Intrance result.neaea.gov.et
2.82K subscribers
582 photos
31 videos
302 files
632 links
መረጃዎች ምንጫቸውን ሳንጠቅስ አናጋራም!

ወቅታዊ ፈጣንና ታማኝነት ያላቸውን ት/ተዊ ቴክኖሎጂ፤ ፋሽንን ጨምሮ የመዝናኛ መረጃዎችን በአንድ ቦታ ለማግኘት፤ ዛሬውኑ በመቀላቀል ራሶን ከዘመኑ ጋር ያዘምኑ፤ የአዋቂ ማህበረሰብ አካል ይሁኑ።

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
@intrancresult
ሀሳብ @TheRsultBot
Download Telegram
ከ18 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና ይሰጣል።

በፀጥታና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ላልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በጎንደር፣ በጋምቤላ፣ በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች 17,753 ተማሪዎች እንዲሁም 300 በውጭ ሀገራት ለሚገኙ ተማሪዎች ፈተናው እንደሚሰጥ የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሦስት መፈተኛ ጣቢያዎች ሲፈተኑ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ከ16 ሺህ በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሁለት እስከ ሦስት የትምህርት ዓይነቶች ሳይፈተኑ መቅረታቸውን አስታውሰዋል።

በጋምቤላ ደግሞ ከ100 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ አልወሰዱም ብለዋል።

በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 982 ተማሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ከ18 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናው ይሰጣል ብለዋል።

በውጭ ሀገራት በኢትዮጵያ ስርዓተ ትምህርት የሚማሩ 300 ተማሪዎች ከዛሬ ነሐሴ 28/2015 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 02/2015 ዓ.ም ፈተናው ይሰጣል።

ለዚህም የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ከኢትዮጵያ ፈተናው ወደሚሰጥባቸው ሀገራት መጓዛቸውን ም/ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። #ENA

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-➳➳➳ ሼር ያድርጉ!! ➢➢➢
#Share  #join 🙏🙏🙏🙏🙏
Share & Support Us
👇👇👇👇👇👇👇👍
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
በፀጥታ ችግር ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከመስከረም 8 ቀን ጀምሮ ይፈተናሉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በፀጥታ ችግርና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመፈተን መዘጋጀቱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር መሰጠቱን አገልግሎቱ አስታውሷል፡፡

ይሁንና በጎንደርና በጋምቤላ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ እና በከፊል 14 ሺህ 891 ተማሪዎች እንዲሁም በሕህ ግ ጥላ ስር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 419 ተፈታኛ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸው ተጠቅሷል፡፡

እነዚህን ተፈታኞች ከመጪው መስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ውጤታቸውም ከመጀመሪያው ዙር ጋር እንደሚገለጽም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-➳➳➳ ሼር ያድርጉ!! ➢➢➢
#Share  #join 🙏🙏🙏🙏🙏
Share & Support Us
👇👇👇👇👇👇👇👍
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ተማሪዎች ተጠቀሙበት 👌 👌 👌 👌
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️👆👆

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-➳➳➳ ሼር ያድርጉ!! ➢➢➢
#Share  #join 🙏🙏🙏🙏🙏
Share & Support Us
👇👇👇👇👇👇👇👍
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ውጤት መቼ ይገለጻል?

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ውጤትን ቶሎ ለማድረስ በሙሉ አቅም እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡

ፈተናውን የማረም ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ማንጠግቦሽ አዳምጤ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

ከመስከረም 07 እስከ 11/2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን ጨምሮ ውጤት ለመግለፅ መታሰቡን ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡

"ምናልባትም እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል" ተናግረዋል፡፡

በነሐሴ መጨረሻ በሰጡት መግለጫ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር) የ12ኛ ክፍል ውጤት እስከ መስከረም አጋማሽ ድረስ ይፋ ይደረጋል ብለው እንደነበር አይዘነጋም።

በትግራይ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ለነበሩ ተማሪዎች ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 02/2016 ዓ.ም የመልቀቂያ ፈተናው ይሰጣል መባሉ ይታወቃል።

➢➢➢
#Share  #join 🙏🙏🙏🙏🙏
Share & Support Us
👇👇👇👇👇👇👇👍
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
#Update

በፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ፈተናቸውን ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናቸውን ያላጠናቀቁ 11,581 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ዛሬ ማስፈተን መጀመሩን ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አሳውል።

ተማሪዎቹ ጠዋት የኬሚስትሪ ትምህርት ፈተና የወሰዱ ሲሆን ከሰዓት ደግሞ የባዮሎጂ ትምህርት ፈተና እየወሰዱ እንደሚገኙ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ም/ፕሬዝዳንት ካሳሁን ተገኘ (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

➢➢➢
#Share  #join 🙏🙏🙏🙏🙏
Share & Support Us
👇👇👇👇👇👇👇👍
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🎉🎉🎉 #share #share
ይሄ channel ከ ቀን ወደ ቀን member እየዳጋ 1k ደርሰናል🎉🎉🎉 ::እንኳን ደስ አላችሁ 🌹🌹🌹🌹 እርስዎም ቢያንስ ለ 10 ሰው share  ያድርጉልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን:: እኛም ደከመን ሰለቸን ሳንል እርሶን ለማገልገል ዝግጁ ነን በቀጣይም ብዙ ነገሮችን ለማሻሻል ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረግን እንገኛለን::ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን🙏🙏
Share #share 🙏

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ይቀላቀሉ ፤
https://t.me/intrancresult
https://t.me/intrancresult
🔰ትንሽ ጠብቁን🙏

"School Code " System ማስገባት አስቸጋሪ ስለነበር ለመቀነር ስባል ነው የዘገየው ።

Registration number እና የመጀመሪያ ስም ብቻ ተጠቀሙ።

1. eaes.edu.et 👉(Reg.no & First name )
2. eaes.et 👉 (Reg.no & First name )
3. eaes.gov.et 👉 (Reg.no & First Name )

SMS :6284

Bot :@EAESbot

በተባለው ሰዓት ባለመለቀቁ ይቅርታ እንጠይቃለን።

ለተማሪዎች ሼር አድርጉ🙏
#Share #share 🙏

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ይቀላቀሉ
https://t.me/intrancresult
https://t.me/education_stor
በ12ኛ ክፍል ውጤት “ራቁታችንን ምን እንደምንመስል አይተነዋል” - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ የመስሪያ ቤታቸውን የዘንድሮ እቅድ እና የበጀት ዓመቱን የሩብ ዓመት አፈጻጸም ለማቅረብ ዛሬ ረቡዕ በፓርላማ ተገኝተው ነበር። የዛሬውን ስብሰባ በጠራው የተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሚኒስትሩ ካቀረባቸው ጥያቄዎች መካከል የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን የሚመለከተው ይገኝበታል።

የቋሚ ኮሚቴውን ጥያቄዎች በንባብ ያሰሙት የፓርላማ አባል “በተከታታይ ለሁለት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት በጣም ዝቅተኛ የሆነበት ምክንያት ምንድነው? ትምህርት ሚኒስቴር የፈተናውን ውጤት እንዴት ያየዋል?” ሲሉ ጠይቀዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “የ12ኛ ክፍል ውጤት እንደዚህ መሆን፤ ምንምን እንኳ really መጠበቅ የነበረን ነገር ቢሆንም ሁላችንንም አስገርሞናል” ብለዋል።

“የፈተናውን አሰጣጥ መቀየር ብቻ ይሄን ካሳየ፤ ከዚህ ተነስተን ብቸኛ ነገር ልንል የምንችለው፤ ከዚያ በፊት ስንሰጣቸው የነበሩ ፈተናዎች በሙሉ የተማሪን እውነተኛ ችሎታ የሚያሳዩ አይደሉም ማለት ነው” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ይሰጡ በነበሩ ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በትምህርት ቤቶች እና በክልል ደረጃ ሳይቀር በተደራጀ መልኩ “ፈተናዎች የሚሰረቁበት” እንደነበር የጠቀሱት ፕ/ር ብርሃኑ፤ በዚያን ጊዜ የነበሩ ውጤቶች የተማሪዎችን ችሎታ የሚያንጸባርቁ እንዳልነበር አስረድተዋል።

“አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ refelect አድርጎልናል። አሁን የምንደበቅበት ቦታ የለም። ሰርቀን የምናሳይበት ቦታ የለም። ራቁታችንን ምን እንደምንመስል አይተነዋል” ሲሉም የትምህርት ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ለተማሪዎች ሼር አድርጉ🙏
#Share #share 🙏

shere Shere 👇🙏🙏🙏
https://t.me/intrancresult
https://t.me/education_stor