💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
9.67K subscribers
1.29K photos
494 videos
124 files
5.16K links
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሎት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለቜ፣ #ሎት ልጅና #ሀያዕ አብሚው ዚሚኖሩ መቌም ዚማይነጣጠሉ ጥምሮቜ ና቞ው።

👉 ሎት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሞብርቃ ነው።

💎ይህንን ዘውድ ኚራሷ ዚገፈፈቜ ሎት ግን ህያው ኹሆኑ ሰዎቜ መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለቜ።
Download Telegram
04 الوسا؊ل المفيدة للحياة السعيدة
  Abu Sufiyan Albenan
―ክፍል (④)
📚الوسا؊ل المفيدة للحياة السعيدة
«ደስተኛ ሕይዎት ለመኖር ዚሚያግዙ ነጥቊቜ!»
ዚኪታቡ pdfለማገኘት👇
t.me/https_Asselfya/8029
✅ ኢማሙ ኢብኑል ቀይም ሹሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ፡-

በተወኩል ላይ ተሚኚዞቹን ያፀና እራሱንም ወደ አላህ ያስጠጋ እንዲሁም እራሱንታዛዥ ያደሚገ ሰው እርካታን ማግኘቱ ቅሮት ዚለውም።❞

        
    📚مدارج السالكين Ù¢ / Ù¡Ù§Ù£"]
t.me/https_Asselfya
~ አግባ! ብዙዎቜ አግብተው ሀብታሞቜ ሆነዋልፀ
ድህነትን #ፈርተህ አንተ ግን ፈዝዘሃል።

=
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
⭕👉ተኚታታይ ስለ ሚመዷን አህካም ዳሰሳ                ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 【ክፍል ሁለት 0⃣2⃣】 〰〰〰〰〰〰 ◟ካፊር እና ፃም 〰〰〰〰〰〰 ↪ 【ነጥብ አንድ】👉 ካፊር ቢፃም ፃሙ ተቀባይነት ያገኛልን⁉ 〰〰〰〰 ◟ካፊር ዹሆነ ሰው በኩፍሩ እስካለ ድሚስ ሚመዷንን መጟም ግዎታ አይሆንበትም። ቢፃም ራሱ ሚሀብና ጥማት ኚማትሚፍ ውጪ ተቀባይነት አይኖሚውም። ነገር ግን ይህ ማለት ነገ አላህ ፊት አይጠዚቅበትም 
⭕👉ተኚታታይ ስለ ሚመዷን አህካም ዳሰሳ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
#ህፃን (ለአቅመ አዳም) ያልደሚሰ ልጅና ፃም

↪ ክፍል ሶስት《0⃣3⃣》

✅ ህጻን ልጅ ብሉግ (አቅመ አዳም) እስኪደርስ ድሚስ ፃም ግደታ አይሆንበትም። ምክንያቱም ዹአላህ መልእክተኛ ï·º እንዲህ ብለዋልና።
رُفِع القلم عن ثلاَثَةٍ عَنِ النَّاءِم حتَّ يَستيْقِ؞ وعنٍِ الصغيرِ يكُؚرَ وعنِ المجنُونِ حتَّ يُفِيق
⭕👉 ኚሶስት ሰዎቜ ላይ ቀለም ተነስቷል።
🔹ዚተኛ ሰው እስኪነቃ ድሚስ
🔹ህጻን ልጅ ብሉግ (አቅመ አዳም) እስኪደርስ
🔹እብድ እስኪነቃ ድሚስ

📚ኢማሙ አህመድ፣ አቡ ዳውድ፣ ነሳኢይና ዘግበውታል።

⭕👉 ስለዚህ በዚህ ሀዲስ መሰሚት አቅመ አዳም ያልደሚሰ ልጅ ቀለም ስለተነሳለት ለምን አልፃምክም ተብሎ ስለማይጠዚቅ ፃም በሱ ላይ ግዎታ አይሆንበትም ማለት ነው።

✅ ነገር ግን ህፃኑ ቢፃም ዚሚቜልና ጉዳት ዚማያመጣበት ኹሆነ አስተዳዳሪዎቹ
እንዲጟም ያዙታል። ይህ በማድሚጋ቞ው ልጁ ነገ ትልቅ ሲሆን እንዳይኚብደውና እንዳይ቞ገር ይሚዳዋል።

✅ ሶሀቊቜ ዹአላህ ሱብሀነሁተአላ ውዳሎ በነርሱ ላይ ይሁንና  ልጆቻ቞ውን ትንሜ ሁነው ሳለ እንዲጟሙ  ያደርጉዋ቞ው ነበር። በዚህ መልኩ ኹፃሙ በኋላ ወደ መስጅድ ይዘዋቾው ይሄዱና ምግብ ትዝ ብሏ቞ው ማልቀስ ሲጀምሩ መጫወቻ ነገር በመስጠትና በማጫወት ምግብ እንዲሚሱና እንዲዘናጉ ያደርጉዋ቞ው ነበር።

👉ስለዚህ በዚህ መሰሚት ህፃናቶቜ እንዲፃሙ ማድሚግና በዚህ ላይ ማለማመድ ዚሰለፎቜን መንገድ ኹመኹተል ውስጥ አንዱ ነው።

🚫ስህተት 🚫
〰〰〰〰〰
◟ብዙ ወላጆቜ ልጆቻ቞ውን ዲንን አያስተምሩም። ዹወላጅ ትልቁ ሀላፊነት ማብላት፣ ማጠጣትና ማልበስ ብቻ ይመስላ቞ዋል። ይህ ሊቀሹፍ ዚሚገባ ትልቅ ስህተት ነው። ልጆቜ ኚምግብ ኚመጠጥ ኹሌላም ነገር በላይ ዲን ያስፈልጋ቞ዋል። በዘመናቜን ብዙ ሙስሊም ወጣቶቜ አጫሜ፣ ቃሚ፣ ጠጪ፣ ዱርዬ እዚሆኑ ያሉት ኚቀተሰብ ክትትልና ዲንን ካለማስተማር ዚተነሳ ነው። ብዙ ወጣቶቜ ጎልማሳነት እድሜ ላይ ሆነው አርካኑል ኢስላም አያውቁም፣ እስልምና ዚሚያበላሞውን አይለዩም። ዚነብያቶቜና ዚሶሀባዎቜ ምንነትም ሆነ ስም አያውቁም። በተቃራኒው ዚካፊር ፊልም አክተርና ኳስ ተጫዋቜ አድናቂ በመሆን ዚመልእክተኛውን ሱና ትተው በፈሚንጆቜ ፋሜንና ዲዛይን ተሞውዶ ይታያሉ። በአብዘሀኛው ዹዚህ ሁሉ መንስኀ ገና በልጅነታ቞ው ዲን ያለማሰሚተመሰራቜን ውጀት ነው።

◟አንዳንድ ልጆቜ ለዲና቞ው ካላ቞ው ፍቅርና ለኢባዳ ካላ቞ው ውዎታ ዚተነሳ መፃም ይፈልጋሉ። ነገር ግን አንዳንድ ወላጆቜ በግድ እንዲያፈጥሩ ሲያደርጓ቞ው ይታያል። ይህም ሌላኛው ሊቀሹፍ ዚሚገባው ጥፋት ነው። በመፃማቾው ግልፅ ዹሆነ ጉዳት ዚማይደርስባ቞ው ኹሆነና አቅሙ እስካላ቞ው ድሚስ ቢፃሙና ቢለማመዱ ዚተሻለ ነው። ምናልባትም አንዳንድ ወላጆቜ ይህን በማድሚጋ቞ው ለልጆቻ቞ው ያዘኑ መስሏ቞ው ሊሆን ይቜላል። ሀቂቃው ግን ይህ ድርጊት ለነሱ ማዘን ሳይሆን እነሱን መበደል ነው። እውነተኛ ዹልጅ እዝነት ማለትፊ
🔹ቁርአን ማቅራት
🔹ሀዲስን ማስተማር
🔹ሞሪአን ማሳወቅ
🔹በኢስላማዊ ተርብያ ማሳደግና
🔹ኢባዳን ማለማመድ
ነው።

◟ክፍል አራት ይቀጥላል ኢንሻአላህ
               ፧              ፧
               ፧              ፧
     t.me/https_Asselfya
     t.me/https_Asselfya
Audio
"ُؚ؎ْرَاكُم اليَومَ جنَّاتٌ"
ደህና እደሩልኝ!
05 الوسا؊ل المفيدة للحياة السعيدة
  Abu Sufiyan Albenan
―ክፍል (â‘€)
📚الوسا؊ل المفيدة للحياة السعيدة
«ደስተኛ ሕይዎት ለመኖር ዚሚያግዙ ነጥቊቜ!»
ዚኪታቡ pdfለማገኘት👇
t.me/https_Asselfya/8029
~ዹበደለንን ይቅር ማለት
መሾነፍ ሳይሆን ፍቅርን
ማስተማር፣ቀናነትን መዝራት፣
ህይወትን ማደስ ነው።

~
~በሜታ ኹሠው ወደሰው እንደሚጋባ ሁሉ
ጀንነትም ኹሠው ወደ ሠው ይጋባል።
ጀናማ አስተሳሰብ
ካላ቞ው ሠዎቜ ጋር መዋል
ጀናማ ያደርጋል።

~
t.me/https_Asselfya
አብዝቶ ዚሚታገስ
በዉሳኔዉ አይፀፀትም።

~
~ለምን ዹለይል ሶላት ሲቆም አያድርም ። ምቀኝነት ያለበት ሰው ሰላም ዹለዉም ።

~
t.me/https_Asselfya
~ወንድ ልጅ ቀት ሊሠራ ይቜላል።
ምቹ መኖሪያ ዚምታደርገዉ ግን ሎት ልጅ ናት።

~
t.me/https_Asselfya
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
⭕👉ተኚታታይ ስለ ሚመዷን አህካም ዳሰሳ 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 #ህፃን (ለአቅመ አዳም) ያልደሚሰ ልጅና ፃም ↪ ክፍል ሶስት《0⃣3⃣》 ✅ ህጻን ልጅ ብሉግ (አቅመ አዳም) እስኪደርስ ድሚስ ፃም ግደታ አይሆንበትም። ምክንያቱም ዹአላህ መልእክተኛ ï·º እንዲህ ብለዋልና። رُفِع القلم عن ثلاَثَةٍ عَنِ النَّاءِم حتَّ يَستيْقِ؞ وعنٍِ الصغيرِ يكُؚرَ وعنِ المجنُونِ 
⭕👉ተኚታታይ ስለ ሚመዷን አህካም ዳሰሳ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
#አቅመ አዳም (ؚلوغ) ዚመድሚሻ ምልክቶቜ

↪{ ክፍል አራት《0⃣4⃣》

📍በወንድም ሆነ በሎት ላይ ማንኛውም ዚሞሪአ ድንጋጌ ግዎታ (ዋጂብ) ዹሚሆነው አቅመ አዳም ወይም ብሉግነት ደሹጃ ላይ ኚደሚሱ በኋላ ነው። ብዙ ሰዎቜ ለአቅመ አዳምነት ደርሰው ነገር ግን ምልክቶቹ በደምብ ካለማወቃ቞ው ዚተነሳ ገና ህፃን ነኝ በሚል እሳቊት ሶላት ፃምና ሌሎቜም ግዎታ ዹሆኑ ኢባደዎቜ ላይ ሲዘናጉ ይታያሉ። በአላህ ፍቃድ እነዚህን ምልክቶቜ በቅደም ተኹተል ዹምንቃኝ ይሆናል።

💠 ወንድ ልጅ አቅመ አዳም (ብሉግ) መድሚሱ ዚምናውቅባ቞ው መንገዶቜ

◌አንድኛፊ መንይ (ዹዘር ፈሳሜ)

~አንድ ሰው ተኝቶም ይሁን ሳይተኛ በዚትኛውም መልኩ መንይ (ዹዘር ፈሳሜ) ኚወጣው ኹዛን ሰአት ጀምሮ ዚሞሪዓ ድንጋጌዎቜ በሱ ላይ ግዎታ ይሆንበታል። ምክንያቱም ይህ ሰው አቅመ አዳም መድሚሱ ኚሚያሳዩ ምልክቶቜ ውስጥ አንዱ ዹሆነው ዹዘር ፈሳሜ ተገኝቶበታልና።

⭕👉 ለዚህም መሹጃው ዹአሏህ ሱብሀነሁተአላ ንግግር ነው።
📌وَإِذَا َؚلَغَ ٱلْأَطْفَٰلُ مِنكُمُ ٱلْحُلُمَ فَلْيَسْتَـْٔذِنُوا۟ كَمَا ٱسْتَـْٔذَنَ ٱلَّذِينَ مِن قَؚْلِهِمْ
ኚእናንተም ሕፃናቶቹ ኢህቲላም (ዹዘር ፈሳሜ ሚያዩበት) ጊዜ ኚደሚሱ እነዚያ ኚእነሱ በፊት ዚነበሩት (ታላላቆቹ) እንዳስፈቀዱ ያስፈቅዱ፡፡
📚 ሱሚቱ አኑር (59)

🔹በሀዲስ ዹአላህ መልእክተኛ ï·º እንዲህ ብለዋል
غُسلُ الجُمُعَةِ واجٌؚ على كُلِّ مُحتلمٍ
ኢህቲላም (ዹዘር ፈሳሜ) ዚማዚት ደሹጃ ላይ በደሚሱ ሁሉ ዹጁሙዓ ትጥበት ግዎታ ነው።

📚ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

◟ሁለተኛፊ "ብልት አካባቢ ፀጉር ማብቀሉ"

~ይህ ፀጉር ኚርዳድ ያለ ልስላሎ ዹሌለው ብልት አካባቢ ዹሚበቅል ሲሆን ይህም አንዱ ቡሉግነት ዚመድሚሻ ምልክት ተደርጎ ይቆጠራል።

⭕👉 ለዚህ መሹጃው አጢያ አልቁሹዝይ ፡፡ዚተባለው ሰሀብይ ዹተናገሹው ንግግር ነው። እሱም እንዲህ አለ፩ "ዹቁሹይዛ ዘመቻ ግዜ በመልእክተኛው ላይ ቀሚብን ዹዘር ፈሳሜ ማዚት ደሹጃ ላይ ዹደሹሰ ወይም ብልቱ አካባቢ ፀጉር ያበቀለ ሰው ይገደል ነበር ብልቱ አካባቢ ፀጉር ያላበቀለ ሰው ይተው ነበር።
📕ኢማሙ አሕመድና ነሳዒይ ዚዘገቡት ሶሂህ ሀዲስ ነው።

⭕👉በኑ ቁሚይዛዎቜ ኚዚሁድ ጎሳ ዹሆኑ አደገኛ ዚኢስላም ጠላቶቜ ነበሩ። በዚህ በበኑ ቁሹይዛ ዘመቻ ጊዜ ዚተማሚኩት እንዲገደሉ ተወስኖ ስለነበሚ ለአቅመ አዳምነት ያልደሚሱት ግን ይተው አይገደሉም ነበር። ለአቅመአዳምነት ለመድሚስ በብልቱ ላይ ፀጉር ማብቀሉ ያለማብቀሉ ታይቶ ካበቀለ ትልቅ ስለሆነ ይገደላል። ካላበቀለ ደሞ ህፃን ነውና ይተው ነበር።

◟ሶስተኛፊ አስራ አምስት {15} አመት መሙላት

ኹላይ ኚተጠቀሱት ምልክቶቜ ውስጥ አንዱ ካልታዚ አስራ አምስት አመት እስኪሞላው ዹሚጠበቅ ይሆናል። ይህ እድሜ ላይ ሲደርስ ግን ቡሉግነቱ ስለሚሚጋገጥ በሞሪአ ዋጂብ ዹተደሹጉ ኢባዳዎቜን ዚመስራት ግዎታ ይኖርባ቞ዋል።

▪ ለዚህም መሹጃው፩
⭕👉አብደላህ ኢብኑ ኡመር እንድ አለ:- ዚእሁድ ዘመቻ ጊዜ በዘመቻው ላይ እንድሳተፍ መልእክተኛው ሰለሏሁአለይሂ ወሰለም ዘንድ ቀሚብኩኝ። ዹዛኔ እድሜዬ 14 ነበር። ነገር ግን ለጅሀድ መልእክተኛው አልፈቀዱልኝም። በቀጣዩ አመት ላይ ዹኾንደቅ ዘመቻ ግዜ መልሜ ቀሚብኩኝ። ዹዛኔ አስራ አምስት አመት ሞልቶኝ ነበርና ዘመቻ ላይ ተፈቅዶልኝ ተሳተፍኩ።
📚( ቡኻሪ ሙስሊምና ሌሎቜም ዘግበውታል።)

~ሎት ልጅ አቅመ አዳም (ብሉግ) መድሚሷ ዚምናውቅባ቞ው ምልክቶቜፊ

◌አንድኛፊ መንይ (ዹዘር ፈሳሜ)
◟ሁለተኛፊ "ብልት አካባቢ ፀጉር ማብቀሏ"
◟ሶስተኛፊ አስራ አምስት {15} አመት መሙላት
◟አራተኛፊ ሀይድ (ዹወር አበባ) ማዚት

~ ኹላይ ያዚና቞ው ወንድ ልጅ አቅመ አዳም (ብሉግ) መድሚሱ ኹሚጠቁሙ ምልክቶቜ ውስጡ አንዱን ካዚቜ ቡሉግ መድሚሷ ዚሚታወቅ ሲሆን ኚወንድ በተጚማሪ ሀይድ ማዚት ይገኝበታል።

⭕👉አንድ ሎት ልጅ በዚትኛውም ዚእድሜ ክልል ደሹጃ ላይ ሀይድ ካዚቜ ብሉግነት ዚመድሚሷ ምልክት ስለሆነ በግዎታነት ዹተደነገጉ ዚተለያዩ ዚኢባዳ አይነቶቜ መፈፀም በሷ ላይ ግዎታ ይሆናል።

⭕👉ማሳሰቢያ!!
     〰〰〰〰〰
①)–አንድ ሰው ብሉግ ደሹጃ ደሹሰ ለማለት ዚግድ ሁሉንም ምልክቶቜ መታዚት አለባ቞ው አይባልም። ይልቁንስ አንዱን ምልክት ኚታዚ በቂ ማሚጋገጫ ነውና በኢባዳ ላይ ዹተገደደ ይሆናል።
②)–አንድ ሰው አቅመ አዳምነት ደሹሰ ለማለት ዚግድ አስራ አምስት አመት ዚሚጠብቁ አሉ ይህ ስህተት ነው። አንድ ሰው ዹዘር ፈሳሜ ካላዚ፣ ፀጉር ካላበቀለ፣ ሎቷም ሀይድ ካላዚቜ ያለው አማራጭ አስራ አምስት አመት መጠበቅ ነው። ነገር ግን በዚትኛውም ዚእድሜ ክልል ላይ አንዱን ምልክት ቀድሞ ኚታዚ ያ በቂ ነውና ብሉግ ደሹሰ ይባላል።
③)–አንድ ሰው ሚመዷን ውስጥ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ብሉግ መድሚሱን ካሚጋገጠ መጀመርያውኑ ፃሞ ኹነበሹ በዛው ፃሙን ይቀጥላል። ፃመኛ ካልነበሚ ደሞ ኹዛ ሰአት ጀምሮ ኚምግብና መጠጥ መታቀብ ይኖርበታል ነገር ግን ቀዷ ዚማውጣት ግዎታ ዚለበትም።
            ፧              ፧
            ፧              ፧
    t.me/https_Asselfya
   
t.me/https_Asselfya
~ጣፋጭ ቲላዋ

በቁርአን እንገሠፅ

~
ውድ ወንድሞቜና እህቶቜ መቾም አዝካሚ ሶባህ እንደማትሚሱ ተስፋ አለኝ ።
ዚክር ዚደሚቀቜን ልብ ያሚጥባል ዚሚጠበቜ ልብ ይበልጥ ወደ አላህ እንድትቀርብ ያደርጋታል።


🖊ወንድማቜሁ አቡ ዓኢሻ ነኝ
https://t.me/Abuebrahim22322