዞረችባትን ስታጽናናው ፡ በቻለችው መጠን ስትረዳው የነበረችውን ሴት በተራው ማፅናናት ያዘ ።
............

ከዚያም ፡ ታርፍበት ወደነበረው ሆቴል እንድትመለስ ፡ ክፍያውንም እሱ እንደሚችልላት ነገራት ፡ ሳንዲ ይህንን ስትሰማ ከዚህ ሰው ላይ የሆቴል መውሰድ ቢከብዳትም ፡ ልጇ ከሷ ጋር እንዲኖር ለማድረግ ያላት ብቸኛ ምርጫ በመሆኑ የኩርቲስን ሃሳብ ተቀብላ ፡ ታርፍበት ወደነበረው ሆቴል አመራች ፡ኩርቲስ ለምኖ ካገኘው ብር የጥቂት ቀን የሆቴል ክፍያ ሰጥቷት ወደተለመደው ቦታው አመራ
............
ሳንዲ ፒርስ ስራ ለመፈለግ ብትሞክርም ምንም ሊሳካላት አልቻለም ፡ እናም ለወራት ፡ በዚህ መልኩ ቆየች ፡ ኩርቲስ ጃክሰን ፡ ከወትሮው የበለጠ ፡ ብዙ ሰወችን እየለመነ ፡ ለምግብ ብቻ የሚበቃውን ይቀንስና ፡ በየእለቱ ወደ ሳንዲ ወደተከራየችው ሆቴል በመሄድ ፡ ክፍያውን ይፈፅምላታል ። ኑሮ መልካም በሆነላት ሰአት ደግነቷን ፡ ላልነፈገችው ሴት ከልጇ ጋር ሳትነጣጠል እንድትኖር በማድረጉ ደስተኛ ነው ።
................
እናም ለወራት እየተመላለሰ ፡ ዘጠኝ ሺህ ዶላር በየጊዜው ሰብስቦ ለሳንዲ ፒርስ ሰጥቷታል ። እናም ግን አንድ ቀን እንደተለመደው ክፍያውን ሊሰጣት ሲሄድ ሳንዲ ፒርስ ትልቅ የምስራች ይዛ ጠበቀችው ።
የስራ ማመልከቻ ያስገባችበት ባንክ ቤት ፡ ከዚህ በፊት ታገኝ ከነበረው ደሞዝ እጥፍ ክፍያ በመክፈል ሊቀጥራት በመወሰኑ ዛሬ ውል እንደፈፀመች ። እናም ከነገ ጀምሮ ቅድሚያ ብድር ወስዳ ፡ ጥሩ ቤት መያዝ እንዳሰበች ነገረችው ።
................
ያንን የጨለማ ጊዜ ፡ ከሰወች እየለመነ ያሳለፋትን ደግ ሰው መቼም እንደማትረሳው ፡ የሱም ህይወት የሚሻሻልበትን መንገድ እንደምትፈልግ ነገረችው ። ኩርቲስ ጃክሰን ደግነቷን ሳትነፍግ መልካም ስታደርግለት የነበረችው ሴት በሆነላት መልካም ነገር ሁሉ ተደሰተ ።
..............
በቻልነው መጠን መልካም እናድርግ መልካምነት መልሶ ይከፍላል ።

© ዋስይሁን
ቢላል ለምን ሞተ?
* * *

ስምንት ቀን ስንት አመት ነው? ሃዘን ያጠላበት አንድ ቀን በስንት አመት ይመነዘራል? ፍስሃ ከተቀላቀለው ግማሽ ዘላለም እና ሃዘን ከደቆሰው አንድ ሳምንት ረዥሙ የቱ ነው?
ሰቆቃ ቀንን ዘልዛላ ያደርጋል፤ ህይወት ምሬት ሲጫናት የሰኣት አጋማሽ ከአእላፍ ቀናት ይልቅ ይረዝማል።

አይሻ ከሳምንት በፊት ወጣት ነበረች። ሃዘን ሲደቁሳት በቀናት እድሜ አሮጊት መሰለች። ቀይ መልኳ ጠቆረ፥ ፊቷ በማዲያት ተወረረ፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ መጎሳቆሏ አጎበጣት፥ ከናፍሮቿ ተሰነጣጠቁ፥ በረዶ መሳይ ጥርሶቿ ዝገት ያገኛቸው መሰሉ።
ከስምንት ቀናት በፊት ከነ አይሻ ቤት አቅጣጫ በተሰማ ከባድ ጩኸት ሰፈሩ ተናወጠ። ተሯሩጠን ቤታቸው ስንደርስ አይሻ በድንጋጤ በድን ሆና ቆማለች። ልጇ ዲና ቀሚሷን ጨምድዳ ይዛ በሃይል ታለቅሳለች።

"ምንድነው የተፈጠረው?" ግራ ገባኝ
"ቢላል... ቢላል... ቢ ላ ል" ያቤፅ ተንተባተበ
"ቢላል ምን ሆነ?"
"ቢ... ላል...." ትንፋሽ አጠረው
"ቢላል ምን ሆነ?" ትዕግሥት አጣኹ
"ቢላል...... ራሱን አጠፋ"
"ኢናሊላሂ..."

ዲና በሃይል ጮኸች።

ዲና፥ መልከመልካሟ፥ ትንሿ አበባ፥ ፍልቅልቋ ኮከብ ከፍ ባለ ድምፅ አለቀሰች።
ይህ ከሆነ ሳምንት አለፈው።

ወዳጃችን ቢላል፥ ታታሪው ሰራተኛ፥ የአባትነት ተምሳሌቱ፥ እውነተኛው አፍቃሪ፥ ከልግስና የማይጎድለው፥ ለዲኑ የሚታመነው..... ወንድማችን ቢላል ላይመለስ አንቀላፋ፥ከራሱ ተጣላ፥ በገዛ እጁ ራሱን አጠፋ።

ከአንድ አሏህ በቀር ማንም ቢሆን በሰው ነብስ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌለው ቢያውቅም ከመርህ አፈነገጠ። ከሚታመንለት እውነት ጋር ተላለፈ።

"ስራ ጠፍቷል። ቤተሰብ ለማስተዳደር እየተቸገረ ነበር" ያቤፅ ከቀብሩ ማግስት ሃዘን በሰበረው መንፈስ ሆኖ አናገረኝ።
"መተጋገዝ እንችል ነበር፥ ራሱ ላይ መፍረድ አልነበረበትም"
"የሰውን እጅ ማየት ያታክታል። እንደቢላል አይነት ኩሩ እና ታታሪ ሰው ራሱን ለጥገኝነት አሳልፎ መስጠት አይሆንለትም። እርሱ መለገስን እንጂ የሰውን እጅ ማየትን አያውቅበትም፥ ከጎዶሎው ላይ ቀንሶ ለሌሎች ቸርነትን ያደርጋል እንጂ ለጎደለው ነገር የሰው እጅ አያይም"
"ቢሆንም ..." ሃሳቤን በእንጥልጥል ተውኩት
ሳምንት አለፈ። ወጣቷ አይሻ አረጀች፥ ፅጌሬዳዋ ጠወለገች፥ ሃዘን አጎሳቆላት፥ ውበቷ ከሸፈ፥ በሳምንት እድሜ ከወጣትነት ወደ እርጅና ተሸጋገረች።

* * *
"ይኼ ቆሻሻ መንግስት ቢላልን ነጠቀን" ያቤፅ ደነፋ
"ምን አልክ?" የሰማሁትን ማመን አልሆነልኝም። ጆሮዬን በአጭበርባሪነት ጠረጠርኩት
"ቢላልን የቀማን መንግስት ነው"
አሁንም ጆሮዬን ማመን ስላልቻልኩ 'ሰልሰው እስቲ' ማለት ቃጥቶኝ ነበር። 'ያቤፅ አብዶ ይሆን' የቅፅበት ጥያቄ አቃጨለብኝ።
"ቢላል ለምን የሞተ ይመስልሃል?" ጠየቀኝ
"ኑሮ ስለከበደው" መለስኩ
"ኑሮ ለምን ከበደው?" ተኮሳተረ
"ሲሚንቶ ስለተወደደ፥ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ስለናረ፥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ ክፉኛ ስለተጎዳ፥ የግንባታ እንቅቃሴ መቋረጥ ስለጀመረ ፥ ግንበኛው ጓደኛችን ላይ ስራ አጥነትን አመጣበት። ስራ ማጣቱ ኑሮውን አከበደው። ይኸው ነው" ሁለታችንም የምናውቀውን ነገርኩት
"ይኽ ለምን ሆነ?"

....

ነገን ፍለጋ
ተስፋአብ ተሾመ
ኤጭ! ...ይኼ እሁድ መጣ ደ'ሞ!
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°

"አንተ!"

"የፈጣሪ ያለኽ! ...ምን ያስጮኽሻል? ...አስደነገጥሽኝ እኮ!"

"ይኼ ምንድን ነው?"

"ምኑ እናቴ?"

"ይኼ!"

"እስኪ መነጽሬን አቀብዪኝ፤ ምንድን ነው?"

"አታሹፍ!"

"ኣ? ...ምን? ...ምኑ? ...የቱ? ...የማን ነው?"

"ከምትንተባተብ ራስኽ ንገረኝ እንጂ!"

"በ ለ ው! ...እነዚኽ ከይሲ ልጆች ከየት አግኝተው አምጥተውት ነው!? ...ትናንት ከቤት ወጥተው ነበር እንዴ?"

"ዝጋ! ...ልጆቼን ያለ ኀጢአታቸው አትስደባቸው! ...የተገኘው ትናንት ለብሰኸው የዋልኸው ጃኬት ውስጥ ነው!"

"ተረጋጊ እናቴ! ...ተረጋጊ! ...መቸም በዚኽ ትዳር የማይቀናብኝ የለም። አንዷ ምቀኛ! ...ኦ! ይቅርታ! አንዱ ምቀኛ መስክሬን ዐይቶ ኪሴ ውስጥ ከትቶብኝ ይኾናል እንጂ፣ እኔም ይኸው ካንቺ እኩል ማየቴ ነው!"

"ዝ..ም በል እኮ ነው የምልኽ!"

"እንዴ! ...እንዴ! ጥፊው ታዲያ ምንድን ነው? ...አበድሽ እንዴ?"

"ማበድ ይነሰኝ!? በዚኽ ልክስክስ አመልኽ ጨርቄን መጣል ይነሰኝ!?"

"ግዴለም እናቴ! ተረጋጊ! ...ትዳር መቼም እንደዚኽ ነው። አንዳችን እሳት ስንኾን አንዳችን ውኃ መኾን አለብን! ...ተረጋጊ! ...የሚጠጣ ውኃ ላምጣልሽ?"

"ቆይ እሺ ምን ልኹን!? ...ትዳሬን ባልኹ! ልጆቼን ባልኹ! ኑሬዬን ባልኹ! እድሜ ልክ ያንተ መጫወቻ ኾኜ ልቅር!?"

"ቀስ! ኧረ ቀስ! ...ልቅሶውን ምን አመጣው ታዲያ!? ...ልጆቹም ይተኙበት!"

"የራሳቸው ጉዳይ!"

"ቀስስስስ... ! ይኸውልሽ እናቴ! ...ነገሩን በማስተዋል ብታዪው እኮ ይኼን ያኽል የሚያበሳጭ አይደለም!"

"ተው እንጂ! ...እ!"

"ጤናዬን ለመጠበቅ! ...ያንቺን የሚስቴን፣ የልጆቼን እናት ጤና ለመጠበቅ እንደምጠቀም፣ ኦ! ይቅርታ! ማለቴ እንደገዛኹት ብታስቢው ጥሩ ነው!"

"እስከ ዛሬስ በሽታ ላይ እንዳልጣልኸኝ በምን አውቃለኹ!?"

"በስማም በዪ አንቺ! ...የሰይጣን ጆሮ ይደፈን! ...ሆ!"

"በቃኝ! በቃኝ! በቃኝ!"

"ምኑ?"

"ይኼ ኑሮ! ...ካንተ ጋር የምኖረው የተልከሰከሰ ሕይወት! ...ከዚኽ በላይ በደል የምሸከምበት ጫንቃ የለኝም!"

"ኮንዶም ባሌ ኪስ ተገኘ ብሎ ይኽን ያኽል ምሬት!? ...ኧረ ተዪ! ፈጣሪን በጦር አትውጊ!?"

"ዝ...ም በል አንተ ልክስክስ ሴሰኛ! ...ዝም በል!"

"እሺ! ...እሺ! ...በዪኝ ግዴለም! ...አጋጭኝ! ...እችለዋለኹ! ...እጅሽ ደግሞ ማቃጠሉ!"

"ቆይ ከእኔ ምን አጥተኽ ነው? ...ምን አጎደልኹብኽ!?"

"ያገኘሽው ኮንዶም እኮ ዐዲስ ነው። አገልግሎት ላይ አልዋለም!'

"ኡኡይ! ዝ...ም በል እኮ ነው የምልኽ! ...ሰይጣኔን አታምጣው!"

"የምን አታምጣው ነው? ...መጥቷል እኮ! ...መጥተዋል። አብራችኹ ናችኹ እኮ! ...ጥፊውን ብቻ አስቀሪልኝ! ...ሌላውን እችለዋለኹ።"

"ውሻ ነኽ እሺ!"

"ነኝ! ...ለዛሬ ነኝ! ...ይኹን! ብቻ አንቺ ተረጋጊ!"

እ ፎ ይ! ኼደች።

"ኧረ ቀስ በሩን! ...ያን የጸሎት መጽሐፍ የት ነው ያደረግሽው? ...በ ለ ው! ደኅና የኼደችልኝን እጠራታለኹ እንዴ! ...እውነት የት ነው ያደረግኹት!? ...ወይኔ! በእኩለ ጾም እንዲኽ ልነጀስ!? ...አይ አንተ ሰይጣን ለዛሬ ተሳኽቶልኻል። ...ቆይ ግዴለም! ...አኹን ጸሎቴ ላይ ድፍት ስል የቤቱ ሰላም ይመለሳል። ...ኤጭ! ይኼ መጽሐፍ የት ኼደ ደ'ሞ!?

© በኃይሉ ገብረእግዚአብሔር

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
አፍሪካን በ 352 ቀናት...

አፍሪካን በ352 ቀን ሮጦ የጨረሰው 🌍

ይህ ሰው ከባድ ፈተናዎችን ሲጋፈጥ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት ከቱርኳ ኢስታንቡል እስከ እንግሊዟ ለንደን ድረስ ሮጧል፡፡ ለአንድ ሳምንት በህይወት ተቀብሯል፡፡ መኪና እየጎተተም ማራቶን ለመሮጥ ሞክሯል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካን ርዝመት መሮጥ የህይወቱ ከባዱ ፈተና ነበር ተብሏል፡፡

ረስ ኩክ ይባላል፡፡ እንግሊዛዊ ነው፡፡ ከ352 ቀናት በፊት በደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው የመጨረሻው ደቡባዊ ጫፍ ላይ ነበር የሚገኘው፡፡ ቦታዋ ደሞ የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ አጉላስ ናት፡፡ ታዲያ ማድረግ አይደለም ለማሰብ የሚከብደውን ተግባር አንድ ብሎ ጀመረ፡፡ በሩጫ አፍሪካን መጨረስ፡፡ በሩጫ ከደቡብ እስከ ሰሜን ጫፍ ማቋረጥ፡፡ መንገዱ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡

ከፍተኛ የሆነ የጤና እክል ገጥሞት ያውቃል፣ መሳርያ ተደግኖበት ተዘርፏል፣ ቪዛ ለማግኘት ተቸግሯል፣ በሰሃራ በረሃ ሙቀት ነዷል፣ የተለያዩ አስፈሪና ከባድ ተራራዎችን እንዲሁም ጥቅጥቅ ደኖችን አቋርጧል፡፡

ለዚህም እንደ አብነት ጉዞውን ከጀመረ በኋላ በ200ኛ ቀኑ ላይ በጤና ችግር ምክንያት ናይጄሪያ ውስጥ በሚገኝ ጤና ተቋም ገብቷል፡፡ ከምርመራው በኋላም በቀን የሚጓዘውን ርቀት መጠን ቀንሶ በማስታገሻዎች ጉዞውን ቀጠለ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ኩክ መነሻውን ከደቡብ አፍሪካ ደቡባዊ ጫፍ / ኬፕ አጉላስ / እስከ ከሰሜን አፍሪካ ሰሜናዊ ጫፍ ቱኒዚያ /ራስ አንጀላ/ ድረስ ሮጠ፡፡ የማይታሰበውን አሳካ፤ ሊደረግ አይችልም ተብሎ የታመነውንም አደረገ፡፡ በዚህም 16 ሀገራትን አቋርጧል፤ 16 ሺሕ ኪሎ ሜትሮችን አካሏል፡፡ ጠቅላላ የሮጠው በማራቶን ቢቀየር ደሞ 376 ማራቶን የመሮጥ ያህል ነው ይለናል የዘጋርዲያን ዘገባ፡፡ የሆነው ሆኖ ኩክ የመጀመሪያው የአፍሪካን አህጉር ርዝመት የሮጠ ሰው ሆኗል፡፡

ኩክ በሩጫው ጊዜያት ከ756 ሺሕ ዶላር በላይ መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ይህንን ገንዘብም በሚያስገርም ሁኔታ ለሁለት የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደሚያውለው ገልጿል፡፡

ኩክ ጉዞውን በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ለጋዜጣው እንደገለጸው ከቤተሰብ ተለይቶ ይህንን ከባድ ጉዞ መጀመር ከባድ እንደነበር ገልጾ በዛ ላይም ህመም ይሰማው እንደነበርና ሌሎች ችግሮችም እንዳጋጠሙት ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ህልሙን ሳያሳካ መቆም እንዳልፈለገ ጠቁሟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ሰዎች ህልማቸውን ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ለመሆን ጉዞውን እንደጀመረ ጠቅሶ በመጨረሻም እንዳለው ተሳክቶለት የጽናት ምሳሌ ለመሆን ችሏል፡፡

በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
ከ112 ዓመታት በፊት በዛሬው ዕለት የሰጠመችው ግዙፏ የታይታኒክ መርከብ

ታይታን (ታይታኒክ) - Unsinkable Ship ...
ቅንጭብጭብ
ከ112 ዓመታት በፊት በዛሬው ዕለት የሰጠመችው ግዙፏ የታይታኒክ መርከብ ታይታን (ታይታኒክ) - Unsinkable Ship ...
#Ethiopia | ታይታኒክ የተገነባችው ሰሜን አይርላንድ ውስጥ “White Star Line” በተባለ ካምፓኒ ነው፡፡

ታይታኒክ 269 ሜትር ርዝመት፣ 28 ሜትር ስፋት፣ 32 ሜትር ቁመት እንዲሁም ከ47 ሚሊዮን ኪ.ግራም በላይ ክብደት ነበራት፡፡

ታይታኒክ የተሰራችው በ7.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ነው፡፡ እ.አ.አ በ1997 ለእይታ የበቃው የጀምስ ካሜሮን ፊልም ታይታኒክ 200 ሚሊዮን ዶላር ወጥቶበታል፡፡

ታይታኒክ በቀን 600 ሺህ ኪ.ግራም ከሰል ትጠቀም ነበር፡፡

ታይታኒክ ከእንግሊዝ ሳውዝ ሀምፕተን ከተማ ወደ ኒውዮርክ ጉዞ የጀመረችው እ.አ.አ ሚያዚያ 10 ቀን 1912 ነው፡፡

መርከቧ ለ4 ቀናት የተሳካ ጉዞ ካደረገች በኃላ 30 ሜትር ቁመት ካለው የበረዶ ግግር ጋር የተላተመችው ሚያዚያ 14 ቀን 1912 ከሌሊቱ 5 ሰዓት ከ40 አካባቢ ነው፡፡ መርከቧ ሙሉ በሙሉ ለመስጠም 2 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ፈጅቶባታል፡፡

በአደጋው ወቅት ከ2 ሺህ 200 በላይ ሰዎች መርከቧ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በህይወት የተረፉት 706 ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡

ታይታኒክ ውስጥ 20 ህይወት አድን ጀልባዎች ነበሩ፡፡ ጀልባዎቹ እያንዳንዳቸው እስከ 64 ሰው የመያዝ አቅም ቢኖራቸውም መርከቧ ውስጥ በተፈጠረው ትርምስ ጥቂት ሰዎችን ብቻ ነበር እየያዙ የወረዱት፡፡

በታይታኒክ አደጋ የሞቱት አብዛኞቹ ወንዶች ናቸው፡፡ ይህም የሆነው ወደ ማምለጫ ጀልባዎች እንዲገቡ ቅድሚያ ለሴቶች እና ለህጻናት በመሰጠቱ ነው፡፡

ከሟቾች ውስጥ 26ቱ ጫጉላ ላይ የነበሩ ጥንዶች ናቸው፡፡

የታይታኒክ የሙዚቃ ባንድ አባላት መርከቧ እስክትሰጥም ድረስ ሙዚቃ መጫወት አላቆሙም ነበር፡፡

መርከቧ ውስጥ የነበሩ አንድ ቄስ ሁለት ጊዜ ወደ ህይወት አድን ጀልባዎች እንዲገቡ ተጠይቀው እሺ ሳይሉ ቀርተዋል፡፡ ቄሱ እስኪሰጥሙ ድረስ ከሞት ጋር የተፋጠጡ ክርስቲያኖችን ኑዛዜ (ንስሐ) ሲሰሙ እና ስርየት ሲለምኑ ነበር፡፡
የታይታኒክ ዋና ካፒቴን ኤድዋርድ ስሚዝ ለመርከቧ ሰራተኞች ያስተላለፉት የመጨረሻ መልዕክት እንዲህ የሚል ነበር፡፡ “ወድ ሰራተኞች የሚጠበቅባችሁን ሁሉ አድርጋችሁል፡፡ ከዚህ በላይ እንድታደርጉ የምጠይቃችሁ ምንም ነገር የለም፡፡ የባህር ላይ ህግን ታውቃላችሁ፡፡ አሁን ሁሉም ሰው ለራሱ ነው፡፡ ፈጣሪ ይባርካችሁ”፡፡

ታይታኒክ ከባህር በታች በ3 ሺህ 840 ሜትር ጥልቀት ነው የሰጠመችው፡፡

ታይታኒክ ከመስጠሟ ከ14 ዓመታት በፊት በ1898 ሞርጋን ሮበርትሰን የተባለ እውቅ ደራሲ ‘ሊሰጥም የማይችለው መርከብ (unsinkable ship) ከበረዶ ግግር ጋር ተላትሞ ሰጠመ’ የሚል ጭብጥ ያለው መጽሐፍ ለንባብ አብቅቶ ነበር፡፡ ደራሲው በምናብ ለፈጠራት መርከብ የሰጣት መጠሪያም “ታይታን” የሚል ነበር፡፡

የታይታኒክ መርከብ ፍርስራሽ የተገኘው አደጋው ከደረሰ ከ73 ዓመታት በኋላ ዶ/ር ሮበርት ባላርድ በተባለ አሜሪካዊ የስነ ውቅያኖስ ተመራማሪ ነበር፡፡ ጊዜውም እ.አ.አ 1985 ዓ.ም ነበር፡፡

የታይታኒክ ፊልም መሪ ተዋናይት ኬት ዊንስሌት “ማይ ኸርት ዊል ጎ ኦን” የተሰኘውን የፊልሙን ማጀቢያ ሙዚቃ እንደምትጠላው ተናግራ ነበር፡፡ ኬት “ሙዚቃውን ስሰማው ሊያስመልሰኝ ይደርሳል“ ነበር ያለችው፡፡

ታይታኒክ ፊልም በ11 ዘርፎች ኦስካር (አካዳሚ አዋርድ) አሸንፏል፡፡ ከሽልማቶቹ ውስጥ ግን አንዱም በተውኔት ዘርፍ የተገኘ አይደለም፡፡ የፊልሙ መሪ ተዋናዮች ኬት ዊንስሌት እና ሊዮናርዶ ዲ ካፔሪዮ በምርጥ ትወና አልተሸለሙም፡፡

© ኢዮብ መንግስቱ - በአብሮነት እንቆይ
@kinchebchabi
የማባልጋት ባለትዳር ነበረች ።

ዋና ተግባራችን ወሲብ ነው ። የምንቀጣጠረው ለወሲብ ብቻ ነው ። የምናወራው ስለ ወሲብ ነው ። አንዳችን አንዳችንን የምንፈልገው ወሲብ ሲያምረን ነው ።

አጠገቤ ሆና ባሏ ደውሎ ያውቃል: "ሰውዬሽ ደወለ" ብዬ ስልኳን አቀብያት አቃለሁ ። ምንም እንዳልተፈጠረ ስታወራው እርቃኗን አትመስልም ነበር። ይገርመኛል ድድብናችን ።

ነውራችን ስለተደጋገመ ተግባራችን ብልግና መሆኑ ተሰወረብን ።

ቢሮዋ እሄዳለሁ፣ ቢሮዬ ትመጣለች ። ጓደኛዬ ቤት፣ እኔ ቤት፣ የሆነ ኮስመን ያለ ሰዋራ ቦታ ፣የሆነ ድብቅ ፅድት ያለ ስፍራ ፣ መኪና ውስጥ ... ብዙ ብዙ ቦታ ትመጣለች እንዋሰባለን ። የታሪካችን መነሻ እና መድረሻው ወሲብ ነው ።
አንድ ቀን በደነገጠ: ተስፋ በቆረጠ ድምፅ "ባሌ አወቀብን" አለችኝ .....ደነገጥኩ ።

ጠፋሁኝ ...ጠፋች

ከአስራ ሰባት ቀን በኋላ ጓደኞቼ "ገኒ ሃዘን ላይ ነች፣ ሙሉ ከላይ እሰከታች ጥቁር ለብሳለች፣ ከስታለች" አሉኝ

"ምን ሆነች?" አልኩ

"ባሏ ሞቶባት ነው፤ ራሱን አጥፍቶ ነው የሞተው" አሉ።

ስደነግጥ፣ ፊቴ ሲቀያየር ፣ እምባዬ ሲያመልጠኝ አዝኜለት ነው የመሰላቸው ። እኔ እንደገደልኩት አልጠረጠሩም ።

የጥፋተኝነት ስሜት ሊገለኝ ሲል ማምለጫ መፅሃፍ ቅዱስ ገለጥኩ።

"ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል " የሚለው ከሁሉም ጎልቶ ተነበበኝ ።
..
ሰው ይዞ መውደቅ ፤ ማስተካከል የማይቻል አወዳደቅ ፣ ሲያስታውሱት የሚያስነክስ አይነት አወዳደቅ፣ እነሳለሁ የማይሉት አወዳደቅ ፣ ወድቄ ነበር የማይሉት አወዳደቅ። በግዜ ምክንያት የማይደበዘዝ አወዳደቅ ...
እንደዚህ አይነት መውደቅ ሲ..ያ...ስ..ጠ..ላ !! !

© አድኃኖም
ይህ ልብወለድ አይደለም፤ እውነተኛ ታሪክ ነው። ወዳጄ Nebiyu Bazezew "አንተ ብትተርከው ይሻላል" ብሎ የነገረኝን ታሪክ እጅጉን ስለደነቀኝ እኔ ፃፍኩላችሁ።


በሬው ጠፋ።
የሚተዋወቁ የሰፈሩ አባወራዎች ናቸው፤ ለቅርጫ ገንዘብ አዋጡ፦ ለፋሲካ። ተወካዮቹ የቅዳሜ ስዑር ዕለት ገበያ ወጡ። ዞር ዞር ብለው ገበያውን አዩ። ዋጋ ጠየቁ። ተከራከሩ። እንደአቅማቸው በሬ ገዙ፦ በ58 ሺህ ብር። ወደ ሰፈራቸው ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሬውን ይዘው መጥተው አንድ ግቢ ውስጥ አሰሩ። አራጅ ቀጠሩ። ለሊት ሰባት ሰዓት ሊያርዱት ከአራጁ ጋር ተቀጣጥረው ተሰነባበቱ።


ለሊት ሰባት ሆነ።
ሰዎች ተሰባሰቡ፤ በሬውን ሊያርዱት ገመዱን ሲፈቱት አመለጠ። ተከተሉት። በዚያ ድቅድቅ ጨለማ የዕውር ድንብራቸውን ሮጡ። ሊደርሱበት አልቻሉም። ፈረጠጠ። ዳገት ወጡ፣ ወረዱ። ልባቸው ሊፈነዳ ደረሰ። ሩጫቸውን ገታ አድርገው ጨለማው ላይ አፈጠጡ። ከፊታቸው ጥቁር ጨለማ ብቻ ተዘርግቷል። ተስፋ ቆረጡ። በሐዘን ተውጠው ወደ ሰፈራቸው ተመለሱ።


አይነጋ የለም፤ ነጋ።
"እንግዲህ ለቅርጫ ማሕበርተኛው ምን ይባላል?" ተባባሉ። ቅርጫ የገቡት ሰዎች በሬው መገዛቱን አይተዋል፤ አንድ ግቢ ውስጥ መታሰሩንም አይተዋል፤ ለሊት በሬው ጠፋ ቢባል ማን ያምናል? ዓመት በዓሉስ እንዴት ዓመት በዓል ይሆናል?!
"ዕድል ቢቀናን ወደ ጫካ ወጥተን እንፈልግ" ተባባሉ። እናም ወፍ ሲንጫጫ ለሊት በሬው ወደፈረጠጠበት አቅጣጫ ጉዞ ጀመሩ።


በጉዞአቸው መሃል ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ታየቻቸው፤ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ኪዳነምህረት። ተሳለሙ።
"እመቤቴ አንቺ እርጂን" አሉ። ስዕለት ተሳሉ። እናም ፍለጋቸውን ቀጠሉ፦ ወደ አንቆርጫ። አንዱን ኮረብታ አልፈው፣ ወደ ሌላ ኮረብታ። "አይ በዚህ ምንም ዳና የለም" እየተባባሉ በሌላ መንገድ ፍለጋ ቀጠሉ፤ ያኛውንም መንገድ እየተው በሌላ አቅጣጫ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ፣ እግራቸው እንዳመራቸው ሲሄዱ ቆይተው ደረሱ፦ አካኮ።


እዚያ ከአንድ የገጠር ጎጆ ፊት ለፊት ጫካ ውስጥ ሰዎች ተሰባስበዋል። ብዙ ናቸው፤ በሬ አርደው እዚያው የሚበላውን ሥጋ እየበሉ ነው። እየተጨዋወቱ፤ እየተጎራረሱ፣ መደብ እየመደቡ ወዘተ። የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው።

በሬ ፈላጊዎቹ ጠጋ ብለው ሰላምታ ሰጧቸው።
ከሠላምታ በኋላ፦ "ኑ! ምሰሉን፤ እዚህ ቁጭ በሉ" አሏቸው፤ ወደሚበሉት ሥጋ እየጠቆሙ ጋበዟቸው።
"አይ አንቀመጥም" አሏቸው የታረደው በሬ የእነሱ መሆኑን ለመለየት ወደ ቆዳው እያማተሩ።

"ኧረ ነውር ነው፤ በዓመት በዓል ሳትቀምሱ አትሄዱም"
"የለም፤ እንቸኩላለን"
"ብትቸኩሉስ፤ ቁጭ በሉ አፋችሁ ላይ ይቺን ጣል አድርጉ" አሏቸው ሥጋ በእጃቸው እያቀበሏቸው። በእጃቸው የዘረጉትን
ሥጋ ተቀብለው በሩቅ ሲያማትሩ አንዱ ሽማግሌ ሌላ ጥያቄ ሰነዘሩ።

"ምነው፤ ምን እግር ጣላችሁ? ምን ሆናችሁ ነው?"
ነገሯቸው፤ በሬ እንደጠፋባቸውና ፍለጋ ላይ እንደሆኑ።
ገበሬዎቹ መንደርተኞች እርስ በርስ ተያዩ።


አካኮ፤ ገበሬዎቹ በሬ የጣሉበት ጫካ ፊት ለፊት ያለው ጎጆ ውስጥ ያሉ አንድ እናት አልፈስክም ብለው አስቸግረዋል። ምክንያቱ የተሸጠው በሬ ነው።

ከፈረንሳይ ለጋሲዮን ጨፌ አካባቢ የጠፋው በሬ ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በፊት "ቤቱ" ደርሷል። የበሬውን መድረስ ያዩት እናት አዝነዋል።

"ይኼንን በሬ የገዙት ሰዎች፤ ቤተሰቦቻቸው፣ ልጆቻቸው ሳያከፍሉ፤ እኔ አላከፍልም" ብለው እህል ሳይቀምሱ ፀሐይ ወገግ ብሏል። ገበሬዎቹ ይህንን ስለሚያውቁ ነው እርስ በርስ የተያዩት።


ገበሬዎቹ በዐይናቸው ተሳስቀው፤ እነዚህ ጥቁር እንግዶች ቁጭ እንዲሉ ወተወቷቸው። እና አረቄ በስኒ እየጋበዟቸው ጥያቄአቸውን ቀጠሉ።

"የት ነው የገዛችሁት?"
"የሸጠላችሁ ሰው መልክ ታውቁታላችሁ?"
"በስንት ገዛችሁ?"
ተጠያቂዎቹ ሁሉንም ጥያቄ በትክክል መለሱ። ይኼኔ አንዱ ወጣት "ልክ ናችሁ፤ እኔ ነኝ የሸጥኩላችሁ" አለ ራሱ ላይ የጠመጠመውን ነጠላ ቢጤ አንስቶ።

"ዐይናችንን የሆነ ነገር ጋርዶት እንጂ ሻጩ ፊት ለፊታችን ነበረ" አለኝ ይኼን ታሪክ የነገረኝ ገዢ።

ቀጠለ ወጣቱ ገበሬ፦
"...በሬው የእናታችን ነው፤ ቤቱ ገብቷል፤አዎ 58 ሺህ ብር ነው የገዛችሁኝ። አሁን ግን እጄ ላይ ያለው 55 ሺህ ነው። እንደገዛችሁኝ አንድ ሺህውን ብር ከጓደኞቼ ጋር ተገባብዘንበታል፤ 2 ሺህ ብር ደግሞ ለደላላ ከፍለናል። የቀረው 55 ሺህ ገንዘባችሁ ነው፤ ውሰዱ"

ተገረሙ።

"እኛ ግን በሬውን...."
አቋረጧቸው አንዱ አባት።
"አይ በሬውን አንሰጣችሁም፤ ይኼ በሬ ካለምክንያት ተመልሶ አልመጣም፤ ከአሁን በኋላ አይሸጥም፤ ከቤትም አይወጣም ብላለች ባለቤቴ"

"ወቸው ጉድ"
"ባይሆን"
"ባይሆን ምን?.."
"ብሩን አንወስድም ካላችሁ ሌላ በሬ እንቀይርላችሁ፤ ሁለት ሺህ ጨምራችሁ ሌላውን በሬ ውሰዱ"

በዚሁ ተስማሙ።
በሬ የጠፋባቸው ሰዎች ሌላ በሬ ይዘው እኩለ ቀን ላይ ወደ ሰፈራቸው ተመለሱ።

እውነተኛ ፋስካም ሆነላቸው።
---
Via ወሰንሰገድ ገብረኪዳን
መዲና ቅጽ 6.pdf
11.4 MB
መዲና ፮ እነሆ

https://t.me/Medinamagazine

በተጨማሪም በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ቤተሰብ ይሁኑን!

https://www.facebook.com/profile.php?id=61556884335163&mibextid=ZbWKwL

https://www.instagram.com/medinadigitalmegazine?igsh=ejZqbjN3OXF0dHJj

ለአስተያየትዎ

medinadigitalmagazine@gmail.com

ነሐሴ 2016 ዓ.ም
ነፍስ ኄር አለቃ ኪዳነ ወልድ
(1864-1936)

#Henock Yared Fenta በ#ሔኖክ ያሬድ ፈንታ እንደከተቡት።



ሆሄ የሥነ ጽሑፍ ሽልማት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በዕለተ ሰኞ ነሐሴ 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ባዘጋጀው ዓመታዊ መሰናዶ፣ በሕይወት ዘመን የሥነ ጽሑፍ የላቀ ባለውለታ ዘርፍ፣ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌን ተሸላሚ አድርጓል፡፡

ነፍስ ኄር አለቃ ኪዳነ ወልድ (1864-1936) በተለይ በመጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ዐቢይ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ይታወቃሉ፡፡ ይህንን ሥራቸው በያዘው ጥልቅ ሐሳብ አንፃር ያዩት አንዳንድ ባለሙያዎች ከኢንሳይክሎፒዲያ ጋር ያመሳስሉታል፡፡

ክብረት ይስጥልን ሆሄ!!!

ኪወክ ሐውልታቸው - መጽሐፋቸው!

በኢትዮጵያ ሕዋ እንደተወርዋሪ ኮከብ ብቅ ብለው ካለፉት እሙራንና ማዕምራን (ታዋቂዎችና አዋቂዎች) መካከል በ19ኛው በ20ኛው ምእት ዓመት ውስጥ የኖሩት አለቃ ኪዳነ ወልድ ከፍሌ አንዱ ናቸው፡፡ ዘንድሮ ከተወለዱ 145ኛ ዓመት፣ ካረፉ ከአፀደ ሥጋ ከተለዩ 73 ዓመት ሞልቷቸዋል፡፡

ሥራዎቻቸው በቤተክህትም ሆነ በቤተመንግሥት ይሁንታንና ይበልታን ያገኘ፣ እስከዘመናችን ድረስም በማጣቀሻነት በማስተማሪያነት፣ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እየሰጠ ለመሆኑ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ከመዠመርያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ የመመረቂያ ድርሳኖች ውስጥ ሳይጠቀሱ ያለፉበት ጊዜ የለም፡፡

ለየድርሳናቱ (ቴሲስ ዲዘርቴሽን) ምልዐት ከኪዳነ ወልድ የጽሑፍ ጎተራ ያልዘገነ ያልቀመሰ፣ ያላTaጣመ አይኖርም፡፡ የግእዝ ቋንቋን ከሌሎች ሴማዊ ቋንቋዎች ጋራ እያገናዘቡ በመመርመር የፊሎሉጂ ጥናት በማድረግ ረገድ በፋና ወጊነት በአገሬው ሊጠቀሱ ቢችልም፣ በዘመናችን የሳቸውን ፈለግ ተከትሎ ንፅፅራዊ ጥናት ስለመቀጠሉ የተሰማ የተጻፈ ነገር አለመኖሩን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረውና ግእዝና ዐረቢኛን ብቻ መሠረት ያደረገው የፊሎሎጂ ትምህርት ክፍል ወደ ሌሎቹም ተዛማጅ ቋንቋዎች ይሸጋገር ይሆን?

ለውጭ አገር ዕውቆች ከኮንፊሽየስ ጀምሮ ክብር የሚሰጠው ዩኒቨርስቲያችን ለኪወክ (ኪዳነወልድ ክፍሌ) የሚሰጠው መቼ ይሆን?

በቀኃሥ ዘመን ለብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ በመወዘክር የማንበቢያ እልፍኝ እንደተሰየመው ለኪወክስ የሚሰይም ማን ይሆን?

***



በመሚል ሄኖክ ያሬድ ፈንታ የከተቡትን ጽሑፍ አጋራናችኹ።
"ሊያብብ ሲል"
ሱስ ሳይበላው፣ ሲጋራ መግዣ መለመን ሳይጀምር፣ ጉስቁልና ሳያፈዘው፣ ለልብሱ መቆሸሽ ደንታ ቢስ ከመሆኑ በፊት፣ ሰዎችም ሲጣራ ባልሰማ መሄድ ሳይጀምሩ፣ ቃል አባይ ከመሆኑ በፊት፣ ክብሬ ማለት ሳያቆም፣ ለትንሽ ለትልቁ መላክ ሳይጀምር በፊት…

ቆንጆ፣ ተወዳጅ እና ዘናጭ ነበር።
ከጓደኞቹ በላይ ድምቅ ያለ ልጅ ነበር፤ የፀጉሩን ፍሪዝ በመስታወት አስር ጊዜ እያየ አስር ጊዜ ያስተካክል ነበር።

ሕልመኛ ነበር። እንደ ሁሉም ወጣት ሀብታም መሆን፣ አዋቂ መሆን፣ ቤተሰቦቹን የመርዳት ሕልም ነበረው።

የተንሸዋረረ አራድነት አሳስቶት የለኮሳት ሲጋራ፣ ለሳቅ ብሎ የተጎነጫት አረቄ፣ ለሙድ ብሎ የቀነጠሳት የጫት ቅጠል ስትደጋገም አፈዘዘችው፤ ሕልሙን፣ ወጣትነቱን፣ ክብሩን አረገፈችው።

ማንም ብርቱ ነኝ ቢል ታግሎ የማያስመልሳትን ወጣትነቱን ለማያውቀው ጣዖት እየሰዋት ነው።

ጥግ ላይ ተቀምጦ፤ ዘመን ሄዶ ዘመን በመጣ ቁጥር የሚመጡ ለውጦችን ከዳር በትዝብት እየተመለከተ
'ጊዜው እንዴት ነው የሚሮጠው?'
የሚል ይመስለኛል።

"አዎ! እሱ ጋ ያመኛል!"
ገጽ-41
(አድኃኖም ምትኩ)
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በዚህ ዓመት ፣ ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ ፥ ትንሸ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሠደጃ ፥ ምናለበት ፤
ለምናልባት ብንተውለት?!

በአንጎላችን መላወሻ ፣ ትንሽ ቦታ እንተውለት
‹‹ምናልባት›› የምንልበት!!
ልክ እንደአምና ለዚህ ዓመት ።

ብንጣላ መታረቂያ ፥ ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሠር ይቅር ማያ ፥ ትንሽ እንተው ! መጠለያ ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ ፣ ጥግ ድረስ የለም ፋታ ፤
በልባችን ደግ በኩል ፣ የጳጉሜ አይነት ፥ እንፈልግ ባዶ ቦታ ።
----------------------------
ነብይ መኮንን - ጳጉሜ 5 2005 ዓ.ም
ምጥን ቅጽ.pdf
14.9 MB
ውድ የመዲና ዲጂታል መጽሔት ቤተሰቦች

እንኳን ለ2017 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! ለአዲስ ዓመት ገጸ በረከት እጅ መንሻ ይሆን ዘንድ የጳጉሜን ልዩ ዕትም ይዘንላችሁ ቀርበናል። የጳጉሜ ዕትም በመሆኗ ከወትሮ በተለየ በገጽ ከመመጠኗ በቀር ያጎደለችው ነገር የለም። ስለምታነቡን እናመሰግናለን።

መልካም አዲስ ዓመት!