Jimma University Official
44.4K subscribers
4.01K photos
28 videos
24 files
152 links
This channel is an official Telegram channel of Jimma University; the country's leading university which is known for its community based education philosophy.
We are in the Community!
Download Telegram
ተማሪዎችን ለመቀበል የኮቪድ-19 የጥንቃቄ ዉይይት
**********************
በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አገልግሎት ስር የሚገኙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች የኮሮና ቫይረስን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ፡፡

ዉይይቱ የ2013ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላን አስመልክቶ ሊደረጉ ስለሚገባቸዉ ጥንቃቄዎች ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ታዉቋል፡፡

የጥበቃና ደህንነት፣ የጠቅላላ አገልግሎት፣ የተማሪዎች መኝታ ተቆጣጣሪዎች፣ የተማሪዎች ካፍቴሪያ እና ሌሎች የሚመለከታቸዉ የስራ ክፍሎች፤ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ሲመጡ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ከግምት ዉስጥ ያስገባ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ለመፍጠር በተደረገዉ ዉይይት ላይ ተሳትፈዋል፡፡

በዉይይቱ ላይ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ እንደተናገሩት ተማሪዎችን መልሶ ለመቀበል እንደከዚህ በፊቱ ባለዉ ሂደት መቀጠል ባለመቻሉ የሚመለከተዉ የስራ ክፍል ሁሉ ከዚህ ቀደም ከነበረዉ ዝግጅት በተለየ ሁኔታ መዘጋጀት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

ምክትል ፕሬዚደንቱ በቀጣዩ የትምህርት ዘመን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ እራሳችንን እየተከላከልን ሰላማዊ እና ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ለመፍጠር ተባብረን እንስራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ጅማ ዩኒቨርቲ ተማሪዎችን መልሶ ለመቀበል ሰፊ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለሀገር ዕድገት
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለሀገር እድገት
***********************
የሃገር ሁለንተናዊ እድገትን ለማፋጠን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን መጠቀምና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተነገረ፡፡
ጅማ ዩኒቨርሲቲ እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል በትብብር መስራት የሚያስችላቸዉን የመግባቢያ ሰነድ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና ተፈራርመዋል፡፡

ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ በስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የዩኒቨርሲቲዉን አብይ የትኩረት አቅጣጫ የሆኑት መማር ማስተማር፣ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎትን ለማሳካት እጅጉን እንደሚያስፈልግ ገልፀዉ፤ ዩኒቨርሲቲዉ በሀገር ዉስጥ እና በዉጭ ከሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ሁሌም ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲዉ ባለሙያዎች ዲዛይን የተደረጉ ሶፍትዌሮች በሙሉ አገልግሎት እየሰጡ በመሆናቸዉ ዩኒቨርሲቲዉ ወረቀት አልባ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት ወደሚያስችለዉ ደረጃ በመሸጋገር ላይ እንደሚገኝና የሁለቱ ተቋማት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ አድጎ ለሀገር እድገት የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ለማድረግ ጅማ ዩኒቨርሲቲ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ ገልፀዋል፡፡

የአለማችን ሀገራት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ የጤና፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ፋይናንስ እና ሌሎች የስራ መስኮችን ማዘመንና ዉጤማ ማድረግ መቻላቸዉን በርካታ መዛግብት ያሳያሉ፡፡

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ዴቨሎፕመንት ም/ፕሬዚደንት አቶ ኮራ ጡሹኔ አለም በቴክኖሎጂ አማካኝነት በፍጥነት እየተለወጠ ስለሚገኝ ከዚህ ተለዋዋጭ ባህሪ ጋር ራስን አስማምቶ መጓዝ ተገቢ እንደሆነ ጠቅሰዉ፤ ‹‹መማር ማለት መከተል ማለት ሳይሆን መምራት ማለት ነዉ ስለዚህ በፍጥነት በመማርና የፈጠራ ስራዎቸችን በማስፋፋት የአለማችንን የቴክኖሎጂ ሰርዓተ-ምህዳር መቀላቀል ይኖርብናል ብለዋል»፡፡
አቶ ኮራ አክለዉም ለትብብር ስራዉ ግብዓት የሚሆኑ በርካታ ወጣት የፈጠራ ባለሙያዎች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስለሚገኙ ትብብሩ ዉጤታማ እንደሚሆን ያላቸዉን እምነት ተናግረዋል፡፡

በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ የተለያዩ የፈጠራ ባለሙያዎች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በመታገዝ የሰሯቸዉን የፈጠራ ስራዎችና ያስገኙትን ጥቅም ያቀረቡ ሲሆን ማዕከሉም እነዚህን ስራዎች ወደ ምርት እንዲገቡ በማድረጉ በኩል እገዛ እንደሚያደርግ ከስምምነት መደረሱ ታዉቋል፡፡

አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚያጋጥሙን ተግዳሮቶች ሁነኛ መፍትሄ እንደሆነ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና አስታዉሰዉ፤ ስራዉም የሰዉ ልጆች አገልግሎት አሰጣጥን ብቁና ተደራሽ በማድረግ የሚስተዋለዉን ተደራራቢ ጫና ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ኢንጂነሩ እንዳሉት የትብብር ስራዉ ዉጤት የሚለካዉ የመግባቢያ ሰነድ በመፈርም ሳይሆን ስራዉ ወደ መሬት ወርዶ ለህብረተሰቡ ብሎም ለሀገር እድገት በሚያበረክተዉ አስተዋጽዖ እንደሆነና ለዚህም ስኬት በትጋት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና የተመራ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ኤክስፐርቶችና ባለሙያዎች ቡድን ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በጅማ ዩኒቨርሲቲ አይ.ሲ.ቲ ፓርክ ጉብኝት አድረገዋል፡፡
JU finalized preparations to handle the suspended second semester courses in two months
JU finalized preparations to handle the suspended second semester courses in two months
***********************************
08 October 2020: Deans and Directors of JU’s Colleges and Institutes presented their report on the final preparation for the crash program (i.e., to finish the suspended semesters in two months) to the Jimma University Executive Management Members.
In their presentation, the Deans/Directors highlighted the procedures employed in preparing their plan and the major decision and action taken/planned to complete the second-semester courses in two months without compromising each course's core competence as per the curriculum. Likewise, unresolved issues and challenges were also enumerated for input and experience sharing by other attendees of the meeting.
Issues related to courses with practical training in each College, CBTP, TTP, Internship, and Student Research Project have been presented extensively in line with the guideline produced by a task force constituted earlier on the same issue. All Deans and Directors itemized different strategies in the areas of continuous assessment, class schedules, and course delivery modalities to accommodate the students having in mind the challenging situation of COVID-19. Also, each course's statues regarding learning materials uploaded on the MOSHE website and the University e-learning moodle were presented to the University management along with the level of student engagement with such materials and the challenges faced by students and instructors.
In his remark, the vice president for academic affairs, Dr. Adula Bekele, appreciated the colleges and Institutes’ efforts in preparing a very comprehensive report but cautioned that consistency must be applied across colleges and faculties in their proposed strategies. He stressed that communication is essential to bring both the instructors and students on board to finish the semesters as per the schedule with all offices ready to support the students both academically and psychologically. He added that the taskforce establish to provide psychosocial support is working hard and they will also share their plan in near future.

In his final remark, JU's President Dr. Jemal Abafita noted that we must be ready to finish the semester courses without compromising each course's core competency as laid out in the curriculum. He argued that all offices' involvement and cooperation is paramount to achieving reasonable success. He further noted that the preparations presented by all deans and directors on the academic front will be aligned with all other ongoing physical preparation in the campus as per the COVID-19 guideline and protocol issued by MOSHE.

The President concluded by thanking participants and office of Vice President for Academic Affairs for the preparation done so far and coordination of the day’s presentation. The president also promised to engage with all Jimma University academic staff in the coming days as part of the preparation to get everyone on board.
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለወገን የሚያደርገዉን ድጋፍ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
********************
ዛሬም በጅማ ከተማ የተባበሩት አካባቢ በቀድሞ አጠራሩ ኢዲዲሲ ዉስጥ ለሚኖሩ ከ 450 በላይ አባወራዎች ፍራሾች፣ ምግብና ምግብ ነክ እንዲሁም የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሁኔታ እና አጋጣሚዎች ለህብረተሰቡ የተለያዩ ድጋፎችን ያደረገ ሲሆን በዛሬዉ እለትም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክስ እና አስተዳደር ሰራተኞች ድጋፍ ግምታቸዉ ከ 500 ሺህ ብር በላይ የሆኑ ፍራሽ፣ የምግብ እህልና ግብዓቶች፣ የንፅህና መጠበቂያን ለተጠቀሱት ተረጂዎች አስረክቧል፡፡

በድጋፍ አሰጣጡ ፕሮግራም ላይ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ፣ አስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ፣ የጅማ ከተማ ም/ከንቲባ አቶ ካሳሁን ጆብር እና የከተማዉ ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ጉዳዮች ሀላፊ አቶ ለታ አሸብር ተገኝተዋል፡፡
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ይህ ድጋፍ ግዜያዊ ችግርን ለመቅረፍ እንጂ ዘላቂ መፍትሄ እንደማይሆን ተናግረዉ፤ መንግስት እነዚህን ወገኖች በዘላቂነት ማቋቋም እንዳለበት በመጠቆም ለዚህም ተግባራዊነት ዩኒቨርሲቲዉ የበኩሉን ድርሻ እንደሚያበረክት ገልጸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዉ ወደፊትም በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎቶቹ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት እንደሚያደርግና በተመሳሳይ ችግር ዉስጥ ያሉ ወገኖችን ለመርዳት ዘላቂ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ዶ/ር ጀማል አባፊጣ አክለዉ ገልፀዋል፡፡
የምግብና ምግብ ነክ እንዲሁም ፍራሾችና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ተረጂዎቹ በተወካዮቻቸዉ አማካኝነት ተረክበዋል፡፡