4th round cyber talent summer camp participants የነገው ቀን "ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" at science museum
🔥22❤5👍1
Congratulations 🎉
"ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ቃል የነገዉ ቀን በሳይንስ ሙዚየም እየተከበረ ይገኛል። ዕለቱን በማስመልከት በተዘጋጀዉ የሃካቶን ውድድር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር/ INSA/ የሳይበር ታለንት ማዕከል ታዳጊዎች አሸናፊ ሆነዋል።
ጳጉሜን-5
#የነገውቀን
ዲጂታል_ኢትዮጵያን_እውን_ማድረግ
#ዲጂታል_ኢትዮጵያ
"ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ቃል የነገዉ ቀን በሳይንስ ሙዚየም እየተከበረ ይገኛል። ዕለቱን በማስመልከት በተዘጋጀዉ የሃካቶን ውድድር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር/ INSA/ የሳይበር ታለንት ማዕከል ታዳጊዎች አሸናፊ ሆነዋል።
ጳጉሜን-5
#የነገውቀን
ዲጂታል_ኢትዮጵያን_እውን_ማድረግ
#ዲጂታል_ኢትዮጵያ
🔥44❤15👍12
በ2017 የኢንሳ ሰመር ካምፕ ተሳታፊ ከነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች መካከል 24ቱ 500 እና በላይ አስመዝግበዋል ከእነዚህ ዉስጥ 9ኙ ሴቶች ናቸዉ! እንኳን ደስ አላችሁ! @insactc
👏158🔥21❤16👍14🤷♂11👀6😁3🆒3
Forwarded from Tikvah-University
#TVTI
በBRICS የክህሎት ውድድር የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን የሜዳልያ አሸናፊዎች ሆነዋል።
የክህሎት ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዙር ተወዳዳሪ የነበረው ዘላለም እንዳለ በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ለውድድሩ ይዞ በመቅረብ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ሆኗል።
አቤኔዘር ተከስተ በእጅ የሚሰራ Plastic Injection Molding Machine ፕሮጀክት ይዞ በመቅረብ የብር ሜዳልያ አሸንፏል።
በAI የታገዘ የነርስ ጥሪ ማድረጊያ ሲስተም ይዛ የቀረበችው ነቢሃ ነስሩ የነሃስ ሜዳልያ አሸንፋለች።
በ BRICS Skill Competition 2025 ከአባል አገራቱ የተውጣጡ 300 ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል።
@tikvahuniversity
በBRICS የክህሎት ውድድር የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን የሜዳልያ አሸናፊዎች ሆነዋል።
የክህሎት ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዙር ተወዳዳሪ የነበረው ዘላለም እንዳለ በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ለውድድሩ ይዞ በመቅረብ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ሆኗል።
አቤኔዘር ተከስተ በእጅ የሚሰራ Plastic Injection Molding Machine ፕሮጀክት ይዞ በመቅረብ የብር ሜዳልያ አሸንፏል።
በAI የታገዘ የነርስ ጥሪ ማድረጊያ ሲስተም ይዛ የቀረበችው ነቢሃ ነስሩ የነሃስ ሜዳልያ አሸንፋለች።
በ BRICS Skill Competition 2025 ከአባል አገራቱ የተውጣጡ 300 ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል።
@tikvahuniversity
👏33❤17🎉4
የCTF ውድድር ጥሪ!
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ)
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወርን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የCapture The Flag (CTF) ውድድር!!
የሳይበር ደህንነት ክህሎትዎን የሚፈትሹበት እና ከሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ጋር የሚወዳደሩበት መድረክ !!
ይወዳደሩ! ይሸለሙ!
ለመመዝገብ፡- ከታች ያለውን QR ኮድ ስካን ያድርጉ
ቦታ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በአካል
ቀን ጥቅምት 1/2018ዓ.ም
ከ ጠዋቱ 2፡ 30 በአካል
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ)
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወርን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የCapture The Flag (CTF) ውድድር!!
የሳይበር ደህንነት ክህሎትዎን የሚፈትሹበት እና ከሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ጋር የሚወዳደሩበት መድረክ !!
ይወዳደሩ! ይሸለሙ!
ለመመዝገብ፡- ከታች ያለውን QR ኮድ ስካን ያድርጉ
ቦታ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) በአካል
ቀን ጥቅምት 1/2018ዓ.ም
ከ ጠዋቱ 2፡ 30 በአካል
🫡16❤12💩9🥰3🔥1😢1🤪1
Forwarded from INSA - የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር - INSA
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል ይከበራል
አዲስ አበባ፡ መስከረም 29/2018 ዓ.ም፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ከጥቅምት 1-30/2018 ዓ.ም ድረስ የሚከበረውን 6ኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡
ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡
በሀገራችን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከማደጉ ጋር ተያይዞ በዜጎች፣ በተቋማት እና ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቁመው፣ የሳይበር ደህንነት ወር የተቋማትን እና የኅብረተሰቡን የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና በማጎልበት ለሳይበር ደህንነት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡና እራሳቸውን ከሳይበር ጥቃት መከላከል እንዲችሉ የሚያግዙ የተለያዩ መርሐግብሮች የሚካሄዱበት ወር እንደሆነ ገልጸዋል።
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች እንደሚከበር የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፤ የመጀመሪያው የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅትና ስርጭት መከላከል ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ዲጂታላይዜሽን እና የሳይበር ደህንነት ጋር የሚያተኩር ነው፡፡
ተጨማሪውን ለማንበብ፡- https://www.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
አዲስ አበባ፡ መስከረም 29/2018 ዓ.ም፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ከጥቅምት 1-30/2018 ዓ.ም ድረስ የሚከበረውን 6ኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፡፡
ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው 6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡
በሀገራችን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከማደጉ ጋር ተያይዞ በዜጎች፣ በተቋማት እና ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቁመው፣ የሳይበር ደህንነት ወር የተቋማትን እና የኅብረተሰቡን የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና በማጎልበት ለሳይበር ደህንነት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡና እራሳቸውን ከሳይበር ጥቃት መከላከል እንዲችሉ የሚያግዙ የተለያዩ መርሐግብሮች የሚካሄዱበት ወር እንደሆነ ገልጸዋል።
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች እንደሚከበር የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፤ የመጀመሪያው የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅትና ስርጭት መከላከል ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ዲጂታላይዜሽን እና የሳይበር ደህንነት ጋር የሚያተኩር ነው፡፡
ተጨማሪውን ለማንበብ፡- https://www.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
❤24💩6🔥2
