❥:::::::::::: ልብ በል:::::::::::❥
☞ችግርህን አላህ ካልፈታው ገንዘብ ችግርህን አይፈታውም አላህ ካልሞላው ሰው ጎንህን አይሞላውም አላህ ካልገለጸልህ እውቀት ጥበብ አይሆንም
፡
ይቺ ዓለም ለሁሉም እኩል ናት፡፡ ዛሬ ብታገኝ ነገ ታጣለህ ዛሬ ብታሸንፍ ነገ ትሸነፋለህ፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው የሚባል መዶሻ አለ፡፡ መልካምነት ዋጋ ያስከፍልሃልና ሁሌም ፍጹም መልካም ሰው ሁን
፡
ህይወትህ ትርጉም እንዲኖራት ዓላማ ይኑርህ፡፡
፡
የአንተነትህ ትልቁ ምዕራፍ ከእውቀትህ በላይ ስራህ መሆኑን አትርሳ፡፡
፡
ንጹህ ልብ ልክ እንደ አበባ ናት! ፍሬ ባናገኝባትም ውበቷ ግን እጅግ ማራኪ ነው፡፡
:
የውድቀት መጀመሪያ ራስህን አዋቂና ብቸኛ አድርጎ ማሰብ ነው
፡
ፍጻሜህ እንዲያምር ራስህን አታመጻድቅ ሁሌም ከስህተትህ ለመታረም ፈቃደኛ ሁን ጥፈፋትህን አሜን ብለህ መቀበልህ ክብርህን የሚጎዳብህ አይምሰልህ፡፡
፡
ጠቢብ ሰው እንኳን ከራሱ ከሰው ስህተት ተምሮ ራሱን ይጠብቃል ይመለሳልና፡፡
፡
በህይወት ውስጥ አንዱ ሲታወር አንዱ መሪ መሆን አለበት
፡
እውነትነ የሚናገር ሰው አፉ ክፉ ይመስላል ልቡ ግን ንጹህ ነው
፡
ህይወት በመደጋገፍ የተሞላች ናትና ወንድምህን ለመርዳት ወደሗላ አትበል!
📩:::::::::::ቴሌግራማችን:::::::::::::📩
https://t.me/ketibeb
☞ችግርህን አላህ ካልፈታው ገንዘብ ችግርህን አይፈታውም አላህ ካልሞላው ሰው ጎንህን አይሞላውም አላህ ካልገለጸልህ እውቀት ጥበብ አይሆንም
፡
ይቺ ዓለም ለሁሉም እኩል ናት፡፡ ዛሬ ብታገኝ ነገ ታጣለህ ዛሬ ብታሸንፍ ነገ ትሸነፋለህ፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው የሚባል መዶሻ አለ፡፡ መልካምነት ዋጋ ያስከፍልሃልና ሁሌም ፍጹም መልካም ሰው ሁን
፡
ህይወትህ ትርጉም እንዲኖራት ዓላማ ይኑርህ፡፡
፡
የአንተነትህ ትልቁ ምዕራፍ ከእውቀትህ በላይ ስራህ መሆኑን አትርሳ፡፡
፡
ንጹህ ልብ ልክ እንደ አበባ ናት! ፍሬ ባናገኝባትም ውበቷ ግን እጅግ ማራኪ ነው፡፡
:
የውድቀት መጀመሪያ ራስህን አዋቂና ብቸኛ አድርጎ ማሰብ ነው
፡
ፍጻሜህ እንዲያምር ራስህን አታመጻድቅ ሁሌም ከስህተትህ ለመታረም ፈቃደኛ ሁን ጥፈፋትህን አሜን ብለህ መቀበልህ ክብርህን የሚጎዳብህ አይምሰልህ፡፡
፡
ጠቢብ ሰው እንኳን ከራሱ ከሰው ስህተት ተምሮ ራሱን ይጠብቃል ይመለሳልና፡፡
፡
በህይወት ውስጥ አንዱ ሲታወር አንዱ መሪ መሆን አለበት
፡
እውነትነ የሚናገር ሰው አፉ ክፉ ይመስላል ልቡ ግን ንጹህ ነው
፡
ህይወት በመደጋገፍ የተሞላች ናትና ወንድምህን ለመርዳት ወደሗላ አትበል!
📩:::::::::::ቴሌግራማችን:::::::::::::📩
https://t.me/ketibeb
❤2👍2
()اللـهـمَّ ﷺصَـلِّﷺوَسَـــلِّـمْ ﷺ وَبَارِك ﷺْ عـلـى ﷺ نَبِيِّنَـــا ﷺ مُحــمَّد
┊┊┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
መልካም ጅምዓ 🌹
https://t.me/ketibeb
┊┊┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
┊┊♡ﷺﷺﷺﷺﷺ
መልካም ጅምዓ 🌹
https://t.me/ketibeb
👍2❤1
የወንጀል መዘዙ ከባድ ነው በተለይ እያወቁ ሲያጠፉ!
(وَلَوْ يُؤَاخِذُ اللَّهُ النَّاسَ بِمَا كَسَبُوا مَا تَرَكَ عَلَىٰ ظَهْرِهَا مِنْ دَابَّةٍ وَلَٰكِنْ يُؤَخِّرُهُمْ إِلَىٰ أَجَلٍ مُسَمًّى ۖ فَإِذَا جَاءَ أَجَلُهُمْ فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِعِبَادِهِ بَصِيرًا)
"አሏህ ሰዎችን በሰሩት በደልና ወንጀል ሁሉ እዚሁ ዱኒያ ላይ የሚቀጣቸው ቢሆን ኖሮ ምድር ላይ ማንንም ሳያስቀር
-ወንጀል የሰሩትንም ያልሰሩትንም እንስሳትንም ጭምር- ባጠፋቸው ነበር
ነገር ግን ለተወሰነ ጊዜ ያቆያቸዋል አጀላቸውም ሲደርስ እርሱ የባሮቹን ምንነት ጠንቅቆ በሚያውቀው መሰረት የስራቸውን ይሰጣቸዋል" አል ፋጢር 45
https://t.me/ketibeb
(وَلَوْ يُؤَاخِذُ اللَّهُ النَّاسَ بِمَا كَسَبُوا مَا تَرَكَ عَلَىٰ ظَهْرِهَا مِنْ دَابَّةٍ وَلَٰكِنْ يُؤَخِّرُهُمْ إِلَىٰ أَجَلٍ مُسَمًّى ۖ فَإِذَا جَاءَ أَجَلُهُمْ فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِعِبَادِهِ بَصِيرًا)
"አሏህ ሰዎችን በሰሩት በደልና ወንጀል ሁሉ እዚሁ ዱኒያ ላይ የሚቀጣቸው ቢሆን ኖሮ ምድር ላይ ማንንም ሳያስቀር
-ወንጀል የሰሩትንም ያልሰሩትንም እንስሳትንም ጭምር- ባጠፋቸው ነበር
ነገር ግን ለተወሰነ ጊዜ ያቆያቸዋል አጀላቸውም ሲደርስ እርሱ የባሮቹን ምንነት ጠንቅቆ በሚያውቀው መሰረት የስራቸውን ይሰጣቸዋል" አል ፋጢር 45
https://t.me/ketibeb
👍4❤2
የቅዱስ ቁርኣን ትርጉም በድምፅ.apk
83 MB
የጁሙዓ + የረመዳን ስጦታ እነሆ!
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቅዱስ ቁርአን የአማርኛ ትርጉም
ድምጽ በወንድም ሙሐመድ ፈረጅ ተዘጋጅቶ ተለቀቀ!
በተጨማሪም በቅርቡ በplay store እና በApp store ላይ ማግኘት ይችላሉ!
#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቅዱስ ቁርአን የአማርኛ ትርጉም
ድምጽ በወንድም ሙሐመድ ፈረጅ ተዘጋጅቶ ተለቀቀ!
በተጨማሪም በቅርቡ በplay store እና በApp store ላይ ማግኘት ይችላሉ!
#ሚንበር_ቲቪ
#ሁለንተናዊ_ከፍታ!
👍4❤3
ወዳጆቼ የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይሁን
ኢድ ሙባረክ‼
በቅርቡ እንገናኛልን ኢንሻ አላህ!
ኢድ ሙባረክ‼
በቅርቡ እንገናኛልን ኢንሻ አላህ!
❤2👍1
ጣፋጭ የአላህ ጥሪ .....
۞ وَسَارِعُوٓا۟ إِلَىٰ مَغْفِرَةٍۢ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا ٱلسَّمَٰوَٰتُ وَٱلْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
۞ ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡
۞ ٱلَّذِينَ يُنفِقُونَ فِى ٱلسَّرَّآءِ وَٱلضَّرَّآءِ وَٱلْكَٰظِمِينَ ٱلْغَيْظَ وَٱلْعَافِينَ عَنِ ٱلنَّاسِ ۗ وَٱللَّهُ يُحِبُّ ٱلْمُحْسِنِينَ
۞ ለእነዚያ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፣ ቁጭትንም ገቺዎች ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት ( ተደግሳለች ) ፡፡ አላህም በጎ ሠሪዎችን ይወዳል ፡፡
۞ وَٱلَّذِينَ إِذَا فَعَلُوا۟ فَٰحِشَةً أَوْ ظَلَمُوٓا۟ أَنفُسَهُمْ ذَكَرُوا۟ ٱللَّهَ فَٱسْتَغْفَرُوا۟ لِذُنُوبِهِمْ وَمَن يَغْفِرُ ٱلذُّنُوبَ إِلَّا ٱللَّهُ وَلَمْ يُصِرُّوا۟ عَلَىٰ مَا فَعَلُوا۟ وَهُمْ يَعْلَمُونَ
۞ ለእነዚያም መጥፎ ሥራን በሠሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኀጢአቶቻቸው ምሕረትን የሚለምኑ ለኾኑት ከአላህም ሌላ ኀጢአቶችን የሚምር አንድም የለ፡፡ (በስሕተት) በሠሩትም ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑ የማይዘወትሩ ለኾኑት (ተደግሳለች) ፡፡
۞ أُو۟لَٰٓئِكَ جَزَآؤُهُم مَّغْفِرَةٌۭ مِّن رَّبِّهِمْ وَجَنَّٰتٌۭ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَا ۚ وَنِعْمَ أَجْرُ ٱلْعَٰمِلِينَ
۞ እነዚያ ምንዳቸው ከጌታቸው ምሕረትና በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ በሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶችም ናቸው፡፡ የሠሪዎችም ምንዳ (ገነት) ምንኛ አማረች! ፡፡
سورة آل عمران ( 133 - 136 )
۞ وَسَارِعُوٓا۟ إِلَىٰ مَغْفِرَةٍۢ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا ٱلسَّمَٰوَٰتُ وَٱلْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
۞ ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡
۞ ٱلَّذِينَ يُنفِقُونَ فِى ٱلسَّرَّآءِ وَٱلضَّرَّآءِ وَٱلْكَٰظِمِينَ ٱلْغَيْظَ وَٱلْعَافِينَ عَنِ ٱلنَّاسِ ۗ وَٱللَّهُ يُحِبُّ ٱلْمُحْسِنِينَ
۞ ለእነዚያ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፣ ቁጭትንም ገቺዎች ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት ( ተደግሳለች ) ፡፡ አላህም በጎ ሠሪዎችን ይወዳል ፡፡
۞ وَٱلَّذِينَ إِذَا فَعَلُوا۟ فَٰحِشَةً أَوْ ظَلَمُوٓا۟ أَنفُسَهُمْ ذَكَرُوا۟ ٱللَّهَ فَٱسْتَغْفَرُوا۟ لِذُنُوبِهِمْ وَمَن يَغْفِرُ ٱلذُّنُوبَ إِلَّا ٱللَّهُ وَلَمْ يُصِرُّوا۟ عَلَىٰ مَا فَعَلُوا۟ وَهُمْ يَعْلَمُونَ
۞ ለእነዚያም መጥፎ ሥራን በሠሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኀጢአቶቻቸው ምሕረትን የሚለምኑ ለኾኑት ከአላህም ሌላ ኀጢአቶችን የሚምር አንድም የለ፡፡ (በስሕተት) በሠሩትም ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑ የማይዘወትሩ ለኾኑት (ተደግሳለች) ፡፡
۞ أُو۟لَٰٓئِكَ جَزَآؤُهُم مَّغْفِرَةٌۭ مِّن رَّبِّهِمْ وَجَنَّٰتٌۭ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَا ۚ وَنِعْمَ أَجْرُ ٱلْعَٰمِلِينَ
۞ እነዚያ ምንዳቸው ከጌታቸው ምሕረትና በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ በሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶችም ናቸው፡፡ የሠሪዎችም ምንዳ (ገነት) ምንኛ አማረች! ፡፡
سورة آل عمران ( 133 - 136 )
👍5❤1
ጠፊዋ ዱንያ
ቀን ቀን የደከምንለት ሌት ሌቱን የቃዠንለት ሃብትና ንብረት አመድ መሆኑ አይቀሬ ነው! ! እንኳን ተሰብሳቢው ሰብሳቢውም አይቀርለት!!
كُلُّ مَنْ عَلَيْهَا فَانٍۢ
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
ያለ የሌለንን ሁሉ ጥለን ወደ ዘላለማዊው የአኺራ ኑሮ የምንጓዝበት አንድ ቀን ከተፍ ማለቱ አይቀሬ ነው! የዛኔ አሳደን ያጠራቀምንው ሸቀጥና ገንዘብ ከአስከፊው የቀብርና የጀሃነም ቅጣት አያድነንም ። ከአላህ እዘነት ጋር መልካም ከለላ የሚሆነን ተውሒዳችንና በትእግስት ያካበትንው መልካም ስራ ነውና ያለፈውን ሁሉ ሊምር ቻይ ወደሆነው الله እንመለስ እና መልካም ስራዎችን እናካብት!!
አላህ በተከበረው ቁርአኑ በዱንያ ላይ የለገሰልንን ሁሉ ጥለን ቤሳቢስቲን ሳይኖረን እሱን የምንገናኝበት ቀን እንደሚመጣ እንዲህ በማለት ያስታውሰናል ፣
وَلَقَدْ جِئْتُمُونَا فُرَٰدَىٰ كَمَا خَلَقْنَٰكُمْ أَوَّلَ مَرَّةٍۢ وَتَرَكْتُم مَّا خَوَّلْنَٰكُمْ وَرَآءَ ظُهُورِكُمْ ۖ ...
መጀመሪያም ጊዜ እንደ ፈጠርናችሁ ኾናችሁ የሰጠናችሁን ሁሉ በጀርባዎቻችሁ ኋላ የተዋችሁ ስትኾኑ የሰጠናችሁን ሁሉ በጀርባዎቻችሁ ኋላ የተዋችሁ ስትኾኑ ለየብቻችሁ ኾናችሁ በእርግጥ መጣችሁን ....
ያለፈው ሁሉ አልፏል በዱንያ ሸቀጦች መታለላችን ይብቃና ወደ አላህ እንመለስ — ፈጣሪያችን አዛኝና መሃሪ ነው!!
አላህ ይምራን!!
ቀን ቀን የደከምንለት ሌት ሌቱን የቃዠንለት ሃብትና ንብረት አመድ መሆኑ አይቀሬ ነው! ! እንኳን ተሰብሳቢው ሰብሳቢውም አይቀርለት!!
كُلُّ مَنْ عَلَيْهَا فَانٍۢ
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
ያለ የሌለንን ሁሉ ጥለን ወደ ዘላለማዊው የአኺራ ኑሮ የምንጓዝበት አንድ ቀን ከተፍ ማለቱ አይቀሬ ነው! የዛኔ አሳደን ያጠራቀምንው ሸቀጥና ገንዘብ ከአስከፊው የቀብርና የጀሃነም ቅጣት አያድነንም ። ከአላህ እዘነት ጋር መልካም ከለላ የሚሆነን ተውሒዳችንና በትእግስት ያካበትንው መልካም ስራ ነውና ያለፈውን ሁሉ ሊምር ቻይ ወደሆነው الله እንመለስ እና መልካም ስራዎችን እናካብት!!
አላህ በተከበረው ቁርአኑ በዱንያ ላይ የለገሰልንን ሁሉ ጥለን ቤሳቢስቲን ሳይኖረን እሱን የምንገናኝበት ቀን እንደሚመጣ እንዲህ በማለት ያስታውሰናል ፣
وَلَقَدْ جِئْتُمُونَا فُرَٰدَىٰ كَمَا خَلَقْنَٰكُمْ أَوَّلَ مَرَّةٍۢ وَتَرَكْتُم مَّا خَوَّلْنَٰكُمْ وَرَآءَ ظُهُورِكُمْ ۖ ...
መጀመሪያም ጊዜ እንደ ፈጠርናችሁ ኾናችሁ የሰጠናችሁን ሁሉ በጀርባዎቻችሁ ኋላ የተዋችሁ ስትኾኑ የሰጠናችሁን ሁሉ በጀርባዎቻችሁ ኋላ የተዋችሁ ስትኾኑ ለየብቻችሁ ኾናችሁ በእርግጥ መጣችሁን ....
ያለፈው ሁሉ አልፏል በዱንያ ሸቀጦች መታለላችን ይብቃና ወደ አላህ እንመለስ — ፈጣሪያችን አዛኝና መሃሪ ነው!!
አላህ ይምራን!!
👍8🥰2
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረከቱህ ?? ዉድ የጥበበ ሉቅማን ቻናል ተከታታዮች እንደምን ከረማችሁ?? ጠፍን አይደል በጣምይቅርታ? ከዚህበኋላ አዳዲስ አስተማሪ መጣጥፎን ታሪኮችን የምናቀርብ ይሆናል ወኢንሿአላህ
👍9🥰2👏2❤1
#ሁለቱ_ልጃገረዶች
#ክፍል_አንድ
ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ወደዚህች ምድር ከመምጣታቸው በፊት ሁለት ወዳጅ የሆኑ ልጃገረዶች መካ ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህ እጅግ ቅርብ የሆነ ወዳጅነት የነበራቸው ልጃገረዶች አሚና እና ኸዲጃ ይባላሉ። መካ የተቆረቆረችው ግብፅን፣ ፍልስጤምን፣ ፋርስን፣ ሜሶፖቶሚያን፣ ህንድንና አፍሪካን በሚያገናኙና የአካባቢው አገራት ቁልፍ የንግድ መዳረ በነበሩ መንገዶች ላይ ነበር፡፡ በወቅቱ ከመላው ዓለም የሚመጡ የተለያዩ ሸቀጦች የሚቀርቡበት ዓመታዊ የገበያ ልውውጥም በዚሁ አካባቢ ይካሄድ
ነበር። እዚያው መካ ውስጥ ደግሞ ሰዎች አንድ ፈጣሪን ብቻ ያመልኩበት ዘንድ በኢብራሂምና እስማኢል የተገነባው ጥንታዊው የአላህ(ሱ.ወ) ቤት ካዕባ ይገኝ ነበር፡፡
ካዕባ በዓለም ውስጥ ከሚገኙት እጅግ ጥንታዊ የሆኑ ህንፃዎች ሁሉ ቀዳሚው በመሆኑ የመላው ዐረብ ህዝብ የኩራት ምንጭ ተደርጎም ይወሰድ ነበር፡፡ ያም ሆኖ ግን ዐረቦች የኢብራሂምን ንፁህ የሆነ እምነት በመዘንጋት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ጣኦታት አንፀው በዚህ ታሪካዊ የካዕባ ህንፃ ውስጥ በማኖር ያመልኩ ነበር፡፡ እናም ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ህዝብ ሸቀጡን ገበያው ላይ በማቅረብ ለመሸጥና ለራሱ የሚፈልገው ካለ ደግሞ ከሌላው ለመሸመት እንደዚሁም በአላህ ቤት ካዕባ በመገኘት የሐጅ ስረዓተ-ጸሎትን ለመከወን በየዓመቱ ወደመካ ይጎርፍ ነበር፡፡ በዚሁ ወቅት የተለያዩ ገጣሚያን የግጥም ድርሰቶቻቸውን በማንበብ እርስ በእርሳቸው የሚወዳደሩበት ትርኢትም የተለመደ ነበር፡፡ መንገደኛ የታሪክ ተራኪዎችም ከየመጡባቸው አካባቢዎች ያጠናቀሯቸውን አዳዲስ ዜናዎች እንዲሁም ከያኒያን ልዩ ልዩ የጥበብ ክህሎቶቻቸውን ከተለያየ የዓለም ክፍል መካ ላይ ለተሰባሰበው ህዝብ ያቀርቡ ነበር፡፡ በወቅቱ እነዚህን ክዋኔዎች በምታስተናግደው መካ ህይወት ደስ የሚል ነበር፡፡
በዘመኑ የአረብ ማህበረሰብ ዝናንና እውቅናን ለመጎናፀፍ ዘወትር
የሚጠመድበትን የውድድር ህይወት ከግብ ለማድረስ እገዛ ያደርጉልኛል በሚል እምነት ለወንድ ልጆች ይሰጠው የነበረው ቦታ የላቀ፤ ለሴት ልጆች ነበረው ክብርም ሆነ ፍላጎት ደግሞ እጅግ የወረደ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ሚስቶቻቸው ሴት ልጅ በሚወልዱ በአብዛኛዎቹ የዐረብ አባቶች ዘንድበከፍተኛ ሐፍረት መሸማቀቅ አሊያም በብስጭት ቤተሰቡን ማወክ በወቅቱ የተለመደ ሁኔታ ነበር። በዚህም ሳያበቁ አባቶች የሚወለዱ ሴት ልጆቻቸውን ከነህይወታቸው በመቅበር ያስወግዷቸው ነበር፡፡ ያም ሆኖ የዚሁ ማህበረሰብ አባል የሆኑት ሁለቱ ባልንጀራ ልጃገረዶች ግን የገጠማቸው የህይወት እድል የተለየ ሆነ፡፡
ባለፀጋ ከሆኑ የተከበሩ ቤተሰቦች የተገኙት አሚና እና ኸዲጃ በወላጆቻቸው ዘንድ በእጅጉ የሚወደዱ ነበሩ፡፡ እናም በማህበረሰቡ ውስጥ የሚፈፀሙትን መልካምም ሆነ ክፉ ተግባራት በዓይናቸው እየተመለከቱ ነበር ያደጉት፡፡
በወቅቱ ጣኦታትን የሚገዛው ሁሉም የመካ ህዝብ አልነበረም፡፡
ጥንታዊ የእምነት መጽሐፍትን የሚያነቡ ፧ ህግጋቱንም አጥብቀው
የሚተገብሩና ከፍልስጤም፣ከየመንና ከየስሪብ የመጡ ሰዎችም መካ ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ ከዚህም ሌላ ነብዩላህ ዒሣን የሚከተሉ
ክርስቲያኖችም ከመካ ነዋሪዎች መካከል ነበሩ፡፡ የክርስትና እምነት
መጽሐፍትን ጠንቅቆ ያጠናው አላህን፣ ነብያቱን፣ መላኢካዎቹንና
የመጨረሻውን የፍርድ ቀንን በተመለከተ አያሌ እውቀቶችን ያካበተው የኸዲጃ የአጎት ልጅ ወራቃ ቢን ነውፈል በወቅቱ መካ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ከዚህም ባሻገር ከመካ ህዝብ መካከል የይሁዳ ወይም የክርስትና እምነት ተከታዮች ሳይሆኑ እንደ ኢብራሂም አንድ አምላክን በመፈለግ ዘወትር ለእርሱ ብቻ የሚፀልዩ ሰዎችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች "ሐነፊዎች" በሚል
ስያሜ ነበር የሚጠሩት፡፡
#ክፍል_አንድ
ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ወደዚህች ምድር ከመምጣታቸው በፊት ሁለት ወዳጅ የሆኑ ልጃገረዶች መካ ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህ እጅግ ቅርብ የሆነ ወዳጅነት የነበራቸው ልጃገረዶች አሚና እና ኸዲጃ ይባላሉ። መካ የተቆረቆረችው ግብፅን፣ ፍልስጤምን፣ ፋርስን፣ ሜሶፖቶሚያን፣ ህንድንና አፍሪካን በሚያገናኙና የአካባቢው አገራት ቁልፍ የንግድ መዳረ በነበሩ መንገዶች ላይ ነበር፡፡ በወቅቱ ከመላው ዓለም የሚመጡ የተለያዩ ሸቀጦች የሚቀርቡበት ዓመታዊ የገበያ ልውውጥም በዚሁ አካባቢ ይካሄድ
ነበር። እዚያው መካ ውስጥ ደግሞ ሰዎች አንድ ፈጣሪን ብቻ ያመልኩበት ዘንድ በኢብራሂምና እስማኢል የተገነባው ጥንታዊው የአላህ(ሱ.ወ) ቤት ካዕባ ይገኝ ነበር፡፡
ካዕባ በዓለም ውስጥ ከሚገኙት እጅግ ጥንታዊ የሆኑ ህንፃዎች ሁሉ ቀዳሚው በመሆኑ የመላው ዐረብ ህዝብ የኩራት ምንጭ ተደርጎም ይወሰድ ነበር፡፡ ያም ሆኖ ግን ዐረቦች የኢብራሂምን ንፁህ የሆነ እምነት በመዘንጋት እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ጣኦታት አንፀው በዚህ ታሪካዊ የካዕባ ህንፃ ውስጥ በማኖር ያመልኩ ነበር፡፡ እናም ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ህዝብ ሸቀጡን ገበያው ላይ በማቅረብ ለመሸጥና ለራሱ የሚፈልገው ካለ ደግሞ ከሌላው ለመሸመት እንደዚሁም በአላህ ቤት ካዕባ በመገኘት የሐጅ ስረዓተ-ጸሎትን ለመከወን በየዓመቱ ወደመካ ይጎርፍ ነበር፡፡ በዚሁ ወቅት የተለያዩ ገጣሚያን የግጥም ድርሰቶቻቸውን በማንበብ እርስ በእርሳቸው የሚወዳደሩበት ትርኢትም የተለመደ ነበር፡፡ መንገደኛ የታሪክ ተራኪዎችም ከየመጡባቸው አካባቢዎች ያጠናቀሯቸውን አዳዲስ ዜናዎች እንዲሁም ከያኒያን ልዩ ልዩ የጥበብ ክህሎቶቻቸውን ከተለያየ የዓለም ክፍል መካ ላይ ለተሰባሰበው ህዝብ ያቀርቡ ነበር፡፡ በወቅቱ እነዚህን ክዋኔዎች በምታስተናግደው መካ ህይወት ደስ የሚል ነበር፡፡
በዘመኑ የአረብ ማህበረሰብ ዝናንና እውቅናን ለመጎናፀፍ ዘወትር
የሚጠመድበትን የውድድር ህይወት ከግብ ለማድረስ እገዛ ያደርጉልኛል በሚል እምነት ለወንድ ልጆች ይሰጠው የነበረው ቦታ የላቀ፤ ለሴት ልጆች ነበረው ክብርም ሆነ ፍላጎት ደግሞ እጅግ የወረደ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ሚስቶቻቸው ሴት ልጅ በሚወልዱ በአብዛኛዎቹ የዐረብ አባቶች ዘንድበከፍተኛ ሐፍረት መሸማቀቅ አሊያም በብስጭት ቤተሰቡን ማወክ በወቅቱ የተለመደ ሁኔታ ነበር። በዚህም ሳያበቁ አባቶች የሚወለዱ ሴት ልጆቻቸውን ከነህይወታቸው በመቅበር ያስወግዷቸው ነበር፡፡ ያም ሆኖ የዚሁ ማህበረሰብ አባል የሆኑት ሁለቱ ባልንጀራ ልጃገረዶች ግን የገጠማቸው የህይወት እድል የተለየ ሆነ፡፡
ባለፀጋ ከሆኑ የተከበሩ ቤተሰቦች የተገኙት አሚና እና ኸዲጃ በወላጆቻቸው ዘንድ በእጅጉ የሚወደዱ ነበሩ፡፡ እናም በማህበረሰቡ ውስጥ የሚፈፀሙትን መልካምም ሆነ ክፉ ተግባራት በዓይናቸው እየተመለከቱ ነበር ያደጉት፡፡
በወቅቱ ጣኦታትን የሚገዛው ሁሉም የመካ ህዝብ አልነበረም፡፡
ጥንታዊ የእምነት መጽሐፍትን የሚያነቡ ፧ ህግጋቱንም አጥብቀው
የሚተገብሩና ከፍልስጤም፣ከየመንና ከየስሪብ የመጡ ሰዎችም መካ ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ ከዚህም ሌላ ነብዩላህ ዒሣን የሚከተሉ
ክርስቲያኖችም ከመካ ነዋሪዎች መካከል ነበሩ፡፡ የክርስትና እምነት
መጽሐፍትን ጠንቅቆ ያጠናው አላህን፣ ነብያቱን፣ መላኢካዎቹንና
የመጨረሻውን የፍርድ ቀንን በተመለከተ አያሌ እውቀቶችን ያካበተው የኸዲጃ የአጎት ልጅ ወራቃ ቢን ነውፈል በወቅቱ መካ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ከዚህም ባሻገር ከመካ ህዝብ መካከል የይሁዳ ወይም የክርስትና እምነት ተከታዮች ሳይሆኑ እንደ ኢብራሂም አንድ አምላክን በመፈለግ ዘወትር ለእርሱ ብቻ የሚፀልዩ ሰዎችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች "ሐነፊዎች" በሚል
ስያሜ ነበር የሚጠሩት፡፡
👍36❤11👏9🥰1😱1
#ሁለቱ_ልጃገረዶች
#ክፍል_ሁለት
ያም ሆኖ ግን በወቅቱ የሚታዩትን የተለያዩ ጥርጣሬዎችና
አለመግባባቶች የሚያስወግድ ብሎም አዲስ የእምነት መንገድን
የሚያመላክት ሌላ ነብይ ወደፊት ከአላህ(ሱ.ወ) ዘንድ ይላካል የሚል ተስፋ በብዙዎች ዘንድ ነበር፡፡ ታዲያ ይህ በብዙዎች አዕምሮ ውስጥ የሚዋልለው ተስፋ በአሚናህና ኸዲጃ ሀሳብ ውስጥም ዘወትር ይመላለሳል፡፡ እናም አሚና እና ኸዲጃ ይህንን ጉዳይ አንስተው በተነጋገሩ ቁጥር ወደፊት ይመጣል ተብሎ የሚጠበቀው የአላህ መልዕክተኛ በእኛ የህይወት ዘመን ውስጥ ይመጣ ይሆን? ይህ ነብይ በሚመጣበት ወቅት ምንኛ የተቀደሰ
ዘመን እንደሚሆን ማየት ያስቸኩላል፤ የሚጠበቀው ነብይ በዒሣ የነብይነት ዘመን እንደተስተዋለው ሰዎች እርስ በእርስ እንዲዋደዱና ፍፁም ቅን በሆነ መንፈስ እንዲመሩ ያደርጋል ልክ እንደሙሳ ሰዎች ልጆቻቸውን ጠንካራ ህግም ተግባራዊ ያደርግ ይሆናል፤ ወይም እንደ ኢብራም ሁሉ ከመግደል እንዲታቀቡና አንዱ ሌላውን ከመስረቅ እንዲቆጠብ የሚያስገድድ ሰዎች ለአንድ አምላክ ብቻ እንዲገዙና እርሱን ብቻ እንዲጠጉ ያስተምርም ይሆናል ግን ህዝቡ ጆሮውን ቢነፍገውስ? በማለት ያስቡ ነበር። ይህንንም ተከትሎ የከዚህ ቀደምቶቹን ነብያት አንቀበልም ከማለት አልፈው አንዳንዶቹን የገደሉ እምቢተኛ ህዝቦች የተከተላቸውን ቅጣት
በማሰብም ሁለቱ ልጃገረዶች በፍርሃት ይጨነቁ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከብዙ ዓመታት በፊት አላህ ነብዩላህ ኑህን፣ ተከታዮቹን የተለያዩ ፍጡራኖቹንና እንስሳትን ከጥፋት ማዳኑን ያስታውሳሉ፤ ከዚህ አንፃር አላህ በእርሱ አንድነት የሚያምኑ ፍጡራኑን ከመርዳት ወደኋላ እንደማይል በማሰብ ይፅናናሉ፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን አሚና በእንቅልፏ የገጠማትን እንግዳ የሆነ
ህልም ለቅርብ ወዳጇ ኸዲጃ ተረከችላት፡፡ አሚና በህልሟ ወንድ ልጅ መውለዷን፤ ልጁም አድጎ የአላህ ነብይ መሆኑን ነበር ያየችው፡፡ በሚያስደንቅ ሁኔታ በዚያው ሌሊት ኸዲጃም በተመሳሳይ እንግዳ ነገር ያለበትን ህልም አየች። ኸዲጃ የአላህ መልዕክተኛ ተደርጎ ከተላከው ሰው ጋር ጋብቻ መመስረቷን፤ ነብዩ የተላከበትን ዓላማ ለመፈፀም በሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ በሚገጥሙት የተለያዩ ፈተናዎች የበኩሏን ድጋፍ
ማድረጓን የሚያሳይ ህልም ነበር በእንቅልፏ ያየችው፡፡ ልጃገረዶች
በተለዋወጧቸው እንግዳ የሆኑ የህልም ክስተቶች ግራ ተጋቡ፡፡ ነገር ግን ከህልሞቹ ጋር በተያያዘ አንድ ልዩ የሆነ መልዕክት እንዳለ ውስጣቸው ነግሯቸዋል። እነዚህ ልጃገረዶች ልቦቻቸው የነገሯቸው እውነት ምን ይሆን? ኸዲጃ ለአቅመ ሄዋን ስትደርስ ወረቃ ቢን ነውፈልን ታገባለች በማለት ወላጆቿ ይናገሩ እንደነበር ኸዲጃ ታስታውሳለች። ያም ሆኖ ግን ወረቃ ትዳር የመያዝ እቅድ እንደሌለውና ህይወቱን መንኩሶ እንደሚያሳልፍ ገለፀ፡፡
ሁለቱ ልገረዶች ትዳር መመስረት የሚጠበቅባቸው ወቅት ደረሰ፡፡
ወላጆቻቸውም በጊዜው ተቀባይነት በነበረው ሥርዓትና ደንብ መሰረት ለእያንዳንዳቸው ይሆናሉ ያሏቸውን ባሎች መረጡ፡፡ በዚህ ወቅት ነበር በልጃገረዶቹ ህይወት ውስጥ እጅግ የተለየ ስሜት የተፈጠረው፡፡ህይወታቸው ወደ አዲስና አስደሳች የሆነ ምዕራፍ ተሸጋገረ። አሚና በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ የተከበሩ የነበሩትን የአብዱል ሙጠሊብ ልጅ አብደላህን አገባች። ባልንጀራዋ ኸዲጃ በበኩሏ ወጣት ከሆነው ነጋዴ አቡ-ሐላ ጋር በትዳር ተሳሰረች። ሁለቱም በመሰረቱት አዲስ ጎጆ እጅግ ደስተኛ ሆኑ።
ያም ሆኖ ግን ይህ የደስታ ህይወት ከአሚና ጋር ብዙም ሳይዘልቅ
በአጭሩ ተቀጨ፡፡ ገና ሙሽርነቱን አጣጥሞ ሳይጨርስ ለንግድ ስራ ሩቅ አገር የተጓዘው የአሚና ባል እንደወጣ ሳይመለስ ቀረ። መንገድ ላይ በድንገት ህይወቱ አልፋ የስሪብ ውስጥ ተቀበረ። አባቱ አብዱል ሙጦሊብ አሚናን ለማፅናናት ብዙ ጥረት አደረጉ፡፡ ስለልጃቸው ሚስት ህልምና ሀሳብ ጠንቅቀው የሚያውቁ ከመሆኑም በተጨማሪ የምትወልደው ልጅ አንድ ቀን ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የተለየ ሰው እንደሚሆን እራሳቸው ጭምር ህልም አይተው ነበር፡፡
አሚና በባሏ መለየት ሳቢያ የተፈጠረባት መሪር ሐዘን ምንም ዓይነት መሻሻል ሳያሳይ ወራቶች ተቆጥረው ወንድ ልጅ ወለደች፡፡ ዐብዱል ሙጠሊብም ህፃኑን ሙሐመድ የሚል ስም አወጡለት፤ የሙሐመድን መወለድ ምክንያት በማድረግም ድል ያለ ድግስ አዘጋጁ፡፡ ሕፃኑ ያለአባት እንደሚያድግ ለማንም ግልፅ ነበር፡፡
በወቅቱ ጨቅላ ሕፃናት በተለይ የመጀመሪያ ዓመት እድሜያቸውን
በተጨናነቀና አቧራ በሚበዛባቸው ከተሞች እንዲያሳልፉ አይደረግም ነበርና ብዙውን ጊዜ ሕፃናቱ ወደባዲያህ ይላኩ ነበር፡፡ እናም የባዲያህ ሰዎች በጎቻቸውንና ግመሎቻቸውን ለመሸጥ ወደመካ በመጡበት ወቅት አሚናህ ለሕፃኑ ልጇ የምትሆንና ሐሊማ የተባለች ሞግዚት አገኘች፡፡ ሙሐመድም በረሃ ውስጥ ለምትኖረው ለዚህች የባዲያህ ሞግዚት ተሰጠ፡፡
ምንም እንኳ ገና የተወለደ ጨቅላ ሕፃንን ከእናት መለየት ለእናት
እጅግ የሚከብድ ቢሆንም ሕፃኑ ወደ ባዲያ መላኩ ጤናማ በሆነ የአየር ፀባይና በተረጋጋ አካባቢ እንዲያድግ እንደዚሁም በአካባቢ ህዝብ ዘንድ የሚነገረውን ትክክለኛ የአረብኛ ቋንቋ በአግባቡ እንዲለምድ የሚያስችለው በመሆኑ ለህፃኑ መልካም እድገት የተሻለ ነበር።
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል...
#ክፍል_ሁለት
ያም ሆኖ ግን በወቅቱ የሚታዩትን የተለያዩ ጥርጣሬዎችና
አለመግባባቶች የሚያስወግድ ብሎም አዲስ የእምነት መንገድን
የሚያመላክት ሌላ ነብይ ወደፊት ከአላህ(ሱ.ወ) ዘንድ ይላካል የሚል ተስፋ በብዙዎች ዘንድ ነበር፡፡ ታዲያ ይህ በብዙዎች አዕምሮ ውስጥ የሚዋልለው ተስፋ በአሚናህና ኸዲጃ ሀሳብ ውስጥም ዘወትር ይመላለሳል፡፡ እናም አሚና እና ኸዲጃ ይህንን ጉዳይ አንስተው በተነጋገሩ ቁጥር ወደፊት ይመጣል ተብሎ የሚጠበቀው የአላህ መልዕክተኛ በእኛ የህይወት ዘመን ውስጥ ይመጣ ይሆን? ይህ ነብይ በሚመጣበት ወቅት ምንኛ የተቀደሰ
ዘመን እንደሚሆን ማየት ያስቸኩላል፤ የሚጠበቀው ነብይ በዒሣ የነብይነት ዘመን እንደተስተዋለው ሰዎች እርስ በእርስ እንዲዋደዱና ፍፁም ቅን በሆነ መንፈስ እንዲመሩ ያደርጋል ልክ እንደሙሳ ሰዎች ልጆቻቸውን ጠንካራ ህግም ተግባራዊ ያደርግ ይሆናል፤ ወይም እንደ ኢብራም ሁሉ ከመግደል እንዲታቀቡና አንዱ ሌላውን ከመስረቅ እንዲቆጠብ የሚያስገድድ ሰዎች ለአንድ አምላክ ብቻ እንዲገዙና እርሱን ብቻ እንዲጠጉ ያስተምርም ይሆናል ግን ህዝቡ ጆሮውን ቢነፍገውስ? በማለት ያስቡ ነበር። ይህንንም ተከትሎ የከዚህ ቀደምቶቹን ነብያት አንቀበልም ከማለት አልፈው አንዳንዶቹን የገደሉ እምቢተኛ ህዝቦች የተከተላቸውን ቅጣት
በማሰብም ሁለቱ ልጃገረዶች በፍርሃት ይጨነቁ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከብዙ ዓመታት በፊት አላህ ነብዩላህ ኑህን፣ ተከታዮቹን የተለያዩ ፍጡራኖቹንና እንስሳትን ከጥፋት ማዳኑን ያስታውሳሉ፤ ከዚህ አንፃር አላህ በእርሱ አንድነት የሚያምኑ ፍጡራኑን ከመርዳት ወደኋላ እንደማይል በማሰብ ይፅናናሉ፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን አሚና በእንቅልፏ የገጠማትን እንግዳ የሆነ
ህልም ለቅርብ ወዳጇ ኸዲጃ ተረከችላት፡፡ አሚና በህልሟ ወንድ ልጅ መውለዷን፤ ልጁም አድጎ የአላህ ነብይ መሆኑን ነበር ያየችው፡፡ በሚያስደንቅ ሁኔታ በዚያው ሌሊት ኸዲጃም በተመሳሳይ እንግዳ ነገር ያለበትን ህልም አየች። ኸዲጃ የአላህ መልዕክተኛ ተደርጎ ከተላከው ሰው ጋር ጋብቻ መመስረቷን፤ ነብዩ የተላከበትን ዓላማ ለመፈፀም በሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ በሚገጥሙት የተለያዩ ፈተናዎች የበኩሏን ድጋፍ
ማድረጓን የሚያሳይ ህልም ነበር በእንቅልፏ ያየችው፡፡ ልጃገረዶች
በተለዋወጧቸው እንግዳ የሆኑ የህልም ክስተቶች ግራ ተጋቡ፡፡ ነገር ግን ከህልሞቹ ጋር በተያያዘ አንድ ልዩ የሆነ መልዕክት እንዳለ ውስጣቸው ነግሯቸዋል። እነዚህ ልጃገረዶች ልቦቻቸው የነገሯቸው እውነት ምን ይሆን? ኸዲጃ ለአቅመ ሄዋን ስትደርስ ወረቃ ቢን ነውፈልን ታገባለች በማለት ወላጆቿ ይናገሩ እንደነበር ኸዲጃ ታስታውሳለች። ያም ሆኖ ግን ወረቃ ትዳር የመያዝ እቅድ እንደሌለውና ህይወቱን መንኩሶ እንደሚያሳልፍ ገለፀ፡፡
ሁለቱ ልገረዶች ትዳር መመስረት የሚጠበቅባቸው ወቅት ደረሰ፡፡
ወላጆቻቸውም በጊዜው ተቀባይነት በነበረው ሥርዓትና ደንብ መሰረት ለእያንዳንዳቸው ይሆናሉ ያሏቸውን ባሎች መረጡ፡፡ በዚህ ወቅት ነበር በልጃገረዶቹ ህይወት ውስጥ እጅግ የተለየ ስሜት የተፈጠረው፡፡ህይወታቸው ወደ አዲስና አስደሳች የሆነ ምዕራፍ ተሸጋገረ። አሚና በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ የተከበሩ የነበሩትን የአብዱል ሙጠሊብ ልጅ አብደላህን አገባች። ባልንጀራዋ ኸዲጃ በበኩሏ ወጣት ከሆነው ነጋዴ አቡ-ሐላ ጋር በትዳር ተሳሰረች። ሁለቱም በመሰረቱት አዲስ ጎጆ እጅግ ደስተኛ ሆኑ።
ያም ሆኖ ግን ይህ የደስታ ህይወት ከአሚና ጋር ብዙም ሳይዘልቅ
በአጭሩ ተቀጨ፡፡ ገና ሙሽርነቱን አጣጥሞ ሳይጨርስ ለንግድ ስራ ሩቅ አገር የተጓዘው የአሚና ባል እንደወጣ ሳይመለስ ቀረ። መንገድ ላይ በድንገት ህይወቱ አልፋ የስሪብ ውስጥ ተቀበረ። አባቱ አብዱል ሙጦሊብ አሚናን ለማፅናናት ብዙ ጥረት አደረጉ፡፡ ስለልጃቸው ሚስት ህልምና ሀሳብ ጠንቅቀው የሚያውቁ ከመሆኑም በተጨማሪ የምትወልደው ልጅ አንድ ቀን ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የተለየ ሰው እንደሚሆን እራሳቸው ጭምር ህልም አይተው ነበር፡፡
አሚና በባሏ መለየት ሳቢያ የተፈጠረባት መሪር ሐዘን ምንም ዓይነት መሻሻል ሳያሳይ ወራቶች ተቆጥረው ወንድ ልጅ ወለደች፡፡ ዐብዱል ሙጠሊብም ህፃኑን ሙሐመድ የሚል ስም አወጡለት፤ የሙሐመድን መወለድ ምክንያት በማድረግም ድል ያለ ድግስ አዘጋጁ፡፡ ሕፃኑ ያለአባት እንደሚያድግ ለማንም ግልፅ ነበር፡፡
በወቅቱ ጨቅላ ሕፃናት በተለይ የመጀመሪያ ዓመት እድሜያቸውን
በተጨናነቀና አቧራ በሚበዛባቸው ከተሞች እንዲያሳልፉ አይደረግም ነበርና ብዙውን ጊዜ ሕፃናቱ ወደባዲያህ ይላኩ ነበር፡፡ እናም የባዲያህ ሰዎች በጎቻቸውንና ግመሎቻቸውን ለመሸጥ ወደመካ በመጡበት ወቅት አሚናህ ለሕፃኑ ልጇ የምትሆንና ሐሊማ የተባለች ሞግዚት አገኘች፡፡ ሙሐመድም በረሃ ውስጥ ለምትኖረው ለዚህች የባዲያህ ሞግዚት ተሰጠ፡፡
ምንም እንኳ ገና የተወለደ ጨቅላ ሕፃንን ከእናት መለየት ለእናት
እጅግ የሚከብድ ቢሆንም ሕፃኑ ወደ ባዲያ መላኩ ጤናማ በሆነ የአየር ፀባይና በተረጋጋ አካባቢ እንዲያድግ እንደዚሁም በአካባቢ ህዝብ ዘንድ የሚነገረውን ትክክለኛ የአረብኛ ቋንቋ በአግባቡ እንዲለምድ የሚያስችለው በመሆኑ ለህፃኑ መልካም እድገት የተሻለ ነበር።
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል...
👍37❤8
#ሁለቱ_ልጃገረዶች
ክፍል ሦስት
በመጀመሪያ ሙሽርነቷን በቅጡ ሳታጣጥም ባሏን በሞት ተነጠቀች
እሁን ደግሞ ምንም ያህል እቅፏ ውስጥ አስገብታ ፍቅሩን ያላጣጣመችው ልጇ ከአጠገቧ ርቆ ሄዷል። በመሆኑም ሙሐመድ ከተወለደ በኋላ የነበሩትን ዓመታትም አሚና ያሳለፈችው ደስታ የሚባል ነገር እርቋት ነበር። ያም ሆኖ በመልካም ሁኔታ ከሚያድገው ጠንካራና ጤኖማ ልጅ በተያያዘ ወደፊት የሚገጥማትን እጀግ ደስታ የሞላበትን ህይወት እያሰበችም ትፅናና ነበር፡፡ ከዚህም ሌላ በወቅቱ ምንም አይዞሽ የሚላት
ወገን የሌላት ብቸኛ ሴት ሳትሆን በባሏ ቤተሰቦች ከፍተኛ ፍቅርና ርህራሄ እየተሰጣት ከእነርሱው ጋር ተቀላቅላ የምትኖር መሆኗም ሐዘኗን እንድትረሳ ያደርጋት ነበር፡፡
እንዲያም ሆኖ ግን የሙሐመድ ሞግዚት ሕፃኑን በየጊዜው እናቱ
ዘንድ እያመጣች ታስጎበኛት ነበር። በነዚህ ወቅቶች ታዲያ ጨቅላው ሙሐመድ በሚያሳያቸው እንግዳ የሆኑ ባህሪያት ዘወትር የምትደነቀው ሞግዚቷ በየጊዜው የምትታዘባቸውን እውነታዎች ለእናቱ ታጫውታት ነበር። ሙሐመድ እርሷ ዘንድ ከመጣ በኋላ በጎቿና ግመሎቿ በእጥፍ መጨመራቸው ከአሁን ወዲያ ምንም ዓይነት የዱንያ ችግር ሊገጥማት እንደማይችል ሁኔታው ሁሉ እጅግ ተዓምር እንደሆነባት ሞግዚቷ ለአሚና ተርካላታለች፡፡ አንድ ቀን እንዲያውም ሕፃኑ ሙሐመድ ከቤት ውጭ እየተጫወተ ሳለ አንድ መላዕክ አጠገቡ መጥቶ ልቡን እንዳጠበለት የተነገራት መሆኑንም ለአሚና አውርታላታለች፡፡ አሚና እነዚህን ተዓምራት በሰማች ቁጥር ታዲያ ልቧ ከአካሏ የሚወጣ እስኪመስል ድረስ ይነጥራል፤ ወደ ልጃገረድነት የእድሜ ትዝታዎቿ በመንጎድም ገጥሟት
የነበረውን እንግዳ የሆነ ህልም ታስታውሳለች የዚያን ጊዜው ግራ
የሚያጋባ ህልም እውን እየሆነ መሆኑን በማጤን ታስባለች፡፡
ከአራት ረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ በህይወቷ ውስጥ አዲስ ስሜት ተፈጠረ፡፡ ዘወትር ትናፍቀው የነበረውን ልጇን በእቅፏ አስገባች፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ደስተኛ ሆነች። አሚና ለሙሐመድ ዘወትር ስለአባቱ ትተርክለት ነበር፡፡ እድሜው ስድስት ዓመት ሲሞላ አሚና ሙሐመድን ወደ የስሪብ ይዛው ሄደች፡፡ በዚያ የሚኖሩ ዘመዶቿን ጎበኘች ልጇም የአባቱን ቀብር እንዲያይ አደረገች፡፡ ነገር ግን ልጇን ይዛ ወደ መካ ስትመለስ ሌላ አዲስ ነገር ግን የሚያሳዝን የህይወት እውነት ተከሰተ። አሚና በሰላም ከወጣችበት መካ ሳትመለስ መንገድ ላይ ቀረች፡፡ በድንገት ህይወቷ አለፈ። ገና ይህንን ምድር ሳይቀላቀል አባቱን የተነጠቀው ሙሐመድ መቅመስ የጀመረውን የእናቱን ፍቅርና እንክብካቤ በወጉ ሳያጣጥም እናቱንም አጣ። በዚህም የተነሳ የሙሐመድ የህይወት መንገድ በድጋሚ መንገዱን ለመቀየር ተገደደ። ሙሐመድ በአያቱ አብዱል ሙጠሊብ ጥበቃ ስር መኖር ጀመረ።
የአሚና አብሮ አደግና የልብ ወዳጅ የነበረችው ኸዲጃም የተለየች
ውጣት ነበረች። ገና ሕፃን ሳለች ጀምሮ የነገሮችን እውነታ የመከታተልና የማወቅ ጉጉቷ ከእድሜዋ የላቀ ነበር ሁልጊዜ አባቷ ከሌሎች ነጋዴዎች ወይም ወንድሞቿ ጋር የስራ ጉዳዮችን በማንሳት በሚወያዩበት ወቅት በአትኩሮት በመከታተል በአዕምሮዋ ትይዝ ነበር። አንዳንዴ እንዲያውም በዚህ ዓይነቶቹ አጋጣሚዎች በምትከታተለው ውይይት ውስጥ ሳይገቧት የሚቀሩና ግር የሚሏት ጉዮች ሲገጥሟት የመጠየቅ ልምድም ነበራት፡፡
በዚህ የማወቅ ጉጉቷና ፍላጎቷ ሁሌም የሚደነቁት አባቷ ታዲያ
የምትጠይቃቸውን ነገር ሁሉ በአግባቡ ነበር የሚያብራሩላት፡፡
ኸዲጃ በተለያዩ የህይወት ጉዮች ዙሪያ በምትሰጠው ጠቃሚ
ምክሮችና አዳዲስ ሀሳቦች የወጣትነትና የመጀመሪያ ባሏ አቡ ሐላልንም ያስደንቀው ነበር፡፡ ኸዲጃ በወጣትነት እድሜዋ ከመሰረተችው ትዳሯ የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ሁለት ወንድ ልጆችን አፍርታለች። ያም ሆኖ ግን ባሏ አብሯት የቆየው ለተወሰኑ ዓመታት ብቻ ነበር። በህልፈተ ሞት ኸዲጃን ተሰናበታት፡፡
የመጀመሪያ ባሏን በሞት ያጣችው ኸዲጃ ያለባል የቆየችው እጅግ አጭር ለሆነ ጊዜ ብቻ ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሌላ ባል አገባች።
ሁለተኛው ባሏ አጢቅ እንደ እርሷ ሁሉ ሩህሩህ ልብ ያለው! ተመሳሳይ ፍላጎትን የሚጋራ ጥሩ ሰው ነበር፡፡ ኸዲጃም አዲሱ ባሏን በተለያዩ ጉዳዮች ማገዝን የዘወትር ተግባሯ አድርጋ ነበር አብራው የምትኖረው፡፡ ኸዲጃ ትዳር እንደመሰረተች በነበረው የመጀመሪያ ዓመት ላይ ሴት ልጅ ወልዳ እንኳ ባሏን በሥራ ከማገዝ የተቆጠበችበት ጊዜ አልነበረም፡፡ በሚኖራት ትርፍ ጊዜ ደግሞ ወደ ካዕባ በመሄድ ፀሎት ታደርግ ነበር። ኸዲጃና ቤተሰቡ በመተጋገዝ፣ በመተዛዘንና በደስታ ዓመታትን ካሳለፉ በኋላ ግን አንድ ፈተና ገጠማቸው። መካ ውስጥ ክፉ ወረርሽኝ ተከሰተ።
ብዙ ሰዎችም በወረርሽኙ ተይዘው ለበሽታ ተዳረጉ በወረርሽኙ ሳቢያ በርካቶች ሞቱ ያም ሆኖ በመድኃኒት እገዛ የተወሰኑ ሰዎች በሽታውን በማሸነፍ ህይወታቸውን ማትረፍ ተቻለ። የወረርሽኙን መከስት ተከትሎ ኸዲጃና ባሏ ሆስፒታል አቋቋሙ። በራሳቸው ወጪም ሐኪም ቀጥረውና የሚያስፈልጉ መድኃኒቶችን ገዝተው አያሌዎችን ከሞት ታደጉ፡፡ ባልና ሚስቱ በሆስፒታሉ የሚረዱ ታካሚዎችን በመንከባከብ ይሳተፉም ነበር። ጥቂት ቆይቶ ወረርሽኙ ከመካ ቢጠፋም የኸዲጃ የትዳር ጓደኛ አጢቅ ታመመ፡፡ እናም ሚስቱን ከሶስት ልጆች ጋር ጥሎ ሞተ። በዚህም የተነሳ ኸዲጃ በዋነኛነት በባሏ ይካሄድ የነበረውን የንግድ ሥራ ኃላፊነት መረከብ ግድ ሆነባት። ባሏ በህይወት በነበረበት ወቅት በሥራው እያገዘችው ስላሳለፈች ልጆቿ አድገው ኃላፊነቱን እስኪረከቡ ድረስ የንግድ ስራውን በራሷ አቅም መቀጠል አልከበዳትም ነበር፡፡ በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ ሴት ነጋዴን ማየት የተለመደ ስላልነበር በመጀመሪያ ላይ አንዳንድ አሉታዊ አስተያየቶች ይሰነዘሩ ነበር፡፡ ቆይቶ ግን የኸዲጃን ነጋዴ መሆን እየለመዱትና እየተቀበሉት መጡ፡፡ ኸዲጃ የሚገጥሟትን መሰናክሎች በአግባቡ በማለፍ የባሏን መዋዕለ ንዋይ ተጠቅማ የንግድ ሥራውን በአጥጋቢ መልኩ መምራት ቻለች። ሴት ከመሆኗ ጋር የሚገጥሟትን ፈተናዎችንም እየተጋፈጠች አሳለፈች፡፡ ኃብቷን በባለቤትነት ለመያዝ በመቋመጥ ለጋብቻ ይቀርቡ የነበሩ የግለሰቦች ጥያቄዎችንም በትዕግስትና በብልሃት አሸነፈች፡፡ ኸዲጃ ከነበረችበት ሁኔታ ጋር በተያያዘ ግን አንድ ልትወጣው ያልቻለችው ነገር ገጥሟት ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ሴቶች ለንግድ ሥራ ወደሌላ ሩቅ አገር መጓዝ አይችሉም ነበር፡፡ ኸዲጃ ለዚህ ሥራ ማድረግ የምትችለው ተወካይ መቅጠር ብቻ
ነበር። እናም ኸዲጃ ይህንን ስልት በመጠቀም ነበር የሩቅ አገር የንግድ ተግባሯን የምትፈፅመው። ሁል ጊዜ በየዓመቱ ወደሶሪያ በሚደረገው የነጋዴዎች ጉዞ ላይ እርሷን ሆኖ የንግድ ስራውን የሚያካሄድ ወጣት በመቅጠር ከነጋዴዎቹ ጋር አብሮ እንዲጓዝ ትልክ ነበር። ያም ሆኖ ግን ኸዲጃ በውክልና የምታካሄደው
የንግድ ተግባር ብዙውን ጊዜ አትረካም ነበር፡፡ ኸዲጃ እርካታውን ያጣችው ወጣት ወኪሎቿ ብልህነትና ብቃት ጎድሏቸው ስራውን በአግባቡ...
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
ክፍል ሦስት
በመጀመሪያ ሙሽርነቷን በቅጡ ሳታጣጥም ባሏን በሞት ተነጠቀች
እሁን ደግሞ ምንም ያህል እቅፏ ውስጥ አስገብታ ፍቅሩን ያላጣጣመችው ልጇ ከአጠገቧ ርቆ ሄዷል። በመሆኑም ሙሐመድ ከተወለደ በኋላ የነበሩትን ዓመታትም አሚና ያሳለፈችው ደስታ የሚባል ነገር እርቋት ነበር። ያም ሆኖ በመልካም ሁኔታ ከሚያድገው ጠንካራና ጤኖማ ልጅ በተያያዘ ወደፊት የሚገጥማትን እጀግ ደስታ የሞላበትን ህይወት እያሰበችም ትፅናና ነበር፡፡ ከዚህም ሌላ በወቅቱ ምንም አይዞሽ የሚላት
ወገን የሌላት ብቸኛ ሴት ሳትሆን በባሏ ቤተሰቦች ከፍተኛ ፍቅርና ርህራሄ እየተሰጣት ከእነርሱው ጋር ተቀላቅላ የምትኖር መሆኗም ሐዘኗን እንድትረሳ ያደርጋት ነበር፡፡
እንዲያም ሆኖ ግን የሙሐመድ ሞግዚት ሕፃኑን በየጊዜው እናቱ
ዘንድ እያመጣች ታስጎበኛት ነበር። በነዚህ ወቅቶች ታዲያ ጨቅላው ሙሐመድ በሚያሳያቸው እንግዳ የሆኑ ባህሪያት ዘወትር የምትደነቀው ሞግዚቷ በየጊዜው የምትታዘባቸውን እውነታዎች ለእናቱ ታጫውታት ነበር። ሙሐመድ እርሷ ዘንድ ከመጣ በኋላ በጎቿና ግመሎቿ በእጥፍ መጨመራቸው ከአሁን ወዲያ ምንም ዓይነት የዱንያ ችግር ሊገጥማት እንደማይችል ሁኔታው ሁሉ እጅግ ተዓምር እንደሆነባት ሞግዚቷ ለአሚና ተርካላታለች፡፡ አንድ ቀን እንዲያውም ሕፃኑ ሙሐመድ ከቤት ውጭ እየተጫወተ ሳለ አንድ መላዕክ አጠገቡ መጥቶ ልቡን እንዳጠበለት የተነገራት መሆኑንም ለአሚና አውርታላታለች፡፡ አሚና እነዚህን ተዓምራት በሰማች ቁጥር ታዲያ ልቧ ከአካሏ የሚወጣ እስኪመስል ድረስ ይነጥራል፤ ወደ ልጃገረድነት የእድሜ ትዝታዎቿ በመንጎድም ገጥሟት
የነበረውን እንግዳ የሆነ ህልም ታስታውሳለች የዚያን ጊዜው ግራ
የሚያጋባ ህልም እውን እየሆነ መሆኑን በማጤን ታስባለች፡፡
ከአራት ረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ በህይወቷ ውስጥ አዲስ ስሜት ተፈጠረ፡፡ ዘወትር ትናፍቀው የነበረውን ልጇን በእቅፏ አስገባች፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ደስተኛ ሆነች። አሚና ለሙሐመድ ዘወትር ስለአባቱ ትተርክለት ነበር፡፡ እድሜው ስድስት ዓመት ሲሞላ አሚና ሙሐመድን ወደ የስሪብ ይዛው ሄደች፡፡ በዚያ የሚኖሩ ዘመዶቿን ጎበኘች ልጇም የአባቱን ቀብር እንዲያይ አደረገች፡፡ ነገር ግን ልጇን ይዛ ወደ መካ ስትመለስ ሌላ አዲስ ነገር ግን የሚያሳዝን የህይወት እውነት ተከሰተ። አሚና በሰላም ከወጣችበት መካ ሳትመለስ መንገድ ላይ ቀረች፡፡ በድንገት ህይወቷ አለፈ። ገና ይህንን ምድር ሳይቀላቀል አባቱን የተነጠቀው ሙሐመድ መቅመስ የጀመረውን የእናቱን ፍቅርና እንክብካቤ በወጉ ሳያጣጥም እናቱንም አጣ። በዚህም የተነሳ የሙሐመድ የህይወት መንገድ በድጋሚ መንገዱን ለመቀየር ተገደደ። ሙሐመድ በአያቱ አብዱል ሙጠሊብ ጥበቃ ስር መኖር ጀመረ።
የአሚና አብሮ አደግና የልብ ወዳጅ የነበረችው ኸዲጃም የተለየች
ውጣት ነበረች። ገና ሕፃን ሳለች ጀምሮ የነገሮችን እውነታ የመከታተልና የማወቅ ጉጉቷ ከእድሜዋ የላቀ ነበር ሁልጊዜ አባቷ ከሌሎች ነጋዴዎች ወይም ወንድሞቿ ጋር የስራ ጉዳዮችን በማንሳት በሚወያዩበት ወቅት በአትኩሮት በመከታተል በአዕምሮዋ ትይዝ ነበር። አንዳንዴ እንዲያውም በዚህ ዓይነቶቹ አጋጣሚዎች በምትከታተለው ውይይት ውስጥ ሳይገቧት የሚቀሩና ግር የሚሏት ጉዮች ሲገጥሟት የመጠየቅ ልምድም ነበራት፡፡
በዚህ የማወቅ ጉጉቷና ፍላጎቷ ሁሌም የሚደነቁት አባቷ ታዲያ
የምትጠይቃቸውን ነገር ሁሉ በአግባቡ ነበር የሚያብራሩላት፡፡
ኸዲጃ በተለያዩ የህይወት ጉዮች ዙሪያ በምትሰጠው ጠቃሚ
ምክሮችና አዳዲስ ሀሳቦች የወጣትነትና የመጀመሪያ ባሏ አቡ ሐላልንም ያስደንቀው ነበር፡፡ ኸዲጃ በወጣትነት እድሜዋ ከመሰረተችው ትዳሯ የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ሁለት ወንድ ልጆችን አፍርታለች። ያም ሆኖ ግን ባሏ አብሯት የቆየው ለተወሰኑ ዓመታት ብቻ ነበር። በህልፈተ ሞት ኸዲጃን ተሰናበታት፡፡
የመጀመሪያ ባሏን በሞት ያጣችው ኸዲጃ ያለባል የቆየችው እጅግ አጭር ለሆነ ጊዜ ብቻ ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሌላ ባል አገባች።
ሁለተኛው ባሏ አጢቅ እንደ እርሷ ሁሉ ሩህሩህ ልብ ያለው! ተመሳሳይ ፍላጎትን የሚጋራ ጥሩ ሰው ነበር፡፡ ኸዲጃም አዲሱ ባሏን በተለያዩ ጉዳዮች ማገዝን የዘወትር ተግባሯ አድርጋ ነበር አብራው የምትኖረው፡፡ ኸዲጃ ትዳር እንደመሰረተች በነበረው የመጀመሪያ ዓመት ላይ ሴት ልጅ ወልዳ እንኳ ባሏን በሥራ ከማገዝ የተቆጠበችበት ጊዜ አልነበረም፡፡ በሚኖራት ትርፍ ጊዜ ደግሞ ወደ ካዕባ በመሄድ ፀሎት ታደርግ ነበር። ኸዲጃና ቤተሰቡ በመተጋገዝ፣ በመተዛዘንና በደስታ ዓመታትን ካሳለፉ በኋላ ግን አንድ ፈተና ገጠማቸው። መካ ውስጥ ክፉ ወረርሽኝ ተከሰተ።
ብዙ ሰዎችም በወረርሽኙ ተይዘው ለበሽታ ተዳረጉ በወረርሽኙ ሳቢያ በርካቶች ሞቱ ያም ሆኖ በመድኃኒት እገዛ የተወሰኑ ሰዎች በሽታውን በማሸነፍ ህይወታቸውን ማትረፍ ተቻለ። የወረርሽኙን መከስት ተከትሎ ኸዲጃና ባሏ ሆስፒታል አቋቋሙ። በራሳቸው ወጪም ሐኪም ቀጥረውና የሚያስፈልጉ መድኃኒቶችን ገዝተው አያሌዎችን ከሞት ታደጉ፡፡ ባልና ሚስቱ በሆስፒታሉ የሚረዱ ታካሚዎችን በመንከባከብ ይሳተፉም ነበር። ጥቂት ቆይቶ ወረርሽኙ ከመካ ቢጠፋም የኸዲጃ የትዳር ጓደኛ አጢቅ ታመመ፡፡ እናም ሚስቱን ከሶስት ልጆች ጋር ጥሎ ሞተ። በዚህም የተነሳ ኸዲጃ በዋነኛነት በባሏ ይካሄድ የነበረውን የንግድ ሥራ ኃላፊነት መረከብ ግድ ሆነባት። ባሏ በህይወት በነበረበት ወቅት በሥራው እያገዘችው ስላሳለፈች ልጆቿ አድገው ኃላፊነቱን እስኪረከቡ ድረስ የንግድ ስራውን በራሷ አቅም መቀጠል አልከበዳትም ነበር፡፡ በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ ሴት ነጋዴን ማየት የተለመደ ስላልነበር በመጀመሪያ ላይ አንዳንድ አሉታዊ አስተያየቶች ይሰነዘሩ ነበር፡፡ ቆይቶ ግን የኸዲጃን ነጋዴ መሆን እየለመዱትና እየተቀበሉት መጡ፡፡ ኸዲጃ የሚገጥሟትን መሰናክሎች በአግባቡ በማለፍ የባሏን መዋዕለ ንዋይ ተጠቅማ የንግድ ሥራውን በአጥጋቢ መልኩ መምራት ቻለች። ሴት ከመሆኗ ጋር የሚገጥሟትን ፈተናዎችንም እየተጋፈጠች አሳለፈች፡፡ ኃብቷን በባለቤትነት ለመያዝ በመቋመጥ ለጋብቻ ይቀርቡ የነበሩ የግለሰቦች ጥያቄዎችንም በትዕግስትና በብልሃት አሸነፈች፡፡ ኸዲጃ ከነበረችበት ሁኔታ ጋር በተያያዘ ግን አንድ ልትወጣው ያልቻለችው ነገር ገጥሟት ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ሴቶች ለንግድ ሥራ ወደሌላ ሩቅ አገር መጓዝ አይችሉም ነበር፡፡ ኸዲጃ ለዚህ ሥራ ማድረግ የምትችለው ተወካይ መቅጠር ብቻ
ነበር። እናም ኸዲጃ ይህንን ስልት በመጠቀም ነበር የሩቅ አገር የንግድ ተግባሯን የምትፈፅመው። ሁል ጊዜ በየዓመቱ ወደሶሪያ በሚደረገው የነጋዴዎች ጉዞ ላይ እርሷን ሆኖ የንግድ ስራውን የሚያካሄድ ወጣት በመቅጠር ከነጋዴዎቹ ጋር አብሮ እንዲጓዝ ትልክ ነበር። ያም ሆኖ ግን ኸዲጃ በውክልና የምታካሄደው
የንግድ ተግባር ብዙውን ጊዜ አትረካም ነበር፡፡ ኸዲጃ እርካታውን ያጣችው ወጣት ወኪሎቿ ብልህነትና ብቃት ጎድሏቸው ስራውን በአግባቡ...
ይ
ቀ
ጥ
ላ
ል
👍34❤2