ኢትዮጵያ የሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አስተዳደርን በማጠናከር በኩል እያከናወነችው ያለው ተግባር አበረታች ነው
ኢትዮጵያ የሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አስተዳደርን በማጠናከር በኩል እያከናወነችው ያለው ተግባር አበረታች መሆኑን የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት(ILO) የኢትዮጵያና የምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኩምቡላ ንዳባ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ የተደራጀ እና ሕጋዊ የሥራ ስምሪትን ለማጠናከር ያለመ አዲስ ፕሮጀክት ዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው ድጋፍ ይፋ አድርጓል።
"በኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ሕጋዊና ሥርዓት ያለው የሠራተኞች ፍልሰት እንዲኖር ክልላዊ ትብብርን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ የሚተገበረው ይህ ፕሮጀክት፤ በዛሬው ዕለት ምክክር ተደርጎበታል።
የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት(ILO) የኢትዮጵያና የምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኩምቡላ ንዳባ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የሠራተኞችን መብት ለማስከበርና ሕጋዊ የጉዞ መንገዶችን ለማመቻቸት ያሳየችውን መሻሻል አድንቀዋል።
ለአራት ዓመታት የሚቆየው ይህ ፕሮጀክት ወቅታዊ፣ ተዓማኒና የተከፋፈለ የስደት መረጃን በማደራጀት የመንግስትን የውሳኔ አሰጣጥ አቅም ማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትን በማጠናከር ለዜጎች በውጭ ሀገር እውቅና የሚኖረው የክህሎት ማረጋገጫ መስጠትና ተወዳዳሪነታቸውን መጨመር እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የቅጥር ኤጀንሲዎችን አሠራር በመቆጣጠርና የሕግ ማዕቀፎችን ተግባራዊ በማድረግ በሠራተኞች ላይ ሊደርስ የሚችለውን በደል መከላከል የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
በሌላ በኩል ከፍልሰት ተመላሾች ትክክለኛ መረጃና የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ብርሃኑ አለቃ እንደገለጹት፤ መንግስት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።
ይህ ፕሮጀክትም ዜጎች በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለሚደርስባቸው እንግልት እንደ ትልቅ መፍትሔ እንደሚታይ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን(ኢሠማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ፕሮጀክቱ ሠራተኞች ወደ ውጭ ከመሄዳቸው በፊት፣ በቆይታቸው እና ሲመለሱ የተሻለ ድጋፍ ማግኘት የሚያስችላቸውን ተቋማዊ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡
ኢሠማኮ ለስኬታማነቱ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
የአውሮፓ ህብረት የፕሮግራም ኦፊሰር ሉቦሚራ ሚሬሶቫ፤ ህብረቱ ኢትዮጵያ የሠራተኛ ፍልሰት አስተዳደርን ለማጠናከር ላደረገችው ጥረት እውቅና እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ፕሮጀክቱ ሕጋዊ የፍልሰት መንገዶችን ተደራሽ በማድረግ ወጣቶች መደበኛ ላልሆኑ ጉዞ፣ ለሞትና ለብዝበዛ እንዳይጋለጡ ጥበቃ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ዘገባው የኢዜአ ነው።
ጥር 22/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtT
ኢትዮጵያ የሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አስተዳደርን በማጠናከር በኩል እያከናወነችው ያለው ተግባር አበረታች መሆኑን የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት(ILO) የኢትዮጵያና የምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኩምቡላ ንዳባ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ የተደራጀ እና ሕጋዊ የሥራ ስምሪትን ለማጠናከር ያለመ አዲስ ፕሮጀክት ዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት ከአውሮፓ ህብረት ባገኘው ድጋፍ ይፋ አድርጓል።
"በኢትዮጵያ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ሕጋዊና ሥርዓት ያለው የሠራተኞች ፍልሰት እንዲኖር ክልላዊ ትብብርን ማጠናከር" በሚል መሪ ሀሳብ የሚተገበረው ይህ ፕሮጀክት፤ በዛሬው ዕለት ምክክር ተደርጎበታል።
የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት(ILO) የኢትዮጵያና የምሥራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኩምቡላ ንዳባ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የሠራተኞችን መብት ለማስከበርና ሕጋዊ የጉዞ መንገዶችን ለማመቻቸት ያሳየችውን መሻሻል አድንቀዋል።
ለአራት ዓመታት የሚቆየው ይህ ፕሮጀክት ወቅታዊ፣ ተዓማኒና የተከፋፈለ የስደት መረጃን በማደራጀት የመንግስትን የውሳኔ አሰጣጥ አቅም ማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትን በማጠናከር ለዜጎች በውጭ ሀገር እውቅና የሚኖረው የክህሎት ማረጋገጫ መስጠትና ተወዳዳሪነታቸውን መጨመር እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የቅጥር ኤጀንሲዎችን አሠራር በመቆጣጠርና የሕግ ማዕቀፎችን ተግባራዊ በማድረግ በሠራተኞች ላይ ሊደርስ የሚችለውን በደል መከላከል የሚያስችል መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
በሌላ በኩል ከፍልሰት ተመላሾች ትክክለኛ መረጃና የማህበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ብርሃኑ አለቃ እንደገለጹት፤ መንግስት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።
ይህ ፕሮጀክትም ዜጎች በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለሚደርስባቸው እንግልት እንደ ትልቅ መፍትሔ እንደሚታይ ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን(ኢሠማኮ) ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ፕሮጀክቱ ሠራተኞች ወደ ውጭ ከመሄዳቸው በፊት፣ በቆይታቸው እና ሲመለሱ የተሻለ ድጋፍ ማግኘት የሚያስችላቸውን ተቋማዊ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡
ኢሠማኮ ለስኬታማነቱ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
የአውሮፓ ህብረት የፕሮግራም ኦፊሰር ሉቦሚራ ሚሬሶቫ፤ ህብረቱ ኢትዮጵያ የሠራተኛ ፍልሰት አስተዳደርን ለማጠናከር ላደረገችው ጥረት እውቅና እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ፕሮጀክቱ ሕጋዊ የፍልሰት መንገዶችን ተደራሽ በማድረግ ወጣቶች መደበኛ ላልሆኑ ጉዞ፣ ለሞትና ለብዝበዛ እንዳይጋለጡ ጥበቃ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ዘገባው የኢዜአ ነው።
ጥር 22/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtT
Facebook
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር - ኢትዮጵያ / Ministry of Labor and Skills- Ethiopia
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር - ኢትዮጵያ / Ministry of Labor and Skills- Ethiopia. 246,394 likes · 7,198 talking about this. This is the Official Facebook Page of the Ministry of Labor and Skills of Ethiopia....
🔊ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
🧰የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከE-LMIS ጋር በመተባበር ከዚህ በላይ በተገለፁት ክፍት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
🏫 ስለሆነም ይሆንን እድል መጠቀም የምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/federal_-civil_services_two/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎችን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
📆 አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከጥር 22 ጀምሮ ለተከታታይ 7ቀናት ማመልከት ይችላሉ።
☎️አስተያየት እና ጥቆማዎን በ9138 የሥልክ መስመር በመደወል እንዲያደርሱን እናሳስባለን።
🧰የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከE-LMIS ጋር በመተባበር ከዚህ በላይ በተገለፁት ክፍት የሥራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
🏫 ስለሆነም ይሆንን እድል መጠቀም የምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/federal_-civil_services_two/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎችን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
📆 አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ከጥር 22 ጀምሮ ለተከታታይ 7ቀናት ማመልከት ይችላሉ።
☎️አስተያየት እና ጥቆማዎን በ9138 የሥልክ መስመር በመደወል እንዲያደርሱን እናሳስባለን።
